• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሌባዬ. . .

September 28, 2012 06:15 am by Editor 4 Comments

ሌባዬ. . .
ድምጹ ሳይሰማ ኮቴውን አጠፍቶ
በጠራራ ፀሐይ የደጄን በር ከፍቶ
መዝለቅ የጀመረው ክርችም በሬን ከፍቶ
ምን ሊዘርፈኝ ይሆን በምኔ ጎምጅቶ?

በማለት ኖላዊት ሽመልስ ስትጠይቅ የሚከተሉት መልሶች ተሰጥተዋታል፡፡
(ምልልሱን ያገኘነው ከፌስቡከ ሲሆን እርስዎም የሃሳብ በመስጫውን በመጠቀም ምላሽዎን እንዲሰጡ እንጋብዝዎታለን፡፡)
*************************************************************************************
ጠንቀቅ
አለሽ ንብረት አለሽ
አንቺዬ ሃብት አለሽ
ገንዘብ የማይገዛው
ለራስሽ ያልታየሽ
እጅግ የበለጠ
ከወርቅ፤ አልማዝ፤ ከእንቁ
አድፍጦ ሊዘርፍሽ
ያመጣው ከሩቁ
እመኚኝ ሃብት አለሽ
ዘብ የሚያስፈልገው
ብቻ ችላ ብለሽ እንዳታሰርቂው፡፡
(ብሌን ከበደ)
***************************************************************************************
በጠራራው ፀሀይ ሊዘርፍሽ የመጣ
ምን ዓይነት ደፋር ነው ምን ዓይነት ፈጣጣ!
በይ ጠንቀቅ ብለሽ ልብሶችሽን ሳይሆን ልብሽን ጠብቂ
ወርቁም ጌጡም ያለው እዚያው ነው እወቂ
እኔ ነግሬአለሁ ኋላ ተጠንቀቂ!
(ሁዳድ ንጉሤ)
**************************************************************************************
የተረፈችውን ስንቴ ተቆንጥራ
እንዳታልቅ ስሰስት ስተባ ስፈራ
ልቡን አደንድኖ ለልቤ ሳይራራ
ሊዘርፍ ይሄ ደፋር መጣ በጠራራ
(ቡቲካ ሽመልስ)
**************************************************************************************
ምን አይነት ደፋር ነው
shame እንኳን የሌለው
ሌባን ሌባ መስረቁ
ነበረ የሱስ ድፍረት
ይሄን ጠንቅቆ አለማወቁ
ቅኔ ምትደረድሪ
እንደሆንሽ ዘራፊ
ይህን አላውቀ የሌባ ጀማሪ
ሊዘርፍሽ የመጣው
እልም ያልሽ ዘራፊ
መሆንሽን አረ ማን ይንገረው?
(ኤልሳ ተገኔ)
**************************************************************************************
ቶማስ ለማ ለቡቲካ ሲመልስ፡-

ባጉል ቀን ተለክፎ
አካላቱ ዝሎ ፣ ሰዉነቱ ሰንፎ
የጣለዉን ዕቃ
ሊፈልግ ቢመጣ
አወይ “ያንች ነገር” ሌባ አስባለው በቃ
************************
አበባሽን ይዘሽ ፣ በቀን ስትዞሪ
ቢመጣ በቀፎሽ ፣ ንብ ሆኖ ማር ሰሪ
እንጀራ ጋጋሪ
ሌባ ማለት ትተሽ ፣ ጓዳዉን መርምሪ
በጎድኑ ግቢ ፣ በክፍተቱ ቅሪ
በቀን የሚገኝ ነው ፣ ፍቅር እዉነትን አብሪ
(ዘገብረየሱስ መስከረም 2004)

(ምልልሱን ያገኘነው ከፌስቡከ ሲሆን እርስዎም የሃሳብ በመስጫውን በመጠቀም ምላሽዎን እንዲሰጡ እንጋብዝዎታለን፤ ታዲያ በግጥም መሆኑን አይዘንጉ፡፡)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Tsinat says

    September 28, 2012 08:25 pm at 8:25 pm

    እሺ እንዲህ እንበል እሱማ ተሳስቶል
    ንብረት ያለሽ መስሎት ሊዘርፍሽ ከጅሎል
    እጅግ የሚገርመዉ ያንቺ መደንገጥ ነዉ
    ንብረት እንደሌለሽ ልብሽ እያወቀዉ

    Reply
  2. Gedion Adenew says

    September 28, 2012 09:57 pm at 9:57 pm

    Anchim minim yelesh-Lesum kentu lifat
    Berishin kerchimesh-Lik ende balehabt
    Layagegn layzerfish- Kenu alefebet!!!

    አንቺም ምንም የለሽ – ለሱም ከንቱ ልፋት
    በርሽን ከርችመሽ – ልክ እንደባለሃብት
    ላያገኝ ላይዘርፍሽ – ቀኑ አለፈበት፡፡

    Reply
  3. Tsinat says

    September 29, 2012 02:17 am at 2:17 am

    የቆለፍኩትን በር ይበርግደዉ ይግባ
    ለማግኘት ከቻለ አንዳች የሚረባ
    እስኪ ቆዩኝማ ምን ይሁን ብይ ነው በሬን የከረቸምኩ
    አልማዝ እንደሸሸግኩ ወርቁን እንደደበቅኩ?
    የቤቱ ባዶነት ልቤ እያወቀዉ ለካስ በከንቱ ነዉ በቴን የከረቸምኩ

    Reply
  4. Abe, says

    October 5, 2012 07:55 pm at 7:55 pm

    ሥረቃት! ስረቃት!
    በጎን የምትወጂው
    እስከሆነ ድረስ
    ቢጎተት ?!
    ቢመለስ ?!
    ያሻውን ቢቆምጥ?!
    ከሌባሽ ሌብነት
    ተማርከሽለታል
    ተሰርቀሽለታል
    በጠፍ በጨረቃ
    “ይዘኸኝ ሂድ” አይነት
    አቆላምጠሸ ጠርተሸ
    ሌባሽ ከሆነልሽ
    አንቺን የሚከፋሽ
    ባይሰርቅሽ እንደሆን ልቤ ጠርጥሮታል
    ሂድ!? በሚለው ቃልሽ ናልኝ ብሰሺዋል
    ሌባዋ ሂድላት
    ስረቃት! ስረቃት!
    (አበበ አዲስ)

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule