• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሁለት ላሞች/የስርዓተ ማህበሮች ትርጓሜ

September 20, 2014 01:53 am by Editor 1 Comment

የየዘመኑን ስርዓተ ማህበር ምንነት ቅልጥጥ አድርጎ ለማሳየትና የማያሻማ ፍቺ ለመስጠት የየሀገሩ የቱርጁማን ጠበብት ያልቧጠጡት የሃሳብ ኮረኮንችና ያልዳሰሱት ሸካራ ብሂል የለም፡፡ በየዘመኑ ለተከሰቱ የማህበረሰብ አስተሳሰቦች ከተለያዩ ምሁራን የተለያየ ፍቺና ትርጓሜ ተሰጥቷል፡፡ ምሁራኑ በዘመናችን ከደረሱበት መተርጉም አንዱ በሁለት ላሞች ተምሳሌትነት የቀረበው ነው፡፡ የነጠረውን ፍጹማዊ መተርጉም እስኪያገኙ ድረስ የፈረንጅ ሊቃውንት ይህንን በሁለት ላሞች ላይ የተመሰረተ ተምሳሌታዊ መተርጉም ሰጥተዋልና ከግልዎ ግምገማ ጋር በማያያዝ ይህችን አጭር ሐተታ ያነጻጽሩት ዘንድ እነሆ ብለናል፡፡

1. ሶሻሊዝም

እርስዎ ሁለት ላሞች ይኖርዎታል እንበል፡፡ በሶሻሊዝም ስርዓተ-ህይወት እስካሉ ድረስ አንዲቷን ላም ለራስዎ መድበው ሌላይቱን ለጎረቤትዎ መዳረግ ግዴታዎ ነው፡፡

2. ኮሚኒዝም

እርስዎ ሁለት ላሞች ይኖርዎታል እንበል፡፡ በኮሚኒዝም ስርዓተ ማህበር ውስጥ እስካሉ ድረስ መንግሥታዊው የኮሚኒስት ፓርቲ ሁለቱንም ላሞችዎን ይወስድብዎትና የድርሻዎ ያህል ብቻ ወተት ያድልዎታል፡፡

3. ፋሺዝም

እርስዎ መንታ ላሞች አሉዎት እንበል፡፡ በፋሺዝም ስርዓ-ህይወት እስካሉ ድረስ የሚገዛዎ የመንግሥት ቁንጮ ሁለቱንም ላሞችዎን ይነጥቅና የሚያልበውን ወተት ለራስዎ ይሸጥልዎታል፡፡

4. ናዚዝም

እርስዎ መንታ ላሞች አሉዎት እንበል፡፡ በናዚዝም ስርዓተ-ሕይወት እስካሉ ድረስ ጨካኙ መንግስት ሁለቱንም ላሞችዎን ዘርፎ ከወሰዳቸው በኋላ ራስዎን ጭምር ያርድዎታል፡፡

5. ቢሮክራሲዝም

እርስዎ ጥንድ ላሞች አሉዎት እንበል፡፡ የሚኖሩበት ስርዓተ ማህበር ቢሮክራሲዝም እስከሆነ ድረስ ሁለቱንም ላሞች ይወስድብዎትና አንደኛይቱን ያርዳታል፤ ሌላይቱን ግን እያለበ ወተቷን እመቅ ያፈሰዋል፡፡

6. ካፒታሊዝም

እርስዎ የሁለት ላሞች ባለቤት ነዎት እንበል፡፡ የሚኖሩበት ስርዓተ ማህበር ካፒታሊዝም እስከሆነ ድረስ በዘዴ ይወስድብዎና አንዲቷን ላም ከሸጠ በኋላ ለገዛ ራሱ ለማራባት ሲል በተሸጠችው ላም ገንዘብ ኮርማ ይገዘባበታል፡፡

ማን ቀረ? ማኦይዝም፤… ሌኒንዘም፣ . .. ራዲካሊዝም፣… ሊብራሊዝም፣ ኒኦ-ሊብራሊዝም፣ አብዮታዊ ዲሞክራሲ ወዘተ… አሉ፡፡ እስቲ በዚህ የሁለት ላሞች ቀመር መሰረት ራስዎ የሚኖሩበትን ስርዓተ ማህበር ለመተርጎም ይሞክሩ፡፡
*****
(ሀይሉ ገብረዮሐንስ፣ ኢትኦጵ መጽሔት፣ ቅጽ 3፣ ቁጥር 031፣ ታህሳስ 1994፣ ገጽ 4)
*****
በጉዳዩ ላይ ድረገጾችን ስንመለከት ያገኘነውን አንድ እኛ እንጨምር:-

7. የቻይና ዓይነት ኮሙኒዝም

እርስዎ መንታ ላሞች አሉዎት እንበል፡፡ እነዚህ ሁለት ላሞች በ300 ሰዎች ይታለባሉ:: ስርዓተ ማህበሩ ባገር ሁሉ ሥራዓጥነት በጭራሽ የለም፣ ምርታማነት አድጓል፣ ተመንድጓል፣ ህዳሴ፣ ውዳሴ ነው ይላል:: እውነት የሚዘግበውን ጋዜጠኛ ይረሸናል፡፡
—–
ጽሁፉን ያገኘነው ከAfendi Muteki ፌስቡክ ገጽ ነው፡፡

Afendi Muteki is a researcher and author of ethnography and history with special focus on the peoples of East Ethiopia. You may follow him on his facebook page. Just click here.

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. wondimu bialifew says

    September 20, 2014 09:34 am at 9:34 am

    greater

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule