• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አማሮችን በገጀራ! ህወሃት በኢሉባቦር እየሰራ ነው

October 22, 2017 12:01 pm by Editor 5 Comments

ህወሃት የአማራው ሕዝብ ላይ ያለው አቋም ከፋሺሽት ጣልያን የተወሰደ ውርስ ነው። በበላይ ዘለቀ ይመራ የነበረው ጦር ጣልያንን እስከፍጻሜው ተፋልሞ ባዋረደበት ግዜ – የጣልያኑ ጀነራል ደቦኖ የተናገረው በታሪክ መዛግብት ላይ ተቀምጧል።

“ደጋግሜ ተናግሬ ነበር። አማራና ኦርቶዶክ ቤተ ክርስትያን ካልጠፉ ሰላም ልናገኝ አንችልም። “

አቦይ ስብሃት እና አባይ ጸሃዬም ይህንኑ የደቦኖ አነጋገር በተደጋጋሚ ሲሉት ተደምጠዋል። የዛሬ 40 ዓመት የወጣው የህወሀት ማኒፌስቶም በገፅ 15 እና 16 ላይ “ጨቋኟ አማራ ህብረተሰብአዊ እረፍትና ሰላም አታገኝም” ብሎናል።

ይህ ፕሮግራም በወረቀት ላይ ብቻ ሰፍሮ አልቀረም። በተግባርም እያሳዩን ነው። በማጂ፤ ጉራ ፈርዳ ወረዳ ሠፋሪ አርሶ አደሮች በአካባቢው ባለሥልጣናት ተገድደው ቀያቸውን ለቅቀው ወጥተዋል፤ በቤኒሻንጉል፣ በጋምቤላ በአስር ሺ የሚቆጠሩ አማሮች  ላይ የማፈናቀል ዘመቻ ተደርጓል፣ ከዚህ ቀደምም በበደኖ፣ በኢንቁፍቱ፣ በወተር፣ በአርሲ፣ ወዘተ አማሮች ላይ የደረሰው ግፍ በታሪክ ታይቶም ተሰምቶም አያውቅም። እስካሁን መልስ ያላገኘው በሕዝብና ቤት ቆጠራ 2.5 ሚሊዮን አማሮች የገቡበት ያለመታወቁም አንዱ የመሰሪ ፕሮግራም እቅድ ነው።

የህወሃት ማኒፌስቶ ወደ ተግባር ተለውጦ፣ ላለፉት 26 አመታት ግፍ እየሰራ ረጅም ተጉዟል። ወልቃይትና ቅማንት ላይ ሲደርስ ደግሞ ማንነትን የሚፈታተን ትንቅንቅ ላይ ይገኛል።

የገጀራው እልቂት ግን ተስፋ የመቁረጥ ምልክት ሳይሆን ይቀራል? ነገሩ እንዲህ ነው። እየተንጠባጠበ ከሚወድቀው የንግድ አጋራቸው ይልቅ፤ የ”ጣና ኬኛ” ፖለቲካ እነ ደብረጽዮንን እረፍት እንደነሳቸው በስፋት ይነገራል። የማይወድዱት የአማራና የኦሮሞ ሕዝብ ህብረት መፈጠሩ ብቻ ሳይሆን፣ እንደ ገና ዳቦ የሚለበልብ ነቄ ትውልድ ሳያስቡት መጣባቸው።

ለጭንቅ ግዜ የቀመሩት የፖለቲካ ሂሳብም እንደቀድሞው ማርሽ እየቀየሩ የሚሄዱበት መንገድ አልሆን አላቸው። ስለዚህ ፊት ለፊት ገጀራ ይዘው መጨፍጨፍ/ማስጨፍጨፍ ተያይዘዋል። በዚህ ሁኔታ ስንቱን ገድለው እንደሚዘልቁት የሚያውቁት ግን አይምስልም።

ወትሮም ውርደት ጌጥ በሆነላቸው የብአዴን ዋርድያዎች ይህ የሚያሳስባቸው ጉዳይ አይደለም። ይልቁንም የአስደናቂው  የ”ጣና ኬኛ” ፖለቲካ አቀንቃኞች ለዚህ ጉዳይ ምላሽ ሊሰጡበት እንደሚችሉ እርግጠኞች እየሆንን ነው። እነ ለማ መገርሳ ከነበሩበት የፍርሃት ቋት ራሳቸውን አውጥተው ከህወሃት እኩል መነጋገር የጀመሩ ይመስላል።

የእነ ደመቀ መኮንን ነገር ባይነሳ ይሻላል። ሲያሻው በቃርያ ጥፊ ሲያጮላቸው – ሲያሻው ደግሞ ሲተፋባቸው ይዘልቁታል እንጂ እንዲተነፍሱም እድል አይሰጣቸውም። በዘረኝነት ውቅያኖስ ውስጥ እየዋኙ ላሉት ለእነ ደብረጽዮን ከጥፊዋ ዋጋ ይልቅ የጥፊዋ ጠቀሜታ ነው የምትታያቸው። እነ ገዱ አንዳርጋቸው አማራው ሲታረድ እነሆ ዝም ብለዋል።

ግዜውን ጨርሶ በባከነ ሰዓት እየተንፈራገጠ ያለው የትግሬ ቡድን ዛሬ በኢሉባቦር ከ20 በላይ ዐማሮች በአንድ ቀን ብቻ በገጀራ መጨፍጨፉ እጅግ የሚያንገበግብ ቢሆንም አዲስ አይደለም። ገዳዮቹ ግን ከቶውንም ከፍርድ አያመልጡም።   መውደቅያቸው ላይ ማጠፍያ ሲያጥራቸው ታርዶ እንደሚንፈራፈር ዶሮ የሆኑ ይመስላል … ይህ ሁሉ ሲሆን የአማራው ህዝብ ትዕግስት እንደ ፍርሃት ተቆጥሮ ከሆነ ግን ትልቅ ስህተት ነው። ሁሉንም ግዜ ይፈታዋል!

ክንፉ አሰፋ


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Takele says

    October 23, 2017 05:04 pm at 5:04 pm

    Dear friends and friends of Ethiopia
    Our country is on the edge of civil war unless and otherwise we the concerned people put our maximum effort to avert this catastrophic situation that we are going to face anytime or any day in the near future  .  Let us try to unite our people in regardless of political party affiliation , ethnic sentiments , religion  etc .  Let all of us talk about reconciliation and bring some sort of mechanism that  help us come together and solve our differences .  We don’t have to leave the problem for a certain group of people or party or civic organizations bring remedy for our naturally wealthy and beautiful country .  The only solution  for our problem is reconciliation . Both sides have to refrain from their rigid stand which   benefit no one . Reconciliation is a master key in building reliable  peace and avoiding conflict . Coming to the round table and try to solve the current situation will serve as a bridge for relationship among people , antagonistic groups  civil society and  the government . It is clear that the process is very sensitive  and everybody has to do his best approach to the nature of our country’s  conflict . Let we all preach about the methods of reconciliation and exercise the Geda system , healing  etc . The role of Ethiopian academicians , the international community and the diaspora is very crucial . We the concerned people of Ethiopia have to give our spare time ,money and talent for reconciliation process to happen without delay .   Reconciliation is both a goal and a process. There are many key elements to a successful reconciliation such as
    . an inclusive national dialogue 
    .  political will
    . security and freedom to speak and move etc .  Truth is important, particularly to prevent historical facts from being presented one-sidedly or linked to religious or ethnic adversaries. 
    We the people who are aspiring good future for the generation to come will do our best to facilitate the situation and form an ad- hoc committee   . The diasporas , traditional leaders , churches , mosques  and business associations will be the actors that can play a seminal and catalytic role as an asset and need to be positively engaged in the process . The road to reconciliation is so complicated because reconciliation is a contested concept with a wide array of confusing and competing approaches, and it must always be carefully tailored to the given context particularly to our country . When dealing with our so complicated Ethiopian problem it will not be difficult to know where and when to begin . ( to be continued)
      tkmamo@yahoo.com

      

     

     .
     

    Reply
  2. Goshu says

    October 29, 2017 07:17 am at 7:17 am

    Dear Takele,

    Your have totally misunderstood the intentions and missions of the tigrian bandas tasked by the Birtish and American monsters to dismantle Ethiopia. Now, the Oromos and Amharas together TPLF is in a total confusion. I am quite sure that tpl will be crashed and crashed by force. The time for dialogue has been over.

    Reply
    • takele says

      November 3, 2017 04:14 am at 4:14 am

      Take a deep breath bro and think twice . The only way to solve our beloved country”s problem is reconciliation . Our people are suffering by man made crises so , we all have the responsibility of facilitating conducive atmosphere for meditation which is immediately followed by reconciliation .
      We don’t want another war and let us say bygone be bygone .

      Reply
  3. አቶ በዛብህ በዛ says

    November 4, 2017 01:04 pm at 1:04 pm

    የወያኔ ፋሽሽት መንጋ አማሮችን በመጨፍጨፍና በማገለል የጀመረውን የዘር ማጽዳት ዘመቻ ዛሬ በኦሮሞ ወገኖቻችን ላይ አጠናክሮ ቀጥሎበታል። ስለሆነም ወያኔን ከምድረ ኢትዮጵያ ነቃቅሎ ከማስወገድ በስተቀር ሌላ አማራጭ ከጸሐይ በታች ለማገኘት አይቻልም። በወያኔ ወይንም በተለጣፊዎቹ በኩል ለህዝብና ለሀገር የሚጠቅም ለውጥ ሊመጣ ይችላል ብሎ ማሰብ ከዝንብ ማር ይገኛል ብሎ እንደመጠበቅ ይቆጠራል። አንድ አምደኛ ስለወያኔ ተፈጥሮአዊ ባህሪ ሲገልጥ ” ወያኔን የምናምነው ገድለነው ከሞተም በሁዋላ አመድ እስከሚሆን ድረስ አቃጥለነው አመዱንም አርቀን ከቀበርነው በሁዋላ ነው” ብሎ ነበር። ትክክል አገላለጥ ነው። ወያኔን የምናምነው ከምድረ ገጽ ከጠፋ በሁዋላ ነው በህይወት ያለ ወያኔን ማመን ጉሙን እንደመዝገ የማቻል ነገር ነው።

    Reply
  4. Tadesse says

    November 7, 2017 09:54 am at 9:54 am

    It is nice to read this,what is wejane here,the people we tigrians hate most too.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule