• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ድንቄም ሀዘን!

March 15, 2017 11:23 pm by Editor 1 Comment

ሲሉ ሰምታ ዶሮ ሞተች ከቋት ገብታ ይሉ ነበር ሳይማሩ የተማሩት ጠቢባን የሆኑ ቀደምት እናትና አባቶቻችን። ድህነት ዛዝላውን ጭኖባቸው የመከራ ኑሮ የነበሩ ወገኖቻችንን መንግስት የቆለለው የቆሻሻ ምርት ተጭኗቸው ሲያልቁ መንግስት የሶስት ቀን ሀዘን ተቀመጠ የሚል አስቂኝ ወሬ በሰማሁ ጊዜ ነበር የጠቀስኩት የዶሮዋ ምሳሌ ትዝ ያለኝ። ሀገር አለን ብለው እንደወግና ስርአታቸው አደባባይ ሊውሉ የወጡ ወገኖቻችንን ባልተደበቀ ሸር በቢሸፍቱ ከተማ እንደወጡ ያስቀረው መንግስት በወቅቱ የሶስት ቀን ሀዘን በማወጅ በሙታንም ህያዋንም ላይ ቀልዶ ነበር። እነሆ አሁን ደግሞ በከመረው ቆሻሻ ህፃናትና ስቶችን ጨፍልቆ ከፈጀ በኋላ ሳቂታውን ፓርላማ ሰብስቦ በሉ አሁን ደግሞ የሀዘን ሰአት ነው አለ አሉ። እንዴት ያለ ቀልደኛ መንግስት ነው ጃል? ለገደለው ህዝብ ሆዱ የሚባባ ሩሩህ መንግስት! የዚህ አይነቱ ቀልድስ የሚያበቃው የት ላይ ይሆን?

በመሰረቱ የአንድ ከተማ አስተዳደር ሀላፊነት ቆሻሻ መቆለል ሳይሆን ከተማውን ማፅዳትና ህዝብንም ከበሽታ መከላከል አልነበረም? ከዚህ ቀደም የአፍሪካ መዲና የሆነችውን ታላቅ ከተማ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ በማቆሸሽ ህዝብ ባ ባጣዳፊ ተቅማጥና ሁከት ማለቅ ሲጀምር “እጃችሁን ታጠቡ” ሲል የአንደኛ ክፍል የሳይንስ መፅሃፍን  በማጣቀስ ያላቅሙ የሚያስተዳድረውን ህዝብ ሲመክር ያልገረመው አልነበረም። ፍየል ወዲህ ቅዝምዝም ወዲያ። በከተማ ንፅህና ጉድለት የመጣውን ችግር እጃችሁን ሳትታጠቡ እየበላችሁ በሽታ አመጣችሁብን ሲል እንደልማዱ ለህዝብ ያለውን ንቀት ደገመው። ምን ደገመው ብቻ ደጋገመው ልበል እንጂ።

ነገሩማ የተባለውን ቀርቶ መስማት የሚፈልገውን ብቻ የሚሰማ መንግስት የህዝብን ችግር በበትክክለኛ ስሙ እንዲጠራ እንዴት መጠበቅ ይቻላል? ነፃነት አጣን ሲባል ስራ አጣን ነው ያላችሁኝ ይልና ስራ እንደሚያመጣ ሁሉ ወደጓዳ ገብቶ ጠመንጃ ይዞ ይመጣል። ስኳር ጠፋ ሲባል እኔ ስልጣን ከያዝኩ ጀምሮ ገበሬው ስኳር መጠጣት ስለጀመረ ነው አለ። ኧረ መብራት ተቸገርን ሲባል ምንላድርግ ልማቱ እኮ ነው ሲል አስረዳ። ሰብዓዊ መብት ለምን ይረገጣል ሲባል በህግ የበላይነት የሚያምንና ሃላፊነት የሚሰማው መንግስት ስላለን እኮ ነው ሲል አስተማረን። እንዴት ያለ ጉድ እኮ ነው ጎበዝ!

ከተነሳሁበት ነጥብ ወጣሁ መሰለኝ፤ የክምር ቆሻሻው ጉዳይ። መከራ በተጫነው ህዝብ ላይ ቆሻሻ ጭኖ ከገደሉ በኋላ ባንዲራ ማውረድና ሀዘን ማወጅ የቀበሮ ባህታዊነት ይመስለኛል። ሃላፊነት የሚሰማው መንግስት ተግባር ሰው እንዳይሞት መጠበቅ እንጂ ገድሎ ማጠን አይደለም። በዚህ ክስተት መንግስት ማዘን ሳይሆን ማፈር አለበት። ያውስ ሃፍረት የባህሪው ከሆነ አይደል? ጎበዝ ማለት ለጥፋቱ ሀላፊነት ወስዶ ይቅርታ መጠየቅና ጉዳዩ የሚመለከታቸውን ሙሰኛ ተሿሚዎቹን መቅጣት ነው። ብቻ ይኅስ ቢሆን ለመገዛት እንጂ ገዢዎቹን በህግ ለመጠየቅ የታደለ ህዝብ በሌለበት ሀገር እንዴት ይታሰባል። እና እባካችሁ እንደፈረደብን ዝም ብለን እንሙትበት፤ እየሳቃችሁ አትዘኑልን በሏቸው። ጥያቄም አለኝ፤ ሀገር መምራቱስ ቢቀር፣  ቤት ጠርጎ መኖር እንኳን እንዴት ተሳናችሁ የሚል። የወገኖቻችንን ነፍስ ይማር።

ህሩይ ደምሴ (zobar2006@gmail.com)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Tadesse says

    March 19, 2017 12:22 am at 12:22 am

    ewnet gud new,asafari, new,hezbun cheresut tegrewm sayker.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm
  • የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ? የመንጣቱ ምክንያት? January 23, 2025 03:41 pm
  • ታሪካዊዉ የፋሲል ቤተመንግሥት ለምን ነጣ? January 23, 2025 03:04 pm
  • የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተወልደ አስተዳደር ዘመን ለተሠራ ስህተት 425ሺ ዶላር ተቀጣ December 14, 2024 01:44 am
  • በትግራይ ከሞትና ከአካላዊ ጉዳት የተረፉት ለስደት ተዳርገዋል November 27, 2024 12:09 pm
  • የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሠራሩን እንዲያርም ጥብቅ መመሪያ ተሰጠው November 27, 2024 11:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule