• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ወ/ሮ ትዕግስት ከታገቱበት ሲና ተለቀቁ!!

May 21, 2013 08:42 am by Editor Leave a Comment

የሱዳን፣ የኤርትራና የግብጽ ዜግነት ባላቸው ራሻይዳዎች ታፍነው ወደ ሲና በረሃ የተወሰዱት ወ/ሮ ትዕግስት ገብሬ ካይሮ መግባታቸው ታወቀ። ወ/ሮ ትዕግስት ቅዳሜ ረፋዱ ላይ ካይሮ የገቡት አጋቾቹ እንዲሰጣቸው ከጠየቁት 25 ሺህ ዶላር በድርድር 15 ሺህ ዶላር ተከፍሏቸው ነው።

ዜናውን በሰሙ ማግስት “የወ/ሮ ትግስት የርዳታ እጆች” በማለት ተሰባስበው የነፍስ አድን ዘመቻውን ከጀመሩት መካከል አንዷ የሆኑት ወ/ሮ ሰብለ ደምሴ በተለይ ለጎልጉል እንደተናገሩት ወ/ሮ ትዕግስት ከአሰቃቂው የሲና በረሃ ወጥተው ካይሮ የገቡት ከአራት ወራት በኋላ ነው።

አጋቾቹ ወ/ሮ ትዕግስትን በ10 ሺህ ዶላር እንደገዙ በመግለጽ 25 ሺህ ብር ካልተከፈላቸው እንደማይለቁና የሰውነት ክፍላቸውን በመሸጥ ያወጡትን ወጪ እንደሚሸፍኑ ይደራደሩ እንደነበር የገለጹት ወ/ሮ ገነት “አስቀድመን 10 ሺህ ዶላር ከፈልን። ቀሪውን 5 ሺህ ዶላር ወ/ሮ ትዕግስት አገር ቤት ያሏቸው ከብቶች ተሽጠውና ከያለበት ተለቃቅሞ እንደሚከፈል በመግለጽ ተደራድረን ከተስማማን በኋላ ክፍያውን ፈጸምን” ብለዋል።

ሱዳን ሸገራብ በሚባለው ሰፊ የስደተኞች ጣቢያ ከባለቤታቸውና ከሁለት ልጆቻቸው ጋር ይኖሩ የነበሩ ወ/ሮ ትዕግስት ገብሬ ጥር 22 ቀን 2005 ዓ ም ቤተ ክርስቲያን ለመሳለም በካምፕ ውስጥ ከሚገኘው ቤታቸው  በግምት ሰላሳ ሜትር ሳይርቁ ራሻይዳዎች አፍነዋቸው እንደወሰዷቸው ጎልጉል መዘገቡ ይታወሳል።

ወ/ሮ ሰብለ ደምሴ፣ ወ/ሮ አዜብ ሮባና ወ/ሮ ኢየሩሳሌም ጸጋዬ ሰብዓዊነት ረፍት ነስቷቸው ባካሄዱት ዘመቻ ከተለያዩ ቤተክርስቲያናት፣ በጉዳዩ ሃዘን ከገባቸው ወገኖች፣ በተሰበሰበ ገንዘብ ወ/ሮ ትዕግስት ህይወታቸው ሳያልፍ ከዕገታው ነጻ መሆናቸው ልዩ ደስታ እንደፈጠረ ያስረዱት ወ/ሮ ሰብለ፣ “ነፍስ ለማዳን በተደረገው ጥሪ የተባበሩ ሚዲያዎች፣ ድርጅቶች፣ ግለሰቦችና ሁሉም ዓይነት የህብረተሰብ ክፍል በህብረታችን ስም ታላቅ ምስጋና እናቀርባለን። ወ/ሮ ትዕግስትና ባለቤታቸውን አግኝተናል። ሃዘናቸው በወገኖቻቸው ርዳታ ተለውጦ የደስታ እንባ አንብተዋል። እኛም ተደስተናል” የሚል መልዕክት አስተላልፈዋል።

“ግን” አሉ ወ/ሮ ሰብለ “ግን ብዙ ወገኖች በተመሳሳይ ችግር ላይ እንዳሉ ስናስብ አሁንም እረፍት የለንም። በምንኖርበት ሁሉ በተለያዩ መንገዶች ድርጊቱ የሚፈጸምበት ቦታ ላይ ያሉ ባለስልጣኖች እንዲህ ያለውን አስነዋሪና ሰብአዊነት የጎደለው ድርጊት እንዲያስቆሙ ትግላችንን መቀጠል አለብን” ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል። ወ/ሮ ትዕግስት አሁን ህክምና እየተደረገላቸው ስለሆኑ ሲያገግሙ ለሌሎች ትምህርት ይሆን ዘንድ፣ በቀጣይ በትብብር ድምጻችንን ለማሰማት የሚያተጋንን ቁምነገር እንዲካፍሉ እንደሚደረግ አስታውቀዋል።

ወ/ሮ ትዕግስት ከሲና በረሃ መልስ ያጋጠማቸውንና በትክክል የተመለከቱትን ለወገኖቻቸው እንደሚያካፍሉ የገለጹት ወ/ሮ ሰብለ ህብረታቸው ዝርዝር ጉዳይ የያዘ የምስጋና መልዕክት አዘጋጅቶ እንደሚያሰራጭ ገልጸዋል።

አፋኞቹ ራሻይዳዎች ናቸው። ራሻይዳ የቆዳቸው ቀለም ጠየም ያለ የሱዳን፣ የኤርትራና የግብጽ ዜግነት ያላቸው ሲሆኑ ቀደም ሲል ከሶስት እስከ አራት ሺህ ዶላር እየተቀበሉ በደላላ አማካይነት ስደተኞችን በሲና በረሃ ወደ ግብጽ ያሻግሩ ነበር። እስራኤል በሲና በረሃ ወደ ድንበሯን ዘልቀው የሚገቡበትን የስውር መንገድ ስትዘጋው ራሻይዳዎቹ የገቢ ምንጫቸው ተዘጋ። ገንዘብ የለመዱት ወንበዴዎች የንግዱን ስልት ቀየሩና ሰው ማፈን ጀመሩ። አፈናውንም ከሚያካሂዱባቸው መንገዶች ጥቂቶቹ ድንበር አቋርጠው የሚጓዙትን አድፍጠው በመያዝ፣ ስደተኞችን ከስደተኛ ካምፕ አፍኖ በመውሰድ፣ ከሌሎች አፋኞች ስደተኞችን በአነስተኛ ገንዘብ በመግዛት እንደሆነ በወቅቱ መዘገባችን ይታወሳል።

በደላሎች እስራኤል ለመግባት ጉዞ ከጀመሩት ወገኖች መካከል ስንቶቹ በሲና በረሃ ሟምተው እንደቀሩ መረጃ የለም። ከሱዳን ምድር ወጥተው ግብጽ በመሻገር ሲና በረሃ እንደ ከብት ተበልተው የሚጣሉት ወገኖች ስቃይ ለሰሚው ግራ ነው። ወገኖቻችን ላይ የሚደርሰው አሰቃቂ መከራ ከቀን ቀን እየተባባሰ ነው። አሰቃቂ ዜናዎች መስማት ለየእለቱ የሚያስፈልገን መሰረታዊ ጉዳይ እስኪመስል ተለመዷል። ይህ አሳሳቢ ጉዳይ “እስከመቼ በዚህ ይቀጥላል” የሚለው የሁሉም ወገን “ዳር ቋሚዎች” ጥያቄ ነው፡፡

የ12 እና የ 1 ዓመት ከስምንት ወር ልጅ ያላቸው ወ/ሮ ትዕግስት ታፍነው በነበረበት ወቅት ባለቤታቸውን በስልክ እንዲያነጋግሩ ይደረጋሉ። ባለቤታቸውም ይሰቃያሉ። እግራቸውና እግራቸው መካከል ብረት ተደርጎባቸዋል። ይደበደባሉ። ይህ ሁሉ የሚደረገው ባለቤታቸው የተጠየቁትን ገንዘብ ባስቸኳይ እንዲከፍሉላቸው ለማስጨነቅ ነው። ባለቤታቸው እንደተናገሩት “ምንም አማራጭ የለኝም። የተጠየቀውን ገንዘብ ማግኘት አልችልም። ልጆቼ ወደፊት ሲጠይቁኝ ለምኜ አቃተኝ ለማለት እየለመንኩ ነው። ባለቤቴ ግን ምንም ማድረግ እንደማልችል ታውቃለች፤ ባይሳካልኝና ነጻ ባላወጣት አትቀየመኝም… ” በማለት ለቪኦኤ መናገራቸው ይታወሳል።

የ12 ዓመቷ ልጃቸው ሱፊ “እኛንም እንዳይወስዱን ስለምንፈራ ከቤት አንወጣም” በማለት  ከቪኦኤ ለቀረበላት ጥያቄ ልብ የሚነካ shagrabመልስ ሰጥታ ነበር፡፡ “እናቴን አፈኗት” ያለችው ህጻን የበርካታዎችን ልብ እረፍት ነስታ ነበር። ወ/ሮ ሰብለ “እንደዚህ አይነት አሳዛኝ ሲቃ የተሞላበት ጉዳይ እየሰማን በውጪ ያለን ወገኖች እንዴት 30 ሺህ ዶላር (በወቅቱ የተጠየቀው) ማዋጣት አቃተን” ሲሉ በመገረም ጠይቀው ነበር። ወ/ሮ ትዕግስት ገብሬ ቢተርፉ ለሌሎች በማስተማር ተመሳሳይ ችግር በሌሎች ወገኖቻችን ላይ እንዳይደርስ የማድረግ ስራ ይሰራል የሚል እምነት እንዳላቸው ወ/ሮ ሰብለ መናገራቸው የሚታወስ ነው።

ወ/ሮ ትዕግስት ከካይሮ ወደ ነበሩበት ሰፊ የስደተኞች ካምፕ ሸገራብ ይመለሳሉ። መቼ እንደ ሆነ ባይገለጽም ከታፈኑበት ምድር፣ በስደት ከሚኖሩበት ሸገራብ ቤተሰቦቻቸውን ተቀላቅለው ኑሮን ይቀጥላሉ ወይስ … ? (Photo: BBC)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule