• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የትግራይ ኢንዱስትሪ ቢሮ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ሪፖርት ማረጋገጫ ሰጠ

February 13, 2024 02:01 am by Editor Leave a Comment

* በ“ጋዜጠኛነት” ስም የሚፈጸመው የሚዲያ ሸፍጥ

በትግራይ ክልል “ከ200 በላይ ኢንዱስትሪዎች ሥራ ጀምረዋል” በሚል ፓርላማ ላይ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የቀረበው ሪፖርት “ከእውነት የራቀ ነው” ሲሉ የከሰሱት የትግራይ ክልል ኢንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊ 212 ኢንዱስትሪዎች ከሰላም ስምምነቱ በኋላ ሥራ እንዲጀመሩ ክስ ባቀረቡበት ዜና ጎን ለጎን አስታወቁ።

ዜናው የክስ ሳይሆን አሃዱና ቲክቫህ በቅብብሎሽ አንዱ ሌላውን ዋቢ አድርገው ባሰራጩት ዜና መግቢያና ርዕስ ቀዳሚ ያደረጉት “ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በፓርላማ ያቀረቡት ሪፖርት ከዕውነት የራቀ ነው” በሚል ነው። ዜናው በመሪ ርዕሱ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ላይ የቀረበውን ክስ አላብራራም፣ እርሳቸው ካሉት ጋርም አላነጻጸረም።

የትግራይ ኢንዱስትሪ ቢሮ ም/ኃላፊ አቶ መሐሪ ገብረሚካኤል “በአሁኑ ወቅት በክልሉ ሥራ የጀመሩት ለትላልቅ ኢንዱስትሪዎች ጥሬ ዕቃ የሚያቀርቡ ሁለት መቶ አነስተኛ ፣ አምስት መካከለኛ እንዲሁም አሥራ ሁለት ትላልቅ ኢንዱስትሪዎች ናቸው” ሲል ዜናው በትምህርተ ጥቅስ የተጠቀሰውን አንቀጽ ማስፈሩን ያዩ ለዝግጅት ክፍላችን “ሚዲያዎቹ ዜና አያነቡም፣ ወይም አይረዱም፣ አለያም ሙያዊ ግድፈት አለባቸው” ሲሉ ተችተዋል።

በኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት እሽቅድድም በሚመስል መልኩ ለላይክና ተከታይ ለማሰባሰብ የሚሰሩ ዜናዎች በስሙ የሚማልበትን “ጋዜጠኝነት” እያደር ቁልቁል እያወረደው እንደሆነ ያመለከቱ፣ ሚዲያዎቹ ለማስተላለፍ የፈለጉትም አሳብ በዕርጋታ ሊሰሩ እንደሚገባ መክረዋል። የተጠቀሱትን የክልሉ የኢንዱስትሪ ቢሮ ምክትል ኃላፊ እውነት በመናገራቸው ሊመሰገኑ እንደሚገባም ጠቁመዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በቅርቡ በፓርላማ ሪፖርታቸውና ማብራሪያቸው ከሰላም ስምምነቱ ወዲህ በትግራይ ከሁለት መቶ በላይ አምራች ኢንዱስትሪዎች ሥራ እንዲጀመሩ መደረጉን መግለጻቸው ይታወሳል። ለትግራይ በቀጥታ ከፌደራል መንግሥት ከ37 ቢሊዮን ብር በላይ ድጋፍ መሰጠቱን በጠቆሙበት ማብራሪያቸው ከሁለት መቶ በላይ አምራች ኢንዱስትሪዎች ወደ ሥራ እንዲገቡ መደረጋቸውን ከማመልከታቸው ውጭ ዝርዝር ጉዳይ አላነሱም።

በዚሁ የትግራይን ጨምሮ መላው የአገሪቱ ህዝብ እየሰማ ማብራሪያ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ “ወደ ሥራ የገቡት ከሁለት መቶ በላይ አምራች ኢንዱስትሪዎች አነስተኛ፣ መካከለኛ፣ ታላላቅ ኢንዱስትሪዎች፣ ጥሬ ዕቃ አቅራቢዎች ወዘተ” ብለው በዝርዝር ሲያስረዱ አልተሰሙም፤ በዚያ ልክ እንዲያስረዱም አይጠበቅም።

መረጃውን የሰጡት ኃላፊ ሳይሆን ሚዲያዎቹ ባልተባለ ጉዳይ ነቀፌታን ማቅረባቸውና ከንቀፌታው በፊት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአደባባይ የተናገሩትን ንግግር ባልሰማ ማለፋቸው መነሻው ምን እንደሆነ እንዳልገባቸው ዜና የሚከታተሉ በጽሁፍ “ይገርማል” ሲሉ ልከውልናል። ዜናውን ዐውዱ እንዲስተካከል አድርጎ መሥራቱም ያስፈለገው በዚሁ ጥቆማ መሠረት ነው።

ለነጮች ግብዓት ይሆን ዘንድ ከወር በፊት የሪፖርተር እንግሊዝኛ ጋዜጣ “የአድዋ መታሰቢያ ሙዚየም በአርክቴክት ችግር ሳቢያ ለአፍሪቃ መሪዎች ጉባኤ እንደማይደርስ ወዳጆቼ ነገሩኝ” ሲል ያስተላለፈውን ዜናም ያስታወሱ አሉ።

ሲጎርስና መሬት ሲሰጠው የታከለ ዑማ ቃል አቀባይ የነበረው ሪፖርተር አገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ መቋቋሙ ይፋ በሆነበት ቀን፣ ከፓርላማ ፌስቡክ ባገኘው ዜና “የምክክር ኮሚሽኑ ሥራዬን አቆማለሁ ሲል አስጠነቀቀ” በማለት የዘገበውን ለአብነት የሚጠቅሱ “በመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ማስታወቂያ የሽያጭ ኪሳቸውን የሚያድለቡ ሚዲያዎች፣ ከመንግሥት እጅ ሽልማት እየወሰዱ ቅምጥ ላደረጋቸው ኃይል ዓላማ ግብዓት መሆናቸው አንድ ሊባል ይገባል” ሲሉ ለሚሰሙ ጥቆማ አቅርበዋል።

የትግራይ ኢንዱስትሪ ቢሮ ምክትል ኃላፊ የሰጡት መረጃ ዕውነትነት ያለው በመሆኑ ለሌሎች የክልሉ ቢሮዎችና ኃላፊዎች ትምህርት የሚሰጥ እንደሆነ ዜናውን ያተመለከቱ ተናግረዋል። አያይዘውም ዜናውን በቅብብሎሽ የዘገቡት ሚዲያዎች እርስ በርስ የሚጣላ ዜና ከመሥራት ራሳቸውን ቢያርቁና ከአደባባይ ስህተት ራሳቸውን እንዲጠብቁ መክረዋል።

ሚዲያዎቹ በዘገባቸው ማገባደጃ “ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ጥር 28 ቀን 2016 በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 14ኛ መደበኛ ስብሰባ ተገኝተው ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት ከ200 በላይ ኢንዱስትሪዎች ሥራ ጀምረው ዜጎችን ተጠቃሚ እያደረጉ ነው ብለው ነበር” የሚል ሃረግ ከትተው ከላይ በርዕስ የተነሱበት የውግዘት ዜና በራሳቸው አምክነውታል። ዜናውን ጠልቀው ሳያነቡ በማኅበራዊ ገጾች የሚራቡ በሚበዙበት አገር መረጃው ምን ያህል ጉዳት እንደሚያስከትል ከወዲሁ መገንዘብ እንደሚገባ ተመልክቷል።

“ይሁን እንጂ” ይላል ዘገባው የጠቅላይ ሚኒስትሩን ንግግር ካስታወሰ በኋላ፣ “ይሁን እንጂ የትግራይ ክልል ኢንዱስትሪ ቢሮ፤ በክልሉ ከጦርነቱ በኋላ ሥራ የጀመሩ ኢንዱስትሪዎችን በተመለከተ ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ለጠቅላይ ሚኒስትሩ የቀረበላቸው ሪፖርት በተጨባጭ መሬት ላይ ካለው እውነታ ጋር የተራራቀ ነው ሲል ሪፖርቱን ውድቅ አድርጓል” ሲል ዳግም ከራሱ ጋር ይጣላል። ሪፖርቱ ከራሱ ጋር አንቀጽ በአንቀጽ ከመላተም አልፎ “መሬት ላይ ካለው ዕውነት ጋር የተራራቀ ነው” ሲል የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ለጠቅላይ ሚኒስትሩ የተሳሳተ ሪፖርት ስለማቅረቡ በንፅፅር አላሳየም።

አቶ መላኩ አለበል የሚመሩት የኢንዱስትሪ ሚኒስትር አቀረበ የተባለው የተሳሳተ ሪፖርት በዜናው ጭራሽ አልተካተተም። ወይም ኃላፊው እንዲዘረዝሩና የስህተተ መረጃ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ስለመቅረቡ በዋቢነት የተቀመጠ አንዳችም አመልካች ሃረግ አልተካተተም። ይህ በሆነበት “ሃሰተኛ” ተብሎ የተፈረደበት ኢንዱስትሪ ሚኒስቴርን ለመጠየቅና መረጃውን ምሉዕ ለማድረግ ስለመሞከሩም የተባለ ነገር የለም።

“የቢሮው ም/ኃላፊ አቶ መሐሪ ገብረሚካኤል በአሁኑ ወቅት በክልሉ ሥራ የጀመሩት ለትላልቅ ኢንዱስትሪዎች ጥሬ ዕቃ የሚያቀርቡ 200 አነስተኛ፣ 5 መካከለኛ እንዲሁም 12 ትላልቅ ኢንዱስትሪዎች ናቸው” ብለዋል በማለት በአሀዱና በቲክቫህ የተዘገበው ዜና ተቃውሞ ለማቅረብ የተዘገበ ቢሆንም ከሰላም ስምምነቱ ወዲህ በትግራይ ሥራ የጀመሩ ኢንዱስትሪዎች ከሁለት መቶ በላይ መሆናቸውን ጠቅሰው ዝርዝር ሳያቀርቡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ለተናገሩት ማረጋጋጫ የሰጠ ዜና ሆኗል። ዜናው 217 የተለያዩ ደረጃ ያሏቸው ኢንዱስትሪዎች ሥራ መጀመራቸውን ኃላፊው አምነው ምስክርነት እንደሰጡ ማረጋገጫ ሆኖ የሚመዘገብ ሆኗል።

ዜናው ከላይ ከዘገበው ጋር ዳግም ሲላተም “ነገር ግን” ብሎ የጀምራል። “ነገር ግን ሁለት መቶ አሥራ ሰባት ኢንዱስትሪዎች ሁለገብ ድጋፍ ተደርጎላቸው ሥራ ጀምረዋል ተብሎ የተገለጸው ከእውነታው ጋር የተራራቀ ነው ሲሉ ተናግረዋል” ሲል ኃላፊውን እንደፈለገው ያላጋቸዋል።

“ከፍተኛ የብድር እና የወለድ መጠንን ጨምሮ የጥሬ ዕቃ አቅርቦት ችግር አሁንም ግዙፍ ኢንዱስትሪዎች ሥራ እንዳይጀምሩ ትልቅ እንቅፋት ሆኖ በቀጠለበት አግባብ ሁለገብ ድጋፍ ተደርጓል ለማለት አያስደፍርም ሲሉ ተችተዋል” የሚለው ዘገባ የድጋፍና የጥሬ ዕቃ አቅርቦት ችግር በመላው አገሪቱ የሚታይ እንደሆነ መንግሥት በተለያዩ ጊዜያት የሚያስታውቀው ችግር መሆኑን አንስቶ ተቺውን ስለመጠየቁ የተባለ ነገር የለም።

ከትግራይ ጦርነት ጋር ተያይዞ በተጣለ ማዕቀብ፣ የኢኮኖሚ ሸርና ሽፍትነት፣ የብድር መቆምና የዓለም ወቅታዊ ቁመና እንደ ምክንያት ተጠቅሶ በፓርላማ መቀረቡን ኃላፊው አስታውሶ ዜናውን ለማመጣጠን ስንዝር ያልተራመደው አሃዱ ሚዲያ፣ “ከ37 ቢሊዮን ብሩ ስንት ደረሳችሁ? ስንቱን ተጠቀማችሁበት” ብሎ ቢያንስ ለማዳመቂያ እንኳን ስለመጠየቁ በዜናው አልተመለከተም።

“በክልሉ በነበረው ግጭት የተነሳ የኢንዱስትሪ ዘርፉ ከነበረበት ከፍተኛ ጉዳት በዘላቂነት እንዲያገግም መሬት የወረዱና ተጨባጭ ድጋፎች እንዲደረጉም ነው የትግራይ ክልል ኢንዱስትሪ ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ መሐሪ ጥሪ ያቀረቡት” በሚል የተቋጨው ዜና ቲክቫህ “ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የአሀዱ ነው” ሲል ምስጋና በመስጠት ነው።

ዜናውን ከአስተያየት ጋር በካሜራ አንስተው የላኩልን “ኃላፊው ሃቀኛ ናቸው። ሌሎችም እሳቸውን መምሰል አለባቸው። ለዚህ ተግባራቸው በአደባባይ ምስጋና ሊቸራቸው ይገባል፤ ሌሎቹም ቢሮዎች እንዲሁ ምስክርነታቸውን ቢሰጡ መልካም ነው፤ መተማመንን ይፈጥራል፤ ዜና ሳታነቡ ርዕስ አይታችሁ የምታጋሩም ተማሩበት” ብለዋል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News, Politics Tagged With: ahadu radio, ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tikvah, tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule