• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የትራምፕ ለግብፅ መወገን የውስጥ ክፍፍል ፈጥሯል

July 22, 2020 11:47 pm by Editor 3 Comments

አሜሪካ ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን ዕርዳታ ለመከልከል እያሰበች ነው

በአባይ ግድብ ጉዳይ ከጅምሩ ለግብፅ ወገንተኛ መሆኗን ስታሳይ የነበረችው አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ የዕርዳታ ዕቀባ ለማድረግ እያሰበች መሆኑን ፎሪይን ፖሊሲ (Foreign Policy) ዛሬ (ረቡዕ) ባወጣው ዘገባ ገለጸ። ይህ የፕሬዚዳንት ትራምፕ አቋም በአስተዳደራቸው ውስጥ ክፍፍል መፍጠሩ አብሮ ተዘግቧል።   

አባይን በተመለከተ “ማድረግ የምችለውን መንገድ ሁሉ እጠቀማለሁ” በማለት ስትናገር የነበረችው ግብፅ የፕሬዚዳንት ትራምፕን እጅ በመጠምዘዝ በኢትዮጵያ ላይ እርምጃ እንዲወሰድ በርትታ እየሠራች ነው።

ግብፅና አሜሪካ ለዘመናት የቆየ የጥቅም ተጋሪዎች ናቸው። እኤአ ከ1980ዓም ጀምሮ አሜሪካ ለግብፅ $40 ቢሊዮን ዶላር የሚሊታሪና $30 ቢሊዮን ዶላር የኢኮኖሚ ዕርዳታ ማድረጓን የስቴት ዲፓርትመንት መረጃ ያመለክታል።

በበርካታ ጥቅሞችና ቀጣናዊ ግንኙነቶች የተሳሰሩት ግብፅና አሜሪካ ለየትኛውም ፓርቲ የወገነ ፕሬዚዳንት ቢመረጥ ከግብፅ ጋር ያለው የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ ሲቀየር አልታየም። የረጅም ጊዜ የአሜሪካ ወዳጅ የነበሩት አምባገነኑ ሆስኒ ሙባረክ ከሥልጣን እንዳይወርዱ አሜሪካ የጣረችውን ያህል በሕጋዊ መንገድ የተመረጡትን መሐመድ ሙርሲን በሕገወጥ መንገድ እንዲወርዱ በማድረግ በኩል ጉልህ ሚና ተጫውታለች።

በስዊዝ ካናል ግብፅ ባላት የባህር የበላይነት ለአሜሪካ የሚሰጠው ጥቅም፤ ግብጽ የእስራኤል ወዳጅ በመሆኗ እና ኢራን የአካባቢውን የበላይነት ለመውሰድ የምታደርገው ጥረት እንደ እስራኤልና አሜሪካ ግብፅንም የሚያሳስባት በመሆኑ፤ በመካከለኛው ምስራቅና በሰሜን አፍሪቃ በየጊዜው የሚነሳው አሸባሪነት እና ጽንፈንነት መባባስ፤ ግብፅ ያላት ጂኦፖለቲካዊ አቀማመጥና ይህም ለአሜሪካ ያለው ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ፤ ወዘተ አሜሪካንን እና ግብፅን በወፍራሙ አጋምዷቸዋል።

አባይን በተመለከተ የትራምፕ አስተዳደር ጉዳዩን እየተመለከተ ያለው በአፍሪካ መነጽር ወይም በኢትዮጵያ ላይ ምን ዓይነት ተፅዕኖ ያሳድራል ከሚለው አኳያ እንዳልሆነ ፎሪይን ፖሊሲ የኋይት ሃውስ ምንጮቹን ጠቅሶ ዘግቧል።     

በተለይ የአባይ ድርድር በሦስቱ አገራት (ኢትዮጵያ፣ ግብፅና ሱዳን) እና በአሜሪካው የገንዘብ ሚኒስቴር መ/ቤት አማካኝነት እንዲካሄድ ከተወሰነ ወዲህ በገንዘብ ሚ/ር እና በተለምዶ እንዲህ ዓይነት ድርድሮችን በመሸምገል የሚታወቀው ውጭ ጉዳይ (ስቴት ዲፓርትመንት) መካከል መቃቃር ተፈጥሯል።

“ሁኔታው እንዲህ አይደለም” በማለት የሚናገሩት የገንዘብ ሚ/ር ቃል አቀባይ “የገንዘብ ሚኒስትሩና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በዚህ ሒደት ውስጥ በትብብር እየሠሩ ነው፤ በሁለቱ መ/ቤቶች ያሉት ቡድኖችም እንዲሁ” በማለት ተናግረዋል።  

አሜሪካ ለኢትዮጵያ ለመከልከል ያሰበችው ዕርዳታ ዓይነት ግልጽ አልሆነም። ነገርግን የሰብዓዊ ዕርዳታን እንደማይጠቀልል የአስተዳደሩ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ይናገራሉ። በ2019 አሜሪካ ለኢትዮጵያ ከሰጠችው $824.3 ሚሊዮን ዶላር ውስጥ $497.3 ሚሊዮን ዶላሩ ለሰብዓዊ ዕርዳታ የተለገሰ ነበር።

ስማቸው እንዳይጠቀስ በመናገር ለፎሪይን ፖሊሲ አስተያየታቸውን የሰጡ የተለያዩ ከፍተኛ ባለሥልጣናት እንደሚሉት በስቴት ዲፓርትመንት እና በዩናይትድ ስቴትስ የዓለምአቀፍ ልማት ኤጀንሲ ውስጥ የሚገኙ ሹሞች አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ ለመውሰድ ያሰበችውን የዕርዳታ ቅነሳ ይቃወማሉ ብለዋል። በተለይ ኢትዮጵያ በእንደዚህ ዓይነት አደገኛ የፖለቲካ ለውጥ ውስጥ ባለችበት ጊዜ ጉዳዩ በአዲስ አበባና በዋሽንግተን መካከል እየተንገረገበ ያለውን ግንኙነት ይጎዳዋል በማለት ይናገራሉ።

ከዚህ አንጻር አንድ ባለሥልጣን እንደተናገሩት ስቴት ዲፓርትመንት ከገንዘብ ሚኒስቴር የመጣውን ጥያቄ “እያቀዛቀዘው” ይገኛል ብለዋል።

ሌሎች ሁለት ባለሥልጣናት ደግሞ ገንዘብ ሚ/ር ስቴት ዲፓርትመንትን ከድርድሩ ቆርጦታል፤ በአዲስ አበባ፣ በግብጽና በካርቱም የሚገኙ ዲፕሎማቶችም እንዲሁ ከድርድሩ ተቆርጠው ወጥተዋል ይላሉ።

ከዚህ በተጻጻሪው ደግሞ ሌላ ባለሥልጣን ይህ እውነት አይደለም፤ የሦስቱም አገራት ተደራዳሪ ቡድኖችና በየአገራቱ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ በትብብርና በቅርበት እየሠሩ ነው በማለት ያስተባብላሉ።

የትራምፕ አስተዳደር በዚህ ዓይነት ውዝግብ ውስጥ ባለበት ወቅት ሌሎች የአገር ውስጥ ችግሮችና የመጪው የአሜሪካ ምርጫ ተዳምረው የዕርዳታ ዕቀባውን ሊያለዝቡት ይችላሉ የሚል አስተያየቶችም ይሰጣሉ። ሌሎች ደግሞ አሜሪካ ከግብፅ ጋር ያላትን ወዳጅነት በይፋ በማሳየት የተጠቀመችበት ትርፋ አልባ፣ ለፖለቲካ ፍጆታ ሲባል የተወራ ነው በሚል ያጣጥሉታል።

በዚህ ሁሉ ውዝግብ ውስጥ ኢትዮጵያ በዓላማዋ ጸንታ የመጀመሪያው ውሃ ሙሌት ማድረጓ የዓለምአቀፍ ሚዲያን ትኩረት የሳበ ዜና ሆኗል።

ባልተጨበጠ ዕቅድ በስሜት ብቻ በመገፋፋት በቀድሞው የበረሃ ወንበዴዎች መሪ መለስ ዜናዊና ግብረአበሮቹ ሲመዘበር የቆየውን ግድብ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አመራር ባጭር ጊዜ ውስጥ ለዚህ ፍሬ ማብቃቱ በርካታ ኢትዮጵያውያንን አስደስቷል፤ የባለቤት ስሜትም አጎናጽፏቸዋል።   


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: Egypt, GERD, usa

Reader Interactions

Comments

  1. Bedlu says

    July 23, 2020 12:37 pm at 12:37 pm

    Trash! Who was the first to come up with the idea and start work? Low iq and full of complex…..get civilized..barbarians

    Reply
  2. Amhara says

    July 23, 2020 05:04 pm at 5:04 pm

    I hate TPLF but it was Melese who brilliantly crafted and established the construction and negotiation. He deserves better praise for this, whether it was for the empahtic ‘great Tigrai’ or Ethiopia. I am really disappointed with the closing sentence. It was the other morons who looted everything of this project and make no mistake it was in good shape somehow. Otherwise, the current management with all these small progress would not have made it; consciously deceived the progress for political reasons. Please correct your last sentence on Meles.

    Reply
  3. Daniel Demissie says

    July 23, 2020 09:34 pm at 9:34 pm

    Sure. I totally agree with your comment.We as Ethiopians should learn to give everyone the credit due to them. I am one of the Ethiopians who hate the policies & practices of TPLF-led government. I worked with them for a while and know how crooked the system from top to bottom was. It was designed to paralyze Ethiopia and Ethiopiawinet, and to some extent they achieved their goal, and Meles was the chief architect of the project. At the same time, he was the guy who took initiative to start the huge project of building the Renaissance Dam. Even if there have been a lot of mischiefs along the way he deserves some sort of genuine appreciation & acknowledgement for the courage he showed in embarking the first step of this national project which united Ethiopians from corner to corner, and around the globe. I hope somebody will have a gut to build a monument for Mr. Meles for the job he did to begin the construction of the dam, and we are not going to demolish it at one point as we here & there trying to do to some historical symbols of our common history.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule