• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሕይወት ዋጋ – “አጥንታቸውን እሾህ ያርገው”

March 16, 2017 04:47 am by Editor 4 Comments

በ2009 ዓ.ም. ቆሼ የሚባል ሰፈር ወይም መንደር ተፈጠረ፤ ቆሼ ማለት ቆሻሻን ማቆላመጫ ነው፤ ቆሻሽዬ ማለት ነው፤ ቆሼ የቆሻሻ ተራራ ነው፤ በዚያ የቆሻሻ ተራራ ዙሪያ መሄጃ የሌላቸው ሰፈሩበት፤ ጥንት ሴትዮዋ እንዳለችው፡-

እሾህ ብቻ ሆነ እግሬን ብዳብሰው
እንዴት መራመጃ መሄጃ ያጣል ሰው!

ሴትዮዋ ይህንን ያንጎራጎረችው ከብዙ ትውልዶች በፊት ነው፤ ጉልበተኞች የኢትዮጵያን ሰዓት ሰንገው ስለያዙት አይነቀነቅም! ባለህበት ሂድ! ነው፤ ዛሬም መሄጃ የለም፤ ቆሻሻንም የሙጢኝ ቢሉ ማምለጥ አይቻልም፡፡

እነዚህ አንድ መቶ አሥራ ሦስት ሟቾች በርግጥ ሰዎች ናቸው? በርግጥ ኢትዮጵያን ናቸው? የምናገረው ጠፍቶኛልና ጥያቄዎች ብቻ ልጠይቅ፡– ቤታቸውን ጉልበተኞች አፍርሰውባቸው፣ መሬታቸውን ሰማይ-ጠቀስ ወይም መንገድ ለመሥራት መሬታቸውን ወስደውባቸው የሚደርሱበት አጥተው፣ ባዶ ቦታ ፈልገው የፕላስቲክ መጠለያቸውን እየሠሩ ግፍን አሜን ብለው በሰላም ተቀብለው ኑሮ ካሉት መቃብር ይሞቃል እያሉ ቀኖችን ሲቆጥሩ ቆሻሻ መጣያው ደባል የሆነባቸው መቼ ነው? ወይስ ቆሻሻ መጣያው ቀድሞ እነሱ ደባል ሆነውት ነው? ጥያቄው ማን ቀደመ ሳይሆን ቆሻሻውና መጠለያ ፈላጊዎቹ አብረው አንዲኖሩ ፈቃድ የሰጣቸው ማን ነው የሚል ነው? የመጠለያ ፈላጊዎቹን ቤት ያፈረሰውና የቆሻሻውን ተራራ የሚክበው ጉልበተኛ ወይም ጉልበተኞች የተለያዩ ናቸው? ወይስ አንድ ነው? አንድ ከሆነ እውር-ደንቆሮ ሳይሆን አይቀርም፤ በማን-አለብኝነት ልባቸው ያበጠ ግዴለሾች ሳይሆኑ አይቀርም፡፡

አንድ መቶ አሥራ ሦስቱና ሌሎቹም ዜጎች ቢሆኑ፣ ማለት የአገሩን ባለቤትነት ከጉልበተኞች ጋር በእኩልነት የሚጋሩ ቢሆኑ፣ ሌሎች ዜጎች እነዚህ በቆሻሻ የተበሉት ወገኖቻቸው መሆናቸውን ቢገነዘቡ ቆሻሻና ዜግነት እንደተደባለቁ ማወቃቸው ይቀራል? ዋናው ችግራችንስ ይኸው ሳይሆን ይቀራል?

የሞቱትን ነፍሳቸውን ይማር ማለቱ አጉል ወግ ነው፤ አጥንታቸውን እሾህ ያርገው ማለቱ ሳይሻል አይቀርም!

(ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም)

(ምንጭ: Mesfin Wolde-Mariam Blog)

መጋቢት 2009

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. dergu temelese says

    March 22, 2017 03:31 pm at 3:31 pm

    ለወዝቶ አደሮች
    ከአመዳሞች
    ይብላኝ ለእናንተ ምርጥ ለምትበሉት፣
    ይብላኝ ለእናንተ ውስኪ ለምትቀዱት፣
    በአምስት አስራ እንድ በቁምሳ ስሌት፣
    እኛማ እያለቅን በርሀብ እርዛት፣
    በህይወት ከመኖር ይሻለናል ሞት፡፡
    ቁርስ ለንደን በልታችሁ ምሳችሁ ናይሮቢ፣
    እራት አዲስ- አባ በሼራተን ግቢ፣
    ዓለምን ስትቀጩ ብርን ስትገድቡ፣
    ለእኛ ጥፋት እንጂ ልማት አታስቡ፡፡
    ወስኪ ጠጥታችሁ በቀል ስታገሱ፣
    የድሀውን ድርሻ ስታግበሰብሱ፣
    ሞትን ስትሸሹ ምስኪኑን ስትገድሉ፣
    ያጣ ወንድማችሁን በጥይት ስትቆሉ፣
    የህግ እስረኛውን በእሳት ስትቀቅሉ፣
    ዝም ብሎ ሲያይ አይኖር ፈጣሪ ሀያሉ፣
    የዘራችሀትን እናንተም ታጭዳላችሁ፣
    አምላክ ዕድሜ ሰጥቶን ለማየት ያብቃችሁ፡፡
    በአቅላችሁ ሆናችሁ በደሉን አስታውሱ፣
    ድሀ ከመረረው አይሳሳም ለነፍሱ፣
    ምኑ ሊቀርበት የምድሩ ህይወት፣
    ተቆራምዶ አይኖርም ለእናንተ መውዛት፡፡

    Reply
  2. Mulugeta Andargie says

    March 23, 2017 03:57 am at 3:57 am

    Prof.Mesfin W/Marian!!! Don’t blame the government!!! They were not pushed to do so!!! They went to the garbage areas!!! Garbage is garbage!!! They went to scavenge garbage!!! To sale garbage!!! It is thrown as a garbage!!! They collect garbage??? They are koshashas!!! Koshasha took them!!! They burried in Koshasha!!!

    Reply
    • Editor says

      March 23, 2017 04:48 am at 4:48 am

      Mulugeta Andargie

      ማንነትህ እንዲታወቅ ነው “አስተያየት” ብለህ የጻፍከውን ያወጣንልህ። ራስህ በጻፍከው አስተያየት (comment) “ቆሻሻ” ማን እንደሆነ ያውም ደግሞ እጅግ የከፋውና መድኃኒቱ አስቸጋሪ የሆነው የዓዕምሮ “ቆሻሻ”ነት ባለቤት ማን እንደሆነ በሰጠኸው አስተያየት ስለመሰከርህ ይህ አደባባይ ወጥቶ መታወቅ ያስፈልገዋልና አትመነዋል። ብዙ ጊዜ ለአስተያየቶች ምላሽ አንሰጥም። ይህንን ግን አንተ ቆሻሻ ያልካቸው ሟቾች “አጥንታቸው እሾህ” ሆኖ ስለሚወጋን ማለፍ አቻልንም። እንዲሁም ስለራሱ መሟገት የማይችልና በህይወት የሌለን ሰው እንዲህ ባለ ቃል ከመናገር ያለፈ ቆሻሻነት የለም።

      የጎልጉል አርታኢ

      Reply
  3. dergu temelese says

    March 30, 2017 02:23 pm at 2:23 pm

    የወቅቱ ኢትዮጵዊ ትውልድ የህይወት አማራጮች
    ብሔራዊ ስሜት የነበረው የኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማርያም መንግሥት ቀይ ባህርን የዓረብ ባህር ለማድረግ እና ኤርትራንም ከእናት አገሯ ለመገንጠል ሻዕብያ እና ወያኔ በአረብ ፔትሮ ዶላር ሰክረው አገራቸውን ለመሸጥ እና ለማፍረስ እየሰሩ ነው፤ ሻዕብያ እና ወያኔ ከእረኛና ዘበኛ እስከ ምሁር በዘር ተደራጅተው ኢትዮጵያን ለማጥፋት ሲሰሩ ቁጭ ብለን መመልከት የለብንም፤ አብዮታዊት እናት ሀገር ወይም ሞት ብለው ለአሥራ ሰባት ዓመታት ሀቀኛ ኢትዮጵያውያንን አስተባብረው ተዋግተዋል፤ በርካታ ጀግኖችም ቀይ ባህር ላይ ደማቸውን አፍሰዋል፡፡ ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማርያም ምንም እንኳ በመጨረሻ ሞትን ፈርተው እንደ ሸሹ ቢነገርላቸውም ያሉትም አልቀረ ዛሬ ቀይ ባህር ወደ ዓረብ ባህርነት ስለመቀየሩ የሳውዲ ዓረቢያ፤ ኳታር እና ዐረብ ኤምሬትስ በአሰብ ወደብ እና በሶማሊያ መስፈር እንዲሁም ታሪካዊ ጠላታችን ቱርክ በአፍሪካ ታላቅ የሆነውን ጦር ሰፈር በሶማሊያ ለመገንባት ጫፍ ላይ መድረሷ ትልቅ ምስክሮች ናቸው፡፡
    ስልጣናቸውን ለሻዕብያ እና ወያኔ አምበሎች አስረክበውና ለሀገሪቱ አንድነት የታገሉትን ኢትዮጵውንን አመስግነው ወደ ሙጋቤ የተጠጉት የቀድሞው መሪ ከተናገሩት የቀረ ነገር ያለ አይመስልም፡፡ ሻዕብያ እና ወያኔ ባላቸው ስምምነት መሠረት ኤርትራ ስትገነጠል ኢትዮጵያን የሚበታትን ህገ መንግሥት (አንቀጽ 39) በወያኔ ተቀርጾና ዝርዝር አፈጻጸሙ ተቀምሮ ላለፉት 26 ዓመታት የትግራይ ኢኮኖሚ እስኪገነባና ታላቋ ዓባይ ትግራይ እስክትመሰረት እንዲሁም ቀሪዋ ኢትዮጵያ በጎሳ እስክትበታተን ድረስ ጥቂት ዓመታትን መጠበቅ ሊኖርብን ይችላል፡፡ ኤርትራ የምትባል ሉዓላዊት አገር ትኖራለች ኢትዮጵያ የምትባል ሉዓላዊት አገር ግን አትኖርም በማለት ኢሳያስ አፈወርቂ የተናገሩትንም ለማየት የቀረን ጊዜ በጥቂት ዓመታት የሚቆጠር ነው፡፡
    ለዘህ ማስረጃው የኦሮሚያን እና አማራን ክልል ከሱዳን የሚያዋስኑትን ቦታዎች ወደ ቤኒሻንጉል ጉምዝ እና ወደ ትግራይ በማካለል ጋምቤላን፣ የዓባይ ግድብ ያለበትን ቦታ ጨምሮ ቤኒሻንጉል ጉምዝን፣ ወልቃይት እና ሁመራን እንዲሁም የአፋርን እና የአሰብ ወደብን በማጠቃለል 100 ሺ ካሬ ኪሎሜትር ስፋት ያላት ታላቋ ትግራይ እንደምትመሠረት ህወሀት ያወጣው ካርታ ይፋ መሆን እና ራስ ዳሸን እና ዋልያ ትግራይ ውስጥ ይገኛሉ በማለት በትግራይ ትምህርት ቤቶች መማሪያ መጻህፍት ከአሥር ዓመት በላይ ሲሰጥ የቆየው ትምህርት በመጨረሻም ትምህርት ሚኒስትር በኢቢሲ ይቅርታ የጠየቀበት በትግራይ ትምህርት ቢሮ ተፈጸመ የተባለው ስህተት ምስክሮች ናቸው፡፡
    ዛሬ ትግራይ በመሠረተ ልማት፣ በጤና፣ በትምህርት፣ በኢንዱስትሪ እና በቢዝነስ ከኢትዮጵያ ግንባር ቀደም መሆኗን በመስማት ሳይሆን አይቶ ማረጋገጥ ይቻላል፡፡ ትግራይ ውስጥ ያልተገነባ ፋብሪካ የለም፡፡ ወጣቱ ትግራይን ለመገንባት የሚያስችለውን ገንዘብ እንዲያመጣ በመላው ኢትዮጵያ ተሰማርቷል፡፡ ትግራይ ውስጥ ያሉ አዛውንት እና መከላከያ ሠራዊት ብቻ ናቸው፡፡ ኤፈርት የተባለው የህወሀት የኢኮኖሚ ድርጅት ሀብት በአፍሪካ ተወዳዳሪ እንደሌለው እንደ ታቦት የሚታዩት ታጋይ አቦይ ስብሀት በአሜሪካ ድምጽ ቀርበው መስክረዋል፡፡ አሁን ያለማጋነን በኢትዮጵያ የትግራይ ሀብት ድርሻ ከ50 ፐርሰንት በላይ ነው ምንም እንኳ ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማርያም ከትግራይ የምናገኘው ገቢ ለጠመኔ መግዣም አይበቃም ብለው የነበረ ቢሆንም፡፡ በእርግጥ የኤፍርት ሀብት ምንጭ ኢትዮጵያ ናት ትግራይ አይደለችም፡፡
    አሁን ሀገሬ ወደ ማይቀረው መበታተን እያመራች ነው፡፡ ምናልባት ፈጣሪ በረቂቅ ስልጣኑ ካልታደጋት በስተቀር፡፡ እርግጥ ነው ኢትዮጵዊ የሆነ ወገን አሁንም አልሞት ባይ ተጋዳይ ሆኖ ከወያኔ እና ሻዕብያ ጋር እየተዋጋ እና ከአገሬ በፊት እኔ ልሙት ብሎ እየሞተ ነው፡፡ ክፋቱ ትግሉ የሚደረገው የኢትዮጵያን ሀብት ሙሉ በሙሉ ከተቆጣጠረው እና ዙሪያውን አይዞህ የሚል የአረብ፣ የሲ አይ ኤ የእንግሊዝ የስላለ ሃይል ( ኤም ኤ 6 ) ድጋፍ ካለው ወያኔ ውስጥ ተከቦ መሆኑ ውስብስብ አደገኛና ተስፋ አስቆራጭ ቢሆንም፡፡ አሁን አትዮጵያን ለማዳን የትግል ስልቱ እጅግ ረቂቅ እና በመንፈስ የሚመራ ሊሆን ይገባል፡፡ ወያኔ ካለው ሰፊ ሀብት በተጨማሪ የምስጢር ማህበራት (ሰይጣን አምላኪዎች) የሆኑ እነ ቢል ጌትስ፣ ጆርጅ ደብሊው ቡሽ እና አንጌላ ሜርክልን የመሳሰሉ ይረዱታል፡፡ እነዚህ ማህበራት ደግሞ ኢትዮጵያን ማዕከል አድርገው ዓለም አቀፋዊ የግጭት ዕቅድ እንዳላቸው በርካታ መረጃዎች አሉ፡፡
    በመጨረሻ ሊያስማማን የሚገባ ነገር ወቅቱ በፈጠረልን ሁለት ኢትዮጵዊ የትውልድ አማራጭ ዕድሎች ውስጥ ያለን መሆኑን ነው፡፡ አንድም የወያኔ እና ተባባሪዎቹ የሰይጣን ማህበራት ለሀገራችን የሸረቡትን ጥፋት በጸሎት፣ በጀግንነት እና በመሰዋትነት መመከት አልያም ለሰይጣን ማህበራት ዳረጎት እና ወያኔ አገልጋይ በመሆን ለሆድ ብቻ መኖር ነው፡፡ እግዚአብሔር በጸሎት፣ በጀግንነት እና በመሰዋትነት አምነን የምንኖር ያድርገን፡፡

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule