• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

48 + 1 ደቂቃ ቢያልፍ ምን እንደሚከተል ግንዛቤ ነበር

October 11, 2014 03:28 am by Editor Leave a Comment

ከስያሜው ጀምሮ እያነጋገረ ያለው የኢህአዴግ የአሜሪካ ጽ/ቤት የጥበቃ ሰራተኛ፣ በኢህአዴግ አባባል “ዲፕሎማት” አገር ለቆ እንዲወጣ ከተሰጠው የጊዜ ገደብ አንድ ደቂቃ ቢዘገይ ምን ሊከተል እንደሚችል አስቀድሞ ከስምምነት ላይ ተደርሶ እንደነበር ተጠቆመ። በስምምነቱ መሰረት ወዲ ወይኒ መባረሩ ከህወሃት ደጋፊዎችና አመራሮች ቅሬታ ማስነሳቱን አስመልክቶ አንድ ከፍተኛ የአሜሪካ ዲፕሎማት “ወያኔዎቹ የተሰራላቸው ውለታ አልገባቸውም ማለት ነው” ሲሉ መደመጣቸውን የጎልጉል ታማኝ ምንጭ ተናገሩ።

ለተቃውሞ ወደ ኢህአዴግ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ባመሩ ኢትዮጵያኖች ላይ ጥይት የተኮሰው የቀድሞው “ዲፕሎማት” ተመልሶ አሜሪካን መርገጥ እንዳይችል ተደርጎ የተባረረው በሁለቱም ወገኖች በተደረገ የውስጥ ስምምነት ነው። ለጉዳዩ እጅግ ቅርብ የሆኑ እንደገለጹት በአሜሪካው የምስጢር አገልግሎት (Secret Service) እና የዋሽንግተን ከተማ ፖሊስ ወዲ ወይኒን ለማሰር ወስነው ነበር። ውሳኔው ተግባራዊ ከመሆኑ በፊት እነ አቶ ግርማ ብሩ “ጓዳቸውን” ፈቅደው ለማሰናበት ቅድሚያውን በመውሰዳቸው ተጠርጣሪው ወንጀለኛ ሳይያዝ ቀርቷል። ከአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚ/ር መ/ቤት (State Department) የተሰጠው መግለጫም ቃል በቃልም ባይሆን ይህንኑ ያረጋገጠ ሆኗል።

የምስጢር አገልግሎቱም ሆነ የከተማው ፖሊስ ከ“ፖለቲካው ግንኙነት” ጋር በተያያዘ ስለሚፈጠረው የፖለቲካ ውዝግብ ቁብ እንደሌለው ስለ አሰራሩ የሚያውቁ ይናገራሉ። ይሁን እንጂ አቶ ግርማ ብሩ “በዲፕሎማሲያዊ ቋንቋ ተነጋግረናል” ሲሉ ለአገዛዙ ተላላኪ ድረገጽ ባለቤት እንዳረጋገጡት የስቴት ዲፓርትመንት ሰዎች የጊዜ ገደብ በማስቀመጥ ያልተፈረደበትን ወንጀለኛ፣ ወዲ ወይኒን፣ ካገር የሚወጣበትን መንገድ እንዳመቻቹ ዲፕሎማቱ አልሸሸጉም።

“አሜሪካ በቂ ጥበቃ አላደረገችልንም” በማለት ተቃውሞ የሚሰነዝሩት አፍቃሪ ህወሃቶች የሚሰነዝሩትን ተቃውሞ አስመልክቶ “የተደረገላቸውን ውለታ ካለመረዳት ነውነው፤ አፋቸውን ቢዘጉ (ዝም ቢሉ) የተሻለ ነው” ሲሉ የተደመጡት ከፍተኛ ሃላፊ፣ ይህንን ሲናገሩ ክፉኛ ተበሳጭተው እንደነበር ለማወቅ ተችሏል። የአሜሪካ መንግስት ተወንጃዩ ፍርድ ቤት ቀርቦ የሚዲያ ቁርስና ምሳ ሲሆን፣ ከዚሁ በጋር ከኢህአዴግ ጋር የሚነሳው ውዝግብና በምስራቅ አፍሪቃ በኩል ስለሚከወነው የፖለቲካ ጨዋታ ሲባል ጉዳዩ አሁን በተከናወነበት መልኩ እንዲጠናቀቅ መወሰኗን ከጉዳዩ ብዙ ርቀት የሌላቸው ክፍሎች አመልክተዋል። አቶ ግርማም ቢሆኑ “በዲፕሎማሲያዊ” ሲሉ ቋንቋውን ቢያስውቡትም ስምምነቱ ስለመኖሩ ከማሳበቅ ወደኋላ አላሉም።

በገደብ፣ በስምምነት የተቆረጠው 48 ሰዓት ቢተላለፍ ምን ሊከተል እንደሚችል ግንዛቤ በመኖሩ እነ አቶ ግርማ ወዲ ወይኒን አፋፍሰው ኢህአዴግ አለገደብ ወደሚገዛት አገር ልከውታል። ይህ ሳይሆን ቀርቶ አንድ ደቂቃ ቢዘገይ “ወዲ ወይኒ ወህኒ ወርደው ወዲ ወህኒ የሚል ስም ይሰጣቸው ነበር” ሲሉ ከዲሲ አካባቢ አንዳንዶች ተሳልቀዋል፡፡

ከኢህአዴግ ወገን አሁንም ዋሽንግተን ዲሲ ለተከራዩት ለጽህፈት ቤታቸው አሜሪካ ልዩ እንክብካቤ እንዲደረግ እየወተወቱ ነው። አሜሪካ ለዚህ ምንም ዓይነት የተለየ ጥበቃ የማታደርግ መሆኑ በተለያዩ መግለጫዎች የተነገረ ቢሆንም በህወሃት/የኢህአዴግ በኩል ጥያቄው እንዲነሳ ያደረገው መነሻ በድጋሚ ተመሳሳይ ውርደት እንዳይከሰትና ወደ ሌሎች አገራትም እንዳይዛመት ስጋት በመኖሩ ነው።

በተመሳሳይ ዜና ከአሜሪካ በሰዓታት ገደብ እንዲሰናበት የተደረገውና ተበደልን ባሉ ወገኖች ላይ ጥይት ሲተኩስ የነበረው ይኸው የትግራይ ተወላጅ ለሞራሉ በሚል ወደ ሌላ አገር ኤምባሲ ተዛውሮ እንዲሰራ አዲስ ምደባ እንደሚሰጠው የጎልጉል የውጪ ጉዳይ ምንጮች አመልክተዋል። ከህወሃት ከፍተኛ ባለስልጣን ወጣ የተባለው ይኸው የአዲሱ ምደባ ጉዳይ ለወዲ ወይኒ “ተጋዳላይነት”፤ ለሌሎች ደግሞ “አለኝታነትን ለማሳየት” በሚል ታስቦ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule