• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሌባዬ. . .

September 28, 2012 06:15 am by Editor 4 Comments

ሌባዬ. . .
ድምጹ ሳይሰማ ኮቴውን አጠፍቶ
በጠራራ ፀሐይ የደጄን በር ከፍቶ
መዝለቅ የጀመረው ክርችም በሬን ከፍቶ
ምን ሊዘርፈኝ ይሆን በምኔ ጎምጅቶ?

በማለት ኖላዊት ሽመልስ ስትጠይቅ የሚከተሉት መልሶች ተሰጥተዋታል፡፡
(ምልልሱን ያገኘነው ከፌስቡከ ሲሆን እርስዎም የሃሳብ በመስጫውን በመጠቀም ምላሽዎን እንዲሰጡ እንጋብዝዎታለን፡፡)
*************************************************************************************
ጠንቀቅ
አለሽ ንብረት አለሽ
አንቺዬ ሃብት አለሽ
ገንዘብ የማይገዛው
ለራስሽ ያልታየሽ
እጅግ የበለጠ
ከወርቅ፤ አልማዝ፤ ከእንቁ
አድፍጦ ሊዘርፍሽ
ያመጣው ከሩቁ
እመኚኝ ሃብት አለሽ
ዘብ የሚያስፈልገው
ብቻ ችላ ብለሽ እንዳታሰርቂው፡፡
(ብሌን ከበደ)
***************************************************************************************
በጠራራው ፀሀይ ሊዘርፍሽ የመጣ
ምን ዓይነት ደፋር ነው ምን ዓይነት ፈጣጣ!
በይ ጠንቀቅ ብለሽ ልብሶችሽን ሳይሆን ልብሽን ጠብቂ
ወርቁም ጌጡም ያለው እዚያው ነው እወቂ
እኔ ነግሬአለሁ ኋላ ተጠንቀቂ!
(ሁዳድ ንጉሤ)
**************************************************************************************
የተረፈችውን ስንቴ ተቆንጥራ
እንዳታልቅ ስሰስት ስተባ ስፈራ
ልቡን አደንድኖ ለልቤ ሳይራራ
ሊዘርፍ ይሄ ደፋር መጣ በጠራራ
(ቡቲካ ሽመልስ)
**************************************************************************************
ምን አይነት ደፋር ነው
shame እንኳን የሌለው
ሌባን ሌባ መስረቁ
ነበረ የሱስ ድፍረት
ይሄን ጠንቅቆ አለማወቁ
ቅኔ ምትደረድሪ
እንደሆንሽ ዘራፊ
ይህን አላውቀ የሌባ ጀማሪ
ሊዘርፍሽ የመጣው
እልም ያልሽ ዘራፊ
መሆንሽን አረ ማን ይንገረው?
(ኤልሳ ተገኔ)
**************************************************************************************
ቶማስ ለማ ለቡቲካ ሲመልስ፡-

ባጉል ቀን ተለክፎ
አካላቱ ዝሎ ፣ ሰዉነቱ ሰንፎ
የጣለዉን ዕቃ
ሊፈልግ ቢመጣ
አወይ “ያንች ነገር” ሌባ አስባለው በቃ
************************
አበባሽን ይዘሽ ፣ በቀን ስትዞሪ
ቢመጣ በቀፎሽ ፣ ንብ ሆኖ ማር ሰሪ
እንጀራ ጋጋሪ
ሌባ ማለት ትተሽ ፣ ጓዳዉን መርምሪ
በጎድኑ ግቢ ፣ በክፍተቱ ቅሪ
በቀን የሚገኝ ነው ፣ ፍቅር እዉነትን አብሪ
(ዘገብረየሱስ መስከረም 2004)

(ምልልሱን ያገኘነው ከፌስቡከ ሲሆን እርስዎም የሃሳብ በመስጫውን በመጠቀም ምላሽዎን እንዲሰጡ እንጋብዝዎታለን፤ ታዲያ በግጥም መሆኑን አይዘንጉ፡፡)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Tsinat says

    September 28, 2012 08:25 pm at 8:25 pm

    እሺ እንዲህ እንበል እሱማ ተሳስቶል
    ንብረት ያለሽ መስሎት ሊዘርፍሽ ከጅሎል
    እጅግ የሚገርመዉ ያንቺ መደንገጥ ነዉ
    ንብረት እንደሌለሽ ልብሽ እያወቀዉ

    Reply
  2. Gedion Adenew says

    September 28, 2012 09:57 pm at 9:57 pm

    Anchim minim yelesh-Lesum kentu lifat
    Berishin kerchimesh-Lik ende balehabt
    Layagegn layzerfish- Kenu alefebet!!!

    አንቺም ምንም የለሽ – ለሱም ከንቱ ልፋት
    በርሽን ከርችመሽ – ልክ እንደባለሃብት
    ላያገኝ ላይዘርፍሽ – ቀኑ አለፈበት፡፡

    Reply
  3. Tsinat says

    September 29, 2012 02:17 am at 2:17 am

    የቆለፍኩትን በር ይበርግደዉ ይግባ
    ለማግኘት ከቻለ አንዳች የሚረባ
    እስኪ ቆዩኝማ ምን ይሁን ብይ ነው በሬን የከረቸምኩ
    አልማዝ እንደሸሸግኩ ወርቁን እንደደበቅኩ?
    የቤቱ ባዶነት ልቤ እያወቀዉ ለካስ በከንቱ ነዉ በቴን የከረቸምኩ

    Reply
  4. Abe, says

    October 5, 2012 07:55 pm at 7:55 pm

    ሥረቃት! ስረቃት!
    በጎን የምትወጂው
    እስከሆነ ድረስ
    ቢጎተት ?!
    ቢመለስ ?!
    ያሻውን ቢቆምጥ?!
    ከሌባሽ ሌብነት
    ተማርከሽለታል
    ተሰርቀሽለታል
    በጠፍ በጨረቃ
    “ይዘኸኝ ሂድ” አይነት
    አቆላምጠሸ ጠርተሸ
    ሌባሽ ከሆነልሽ
    አንቺን የሚከፋሽ
    ባይሰርቅሽ እንደሆን ልቤ ጠርጥሮታል
    ሂድ!? በሚለው ቃልሽ ናልኝ ብሰሺዋል
    ሌባዋ ሂድላት
    ስረቃት! ስረቃት!
    (አበበ አዲስ)

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule