• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ዕጹብ ሠዓልያን

February 3, 2014 07:03 am by Editor 1 Comment

እጅግ የረቀቀው ፤ የሰው ልጅ ሠልጥኖ

እጅግ መራቀቅን ፤ ሀ ያለው ጀግኖ

ለመቸውም ቢሆን ፤ ሆኖ የታደለ

ለሥልጣኔው ግንብ ፤ መሠረት የጣለ

ረቂቅ ሥዕላትን ፤ ነው ያኔ እንደሣለ

ያለእነዚያ ሥዕሉ ፤ በአገልግሎታቸው

አይገቡበት ነገር ፤ ምንም ስለሌለው

እንኳን እዚህ ሊደርስ ፤ እረቆ ሊማማር

ምንም ምን ለማድረግ ፤ ከቶም አይችል ነበር

በዓይን የማይታዩን ፤ በመሣሪያም ቢሆን

የማይዳሰሱም ፤ ብቻ የሚሰሙን

የሣለ ዕለት ነው ፤ ድንቅ አድርጎ እነሱን

በጆሮዎቹ ብቻ ፤ የሚያዳምጣቸውን

ለተለያዩ ድምፆች ፤ መልክ ቅርጻቸውን

እነ አበገደን ፤ እነ አሌፍ ቤትን

የሣለ ጊዜ ነው ፤ ጥንት በድሮ ዘመን

    የኛ አያቶች ደግሞ ፤ በዚህ ጥበባቸው

    እጅግ በረቀቀው ፤ የሥዕል ሞያቸው

    የሚያህላቸው የለም ፤ የሚስተካከላቸው

    ይሄን በክሂላቸው ፤ አሳይተዋልና

    ከማን ቋንቋ ይልቅ ፤ በዓለም ካለው ዝና

    በቋንቋ ያሉትን ፤ ድምፀ አካል ቁመና

    እያንዳንዳቸውን ፤ ነጥለው በማየት

    ብዙ የድምፅ ሥዕላትን ፤ ሥለው በማሳየት

    ፎነቲክ ይለዋል ፤ ሥነ ልሳን ትምህርት

ከዚህም በይበልጥ ፤ እጅግ የሚደንቀው

የእነዚህ ሥዕላት ፤ የዓሣሣል ዘያቸው

ሥውር ወይ አብስትራክት ፤ ተብሎ እንደሚጠራው

ኅብረ መልክ የያዙ ፤ ምሥጢራዊ ናቸው ፡፡

ሀ ናት ብለን ስንል ፤ አም አብሮ ይሰማል

ለ ናት ብለን ስንል ፤ ·ም አብሮ ተሥሏል

አናባቢውና ፤ ተነባቢው አብረው

በአንድ የሚታዩበት ፤ እንደ አንድ ተዋሕደው

ሲለበሪ ተብለዋል ፤ በዚህ ባሕሪያቸው ፡፡

በዚህ ልዩ ባሕሪው ፤ በመጢቅ ብቃቱ

ከሰው ልጅ ላሳናት ፤ በዓለም ካሉቱ

ብቸኛው መሆኑን ፤ የኛ የሆነው ሀብቱ

ተመስክሮለታል ፤ ገና ከበፊቱ

በዲልማን በቤንደር ፤ በየሊቃውንቱ

    መች በዚህ ይበቃና ፤ የአያቶቻችን ፤ የድምፅ ሥዕላት ምሥጢር

    የእኛ የድምፅ ሥዕላት ፤ ሰብአዊ አካል ናቸው ፤ ባለ ብዙ ዓይነት ግብር

    ሌላም ሌላም ብዙ ፤ ባሕል ወግ ሃይማኖት ፤ ሰብአዊ መስተጋብር

    የሚያሳዩ ናቸው ፤ትንቢት የሚነግሩ ፤ የሚያስተምሩ ምሥጢር

ተጽፈው ሲታዩም ፤ ስንኝና ሐረግ ፤ ቃላትን መሥርተው

የአካለ ሰለጥ ፤ ማለት የጅምናስቲክ ፤ ትርዒት ዓሳይተው ነው

አንደኛው አንድ እግሩን ፤ ቄንጥ ባለው ሁሌታ ፤ ከፍ አድርጎ አንሥቶ

አንዱም ወገብ ይዞ ፤ ሌላው እጅ ዘርግቶ

አንዱ አጎንብሶ ፤ ሌላውም ተጣጥፎ

አንዱ ተንበርክኮ ፤ ሌላው ተደግፎ

አንዱ በጭንቅላት ፤ ሌላው በጉልበቱ

አንዱ በትከሻው ፤ ሌላው በደረቱ

ጢባጢቧቸውን ፤ ሲያንኳሉ ሲመቱ ፡፡

የእናት አባቶቻችን ፤ ዕጹብ ሠዓልያን ፤ የሥዕል ችሎታ

ብዙ ነው ምሥጢሩ ፤ ብዙ ያመራምራል ፤ ብዙ አለው አንድምታ

ብዙ ሀገራትም ፤ በዚህ በመመሰጥ ፤ ተማርከው በሥዕሉ

ፊደሎቻቸውን ፤ ከእኛ እየቀዱ ፤ የወሰዱ አሉ

እንደ አርመን ያሉ ፤ ከእኛ እንደወሰዱ ፤ ይመሰክራሉ

ሌሎቹም ብዙዎች ፤ ከእኛ እንደወሰዱ ፤ ብዙ ማስረጃ አለ

የዘረኝነት ከል ፤ ለብሰው ቢዳፈኑም ፤ አይቀር እንደታበለ

የሚሆን ከሆነ ፤ የእውነት ቀን የሚመጣ ፤ እብለት የሚከዳ

ያኔ ይታወቃል ፤ የፊደል ዘር ሁሉ ፤ ከእኛ እንደተቀዳ

የእኛ እጅ የሌለበት ፤ የጥበብ መሠረት ፤ አንድም የለምና

ከሥነ-ፈለኩ ፤ የሕዋ ምርምር ፤ እስከ ፍልስፍና

ከአሥተዳደር ጥበብ ፤ ከቅኔ ድርሰቱ ፤ እስከ ሕክምና

ከዮቶር እስከ ኤዞፕ ፤ የተውኩት ዕውቀት ነው ፤ የዓለሙ ፋና

በየትኛውም መስክ ፤ እኛ ያልረገጥነው ፤ የለምና ዳና፡፡

የአውሮፓ ሀገራት ፤ ጥንታዊ ፈላስፎች ፤ ኢትዮጵያን ሲያገኑ

ሕዝቧንም ሲያደንቁ ፤ እንዲሁ ያለምክንያት ፤ ይመስላል በውኑ?

የሐበሻ ፊደላት ፤ ዕጹብ ድንቅ ሥዕላት ፤ ብዙ ውለታ አላቸው

የሥልጣኔን በር ፤ ወለል አርገው ከፍተው ፤ በማስገባታቸው

ለመላው ዓለም ሕዝብ ፤ ሥልጣኔን ይዘው ፤ በመቆየታቸው

ታሪክ ፍልስፍናን ፤ የባሕል ትውፊት ጥበብ ፤ ባለአደራ ሆነው

በትውልደ ትውልድ ፤ መረጃውን ይዘው ፤ በማሻገራቸው፡፡

የዕጹብ ድንቅ ሥዕላት ፤ ዕጹብ ሠዓልያን ፤ የሐበሻ አያቶች

ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው
ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው

ለጥበብ ባለቤት ፤ መሣሪያ ሆናቹህ ፤ የእግዚአብሔር እጆች

የሣላቹህት ሥዕል ፤ ለሰው ልጆች ሁሉ ፤ ሥልጣኔን ሰቷል

ምስጋና ይግባቹህ ፤ ዕጹብ ሠዓልያን ፤ ኩራት ሆናቹህናል፡፡

ምስጋና ይግባቹህ ፤ ዕጹብ ሠዓልያን ፤ ኩራት ሆናቹህናል፡፡

መጋቢት 2003 ዓ.ም.

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. ayalew says

    February 4, 2014 08:41 am at 8:41 am

    Thank you Ato Amsalu.
    I am still waiting your article related to Ethiopian Writing system.

    Ayalew

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የሲኖዶሱ ውዝግብ አካሄድና መጪው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ February 6, 2023 02:03 am
  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule