• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

48 + 1 ደቂቃ ቢያልፍ ምን እንደሚከተል ግንዛቤ ነበር

October 11, 2014 03:28 am by Editor Leave a Comment

ከስያሜው ጀምሮ እያነጋገረ ያለው የኢህአዴግ የአሜሪካ ጽ/ቤት የጥበቃ ሰራተኛ፣ በኢህአዴግ አባባል “ዲፕሎማት” አገር ለቆ እንዲወጣ ከተሰጠው የጊዜ ገደብ አንድ ደቂቃ ቢዘገይ ምን ሊከተል እንደሚችል አስቀድሞ ከስምምነት ላይ ተደርሶ እንደነበር ተጠቆመ። በስምምነቱ መሰረት ወዲ ወይኒ መባረሩ ከህወሃት ደጋፊዎችና አመራሮች ቅሬታ ማስነሳቱን አስመልክቶ አንድ ከፍተኛ የአሜሪካ ዲፕሎማት “ወያኔዎቹ የተሰራላቸው ውለታ አልገባቸውም ማለት ነው” ሲሉ መደመጣቸውን የጎልጉል ታማኝ ምንጭ ተናገሩ።

ለተቃውሞ ወደ ኢህአዴግ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ባመሩ ኢትዮጵያኖች ላይ ጥይት የተኮሰው የቀድሞው “ዲፕሎማት” ተመልሶ አሜሪካን መርገጥ እንዳይችል ተደርጎ የተባረረው በሁለቱም ወገኖች በተደረገ የውስጥ ስምምነት ነው። ለጉዳዩ እጅግ ቅርብ የሆኑ እንደገለጹት በአሜሪካው የምስጢር አገልግሎት (Secret Service) እና የዋሽንግተን ከተማ ፖሊስ ወዲ ወይኒን ለማሰር ወስነው ነበር። ውሳኔው ተግባራዊ ከመሆኑ በፊት እነ አቶ ግርማ ብሩ “ጓዳቸውን” ፈቅደው ለማሰናበት ቅድሚያውን በመውሰዳቸው ተጠርጣሪው ወንጀለኛ ሳይያዝ ቀርቷል። ከአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚ/ር መ/ቤት (State Department) የተሰጠው መግለጫም ቃል በቃልም ባይሆን ይህንኑ ያረጋገጠ ሆኗል።

የምስጢር አገልግሎቱም ሆነ የከተማው ፖሊስ ከ“ፖለቲካው ግንኙነት” ጋር በተያያዘ ስለሚፈጠረው የፖለቲካ ውዝግብ ቁብ እንደሌለው ስለ አሰራሩ የሚያውቁ ይናገራሉ። ይሁን እንጂ አቶ ግርማ ብሩ “በዲፕሎማሲያዊ ቋንቋ ተነጋግረናል” ሲሉ ለአገዛዙ ተላላኪ ድረገጽ ባለቤት እንዳረጋገጡት የስቴት ዲፓርትመንት ሰዎች የጊዜ ገደብ በማስቀመጥ ያልተፈረደበትን ወንጀለኛ፣ ወዲ ወይኒን፣ ካገር የሚወጣበትን መንገድ እንዳመቻቹ ዲፕሎማቱ አልሸሸጉም።

“አሜሪካ በቂ ጥበቃ አላደረገችልንም” በማለት ተቃውሞ የሚሰነዝሩት አፍቃሪ ህወሃቶች የሚሰነዝሩትን ተቃውሞ አስመልክቶ “የተደረገላቸውን ውለታ ካለመረዳት ነውነው፤ አፋቸውን ቢዘጉ (ዝም ቢሉ) የተሻለ ነው” ሲሉ የተደመጡት ከፍተኛ ሃላፊ፣ ይህንን ሲናገሩ ክፉኛ ተበሳጭተው እንደነበር ለማወቅ ተችሏል። የአሜሪካ መንግስት ተወንጃዩ ፍርድ ቤት ቀርቦ የሚዲያ ቁርስና ምሳ ሲሆን፣ ከዚሁ በጋር ከኢህአዴግ ጋር የሚነሳው ውዝግብና በምስራቅ አፍሪቃ በኩል ስለሚከወነው የፖለቲካ ጨዋታ ሲባል ጉዳዩ አሁን በተከናወነበት መልኩ እንዲጠናቀቅ መወሰኗን ከጉዳዩ ብዙ ርቀት የሌላቸው ክፍሎች አመልክተዋል። አቶ ግርማም ቢሆኑ “በዲፕሎማሲያዊ” ሲሉ ቋንቋውን ቢያስውቡትም ስምምነቱ ስለመኖሩ ከማሳበቅ ወደኋላ አላሉም።

በገደብ፣ በስምምነት የተቆረጠው 48 ሰዓት ቢተላለፍ ምን ሊከተል እንደሚችል ግንዛቤ በመኖሩ እነ አቶ ግርማ ወዲ ወይኒን አፋፍሰው ኢህአዴግ አለገደብ ወደሚገዛት አገር ልከውታል። ይህ ሳይሆን ቀርቶ አንድ ደቂቃ ቢዘገይ “ወዲ ወይኒ ወህኒ ወርደው ወዲ ወህኒ የሚል ስም ይሰጣቸው ነበር” ሲሉ ከዲሲ አካባቢ አንዳንዶች ተሳልቀዋል፡፡

ከኢህአዴግ ወገን አሁንም ዋሽንግተን ዲሲ ለተከራዩት ለጽህፈት ቤታቸው አሜሪካ ልዩ እንክብካቤ እንዲደረግ እየወተወቱ ነው። አሜሪካ ለዚህ ምንም ዓይነት የተለየ ጥበቃ የማታደርግ መሆኑ በተለያዩ መግለጫዎች የተነገረ ቢሆንም በህወሃት/የኢህአዴግ በኩል ጥያቄው እንዲነሳ ያደረገው መነሻ በድጋሚ ተመሳሳይ ውርደት እንዳይከሰትና ወደ ሌሎች አገራትም እንዳይዛመት ስጋት በመኖሩ ነው።

በተመሳሳይ ዜና ከአሜሪካ በሰዓታት ገደብ እንዲሰናበት የተደረገውና ተበደልን ባሉ ወገኖች ላይ ጥይት ሲተኩስ የነበረው ይኸው የትግራይ ተወላጅ ለሞራሉ በሚል ወደ ሌላ አገር ኤምባሲ ተዛውሮ እንዲሰራ አዲስ ምደባ እንደሚሰጠው የጎልጉል የውጪ ጉዳይ ምንጮች አመልክተዋል። ከህወሃት ከፍተኛ ባለስልጣን ወጣ የተባለው ይኸው የአዲሱ ምደባ ጉዳይ ለወዲ ወይኒ “ተጋዳላይነት”፤ ለሌሎች ደግሞ “አለኝታነትን ለማሳየት” በሚል ታስቦ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule