• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሁለት ላሞች/የስርዓተ ማህበሮች ትርጓሜ

September 20, 2014 01:53 am by Editor 1 Comment

የየዘመኑን ስርዓተ ማህበር ምንነት ቅልጥጥ አድርጎ ለማሳየትና የማያሻማ ፍቺ ለመስጠት የየሀገሩ የቱርጁማን ጠበብት ያልቧጠጡት የሃሳብ ኮረኮንችና ያልዳሰሱት ሸካራ ብሂል የለም፡፡ በየዘመኑ ለተከሰቱ የማህበረሰብ አስተሳሰቦች ከተለያዩ ምሁራን የተለያየ ፍቺና ትርጓሜ ተሰጥቷል፡፡ ምሁራኑ በዘመናችን ከደረሱበት መተርጉም አንዱ በሁለት ላሞች ተምሳሌትነት የቀረበው ነው፡፡ የነጠረውን ፍጹማዊ መተርጉም እስኪያገኙ ድረስ የፈረንጅ ሊቃውንት ይህንን በሁለት ላሞች ላይ የተመሰረተ ተምሳሌታዊ መተርጉም ሰጥተዋልና ከግልዎ ግምገማ ጋር በማያያዝ ይህችን አጭር ሐተታ ያነጻጽሩት ዘንድ እነሆ ብለናል፡፡

1. ሶሻሊዝም

እርስዎ ሁለት ላሞች ይኖርዎታል እንበል፡፡ በሶሻሊዝም ስርዓተ-ህይወት እስካሉ ድረስ አንዲቷን ላም ለራስዎ መድበው ሌላይቱን ለጎረቤትዎ መዳረግ ግዴታዎ ነው፡፡

2. ኮሚኒዝም

እርስዎ ሁለት ላሞች ይኖርዎታል እንበል፡፡ በኮሚኒዝም ስርዓተ ማህበር ውስጥ እስካሉ ድረስ መንግሥታዊው የኮሚኒስት ፓርቲ ሁለቱንም ላሞችዎን ይወስድብዎትና የድርሻዎ ያህል ብቻ ወተት ያድልዎታል፡፡

3. ፋሺዝም

እርስዎ መንታ ላሞች አሉዎት እንበል፡፡ በፋሺዝም ስርዓ-ህይወት እስካሉ ድረስ የሚገዛዎ የመንግሥት ቁንጮ ሁለቱንም ላሞችዎን ይነጥቅና የሚያልበውን ወተት ለራስዎ ይሸጥልዎታል፡፡

4. ናዚዝም

እርስዎ መንታ ላሞች አሉዎት እንበል፡፡ በናዚዝም ስርዓተ-ሕይወት እስካሉ ድረስ ጨካኙ መንግስት ሁለቱንም ላሞችዎን ዘርፎ ከወሰዳቸው በኋላ ራስዎን ጭምር ያርድዎታል፡፡

5. ቢሮክራሲዝም

እርስዎ ጥንድ ላሞች አሉዎት እንበል፡፡ የሚኖሩበት ስርዓተ ማህበር ቢሮክራሲዝም እስከሆነ ድረስ ሁለቱንም ላሞች ይወስድብዎትና አንደኛይቱን ያርዳታል፤ ሌላይቱን ግን እያለበ ወተቷን እመቅ ያፈሰዋል፡፡

6. ካፒታሊዝም

እርስዎ የሁለት ላሞች ባለቤት ነዎት እንበል፡፡ የሚኖሩበት ስርዓተ ማህበር ካፒታሊዝም እስከሆነ ድረስ በዘዴ ይወስድብዎና አንዲቷን ላም ከሸጠ በኋላ ለገዛ ራሱ ለማራባት ሲል በተሸጠችው ላም ገንዘብ ኮርማ ይገዘባበታል፡፡

ማን ቀረ? ማኦይዝም፤… ሌኒንዘም፣ . .. ራዲካሊዝም፣… ሊብራሊዝም፣ ኒኦ-ሊብራሊዝም፣ አብዮታዊ ዲሞክራሲ ወዘተ… አሉ፡፡ እስቲ በዚህ የሁለት ላሞች ቀመር መሰረት ራስዎ የሚኖሩበትን ስርዓተ ማህበር ለመተርጎም ይሞክሩ፡፡
*****
(ሀይሉ ገብረዮሐንስ፣ ኢትኦጵ መጽሔት፣ ቅጽ 3፣ ቁጥር 031፣ ታህሳስ 1994፣ ገጽ 4)
*****
በጉዳዩ ላይ ድረገጾችን ስንመለከት ያገኘነውን አንድ እኛ እንጨምር:-

7. የቻይና ዓይነት ኮሙኒዝም

እርስዎ መንታ ላሞች አሉዎት እንበል፡፡ እነዚህ ሁለት ላሞች በ300 ሰዎች ይታለባሉ:: ስርዓተ ማህበሩ ባገር ሁሉ ሥራዓጥነት በጭራሽ የለም፣ ምርታማነት አድጓል፣ ተመንድጓል፣ ህዳሴ፣ ውዳሴ ነው ይላል:: እውነት የሚዘግበውን ጋዜጠኛ ይረሸናል፡፡
—–
ጽሁፉን ያገኘነው ከAfendi Muteki ፌስቡክ ገጽ ነው፡፡

Afendi Muteki is a researcher and author of ethnography and history with special focus on the peoples of East Ethiopia. You may follow him on his facebook page. Just click here.

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. wondimu bialifew says

    September 20, 2014 09:34 am at 9:34 am

    greater

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዛሬ ‘ኃያል ነን’ የሚሉ ሀገራት ኢትዮጵያ ላይ በሚዲያ /በመረጃ/፣ በዲፕሎማሲ፣ በሳይበር እና በተልእኮ የተቀነባበረ ‘ግራጫ ጦርነት’ እያካሄዱባት ነው” ጠ/ሚ ዐቢይ July 7, 2022 10:03 am
  • የኦሮሞ ልሂቃንና ፖለቲከኞች በአማራ ተወላጆች ላይ እየደረሰ ያለውን “የዘር ማጥፋት” ወንጀል እንዲያወግዙት አብን ጠየቀ July 6, 2022 01:38 pm
  • “አማራን ኦሮሚያ ውስጥ የመግደል እና የመጨፍጨፍ እቅድ የኦነግ ሳይሆን የኦሮሚያ ብልጽግና ነው” አቶ ሃንጋሳ July 6, 2022 01:53 am
  • “በኢትዮጵያዊያን የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ በመግባት ሀገሪቱን ማተራመስ አለብን” አይማን አብድልአዚዝ ግብጻዊው ፖለቲከኛ July 5, 2022 12:57 pm
  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule