• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የዘረኛው ህወሐት የምስረታ ሰነድ በቁጥር አንድ ጠላትነት ያስቀመጠው ህዝብ

September 30, 2017 12:06 am by Editor Leave a Comment

ህወሐት በትግል ፕሮግራሙ የአማራን ያክል  የሚጠላው ሌላ  ህዝብም ሆነ አካል  እንደሌለ በግልጽ ያስቀመጠ ድርጅት ነው። የአማራ ህዝብ መሬት እያረሰ የሚኖር ደሀ ህዝብ ቢሆንም በህወሐት የምስረታ  ሰነዶች እንደ ገዥ ብሄር ተፈርጆአል።

አስገራሚው ነገር  አማራ ንጉሱንም ሆነ ደርግን በማስወገድ ትግል ከሌሎች ህዝቦች እኩል ድርሻ የነበረው ህዝብ ነው። እንደ ህዝብ በህወሐት የሚጠላው በተጨበጠ ምክንያት አይደለም። ህወሐት  የአማራን በሌሎች እንዲጠላ ካደረገባቸው የተደራጁ  ስብከቶች በተጨማሪ የብሄረሰቡን ማንነት የሚያዳክምባቸው ልዩ ልዩ እርምጃዎችንም ወስዶአል። አንዱ ሴቶች  ፍላጎታቸው ሳይጠየቅ የረጅም ግዜ የወሊድ መከላከያ መርፌ እንዲወጉ ማድረጉ ነው። በዚህም እኤአ 2007 የህዝብ ቆጠራ የህዝብ ቁጥሩ ከሚጠበቀው በ3 ሚሊዮን የቀነሰ ብቸኛ ህዝብ ሆኖአል። ሌላው በትግራይ  ክልል የልዩ ወረዳ አስተዳደር ክብር የሚገባቸው ልዩ ልዩ ብሄረሰቦች እያሉ ህወሐት አማራ ክልል መጥቶ የልዩ ዞን ፍላጎት ቀስቀሰሽና አስፈጻሚ መሆኑም ከዚሁ  አማራን ለማዳከም ካለው ጽኑ ፍላጎት ጋር ይያያዛል።

የአማራን ክልል መሬት በጉልበት ወደራሱ የማካለል ስራም ሌላው ተግባሩ ነው። ራሳቸውን በአማራነት የሚገልጹ ሰዎችን በግፊት ወደ ትግሬነት የመቀየር ስራም ሰርቶአል። ህወሐት በፕሮግራሙ ውስጥ አማራን ግንባር ቀደም ጠላቴ ነው ብሎ ከመጻፍ ጀምሮ በተከታታይ በዚህ ህዝብ ላይ እየፈጸማቸው ያሉ ግፎች መነሻቸው ምንድን ነው?

የመጀመሪያው መሰረታዊ ምክንያት ህወሐት ኢትዮጵያን እንደ ሀገር ፈጽሞ ማየት አለመፈለጉ ነው። ይህ ጥላቻ  ምንጩ የወራሪው ኢጣልያ አገልጋይ ከነበሩ ጥቂት  ባንዳ  የትግራይ ልጆች ነው። እነዚህ በቀድሞው  የህወሐት አባል በአቶ ገብረመድን  አጠራር ሻምቡሽ  እየተባሉ የሚጠሩት የትግራይ ባንዳዎች በልጆቻቸው በኩል ስብከቱን በማጉላት  በአሁኑ ወቅት ብዙ ተከታይ አግኝተዋል። የአማራ ህዝብ ደግሞ ፖለቲከኛ ሆነ ደሀ ገበሬ ከሌላው የኢትዮጵያ ህዝብ ጋር ሀገሪቷን  ከወራሪ ሲከላከል የቆየ ህዝብ ነበር። በዚህም ቂም ተይዞበታል።

ብዙዎች የዋሆች ህወሐት ኢትዮጵያዊ መባል ካልፈለገ  ለምን ታዲያ  ሁሉን አድራጊ በሆነበት በአሁን ወቅት መገንጠልን አይፈጽመውም  የሚል ጥያቄ ይጠይቃሉ። መልሱ የትግራይ የኢኮኖሚ፣ የፖለቲካ፣ የስነልቦና የበላይነቱ እስካልተነካበት የመገንጠል ፍላጎቱን ገሀድ አያወጣም የሚል ይሆናል። አዎ እንደ ነብር ደምህን እየመጠጠ ይቆያል። ደምህ ካለቀ ወይም አሻፈረኝ ካልክ ግን  ያኔ ይተገብረዋል።

ሁለተኛው ምክንያት የተለመደው የከፋፍለህ ግዛ ባህሪው ነው። ሌሎች የኢትዮጵያ ህዝቦችን ኣስፈራርቶ ለመግዛት  የሚፈሩት ጠላት ሊፈጥርላቸው ይገባል። ለዚህም አማራን አስቀምጦላቸዋል። በሁለተኛነትም ከአማራ ህዝብ ጋር ህብረት እንዳይፈጥሩ ማድረጊያ ስልቱም ነው። ይህ ስልቱም ከጠበቀው በላይ ሰርቶለታል። በዚህም  የአማራ ህዝብ ለትውልዶች ከኖረባቸው አካባቢዎች ተደጋጋሚ ጥቃቶች  ተፈጽሞበታል። በኦሮሚያ፣ ደቡብ  ብ/ብ/ህ ክልል እና በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል  ውስጥ የተፈጸሙትን ግድያዎችና ማፈናቀል መጥቀስ ይቻላል።

የአለም ህዝቦች መልቲ ካልራሊዝምን እንደ ሀብት በሚቆጥሩበት  በዚህ የስልጣኔ ዘመን አባቶቹ የጣልያን ሻምቡሽ ሆነው የተነገራቸው ስብከት ላይ ተቸንክሮ የቆመውን ህወሐት በተግባር በቃ ልንለው ይገባል። አለበለዚያ ግን የሰሞኑ የአለም ባንክ  ይፋ ያወጣው የኢትዮጵያ ክልሎች  የመንገድ ግንባታ ግስጋሴ የ 10 ዓመት ሪፖርት በግልጽ እንዳስቀመጠው (ትግራይ ክልል አንደኛ እንዲሁም አማራ መጨረሻ) ህወሀት የአማራንም ሆነ ሌሎች ህዝቦችን ደም መምጠጡን ይቀጥላል።

ያሬድ አውግቸው (yaredawgichew@gmail.com)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule