• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የግብሩ አመጽ – የፍጻሜው ጦርነት

July 23, 2017 07:18 am by Editor Leave a Comment

የአስቸኳይ (የአፈና) ግዜ  አዋጁ ገና አልተነሳም። በአዲሱ የግብር ትመና ሳብያ ከዳር እስከዳር የተነሳው ሕዝባዊ አድማ እና አመጽ ግን አዋጁን ውድቅ ያደረገው ይመስላል። አንድ ስርዓት ራሱ ያወጣው ህግ በህዝብ ሲሻርበት – ያኔ ነው ያበቃለት!

ከቶውን “የአለምን  ኢኮኖሚ እየመራች ያለች ሃገር” የበጀት ሸክሟን ለምን በህዝብ ላይ መጣል እንዳለባት ግልጽ አልሆነም። እውነታው ከነዚህ ሁለት እይታዎች ውጭ አይሆንም።  ይነፋ የነበረው የእድገት ቀረርቶ እና ይነገር የነበር ሁለት ዲጅት እድገት ቁጥር ሁሉ ውሸት ነበር፣  ወይንም ደግሞ የሃገሪቱ ሃብት በጥቂቶች እየተዘረፈ ነው።

ጆሮን ያሰለቸው የ”እድገት እና ትራንስፎርሜሽኑ” ዘፈን ቀዝቀዝ ማለት ሲጀምር የ “ደብል ድጅቱ” የፈጠራ ተረት እንደ በረዶ እየነጻ መሄዱ አልቀረም። እድገቱ የህዝቡን  ህይወት አልለወጠም። ተጀምሮ ከሚቋረጥ ህንጻ እና መንገድ ውጭ ትራንስፎርሜሽኑም በተግባር አልታየም። ይልቁንም ተሸፍኖ የነበረው ችግር አሁን ፈጥጦ ወጥቶ በህዝብ ጫንቃ ላይ ጉብ ሊል ዳዳው፣ ገበሬውን መሬት በመንጠቅ፣ ነጋዴው ላይ ደግሞ ሚዛናዊ ባልሆነ የገቢ ግምት – ከፍተኛ ግብር በመጫን።   ምላሹንም እንደምናየው ነው።  አድማ፡ ህዝባዊ አመጽ፣… ተቃውሞ!

በዘንድሮው የበጀት አመት የህወሃት መንግስት 320 ቢሊዮን ብር ማጽደቁን አብስሮን ነበር።  ይህ በጀት የ100 ቢሊዮን ብር  (1/3ኛ) የበጀት ጉድልት ነበረበት። ይህ የ100 ቢሊዮን ብር የበጀት ጉድለት ከብድር እና እርዳታ ይሸፈናል ተብሎ  ነበር የተጠበቀው። የ11 በመቶው እድገት ተረት – ተረት  ውስጥ የእርዳታው እና የብድሩ መጠን ተገልጾ አያውቅም። ሃገሪቱ በደፈናው እያደገች ነው አሉን። በፈጣን እድገት የአለምን ኢኮኖሚ የምትመራ ሃገር ተባለ።  ፈረንጆቹም አመኑ።

እርዳታን  እንደ ስትራቴጂ የቀመሩት የህወሃት ጠበብቶች፣ ፈረንጆች ፊታቸውን ማዞር እንደማይሳናቸው እንኳን አላሰቡትም። በሶማሊያ ውስጥ የነሱን ቆሻሻ ጦርነት ስለተረከቡ ብቻ ጉዳዩን እንደ ይገባኛል መብት (for granted) አዩት። የሶማልያ ጉዳይ፣ የአልሻባብ ፖለቲካ ዲስኩር፣ የጸረ-ሽብር እንቶፈንቶ አሁን የለም። አሜሪካም ሆነች የአውሮፓ ህብረት ዜጎችን በአዋጅ እና በአስቸኳይ ግዜ አዋጅ አፍኖ የያዘው ስርዓት ጋር በረጅሙ እንደማይዘልቁ ግልጽ ነው። ታዲያ ከቻይናው የእድሜ-ልክ የእዳ ቁልል ውጭ የታሰበው የውጭ ገቢ ጠፋ። ማጠፍያው አጠረ። ለሰራዊቱና ለደህንነቱም ደሞዝ መከፈል አለበት።  …ቀሪው ገንዘብ ከግብር እና ከሃገር ውስጥ የሚሰበሰብ ገንዘብ ብቻ ነው።

እናም እዳው ሕዝብ  ላይ ተቆለለ። የቀን ገቢ በግምት እየታየ ተጫነ። በገቢና ወጪ ሳይሆን፣  በህዝብ ላይ በግምት ግብር ሲጫን በታሪክ የመጀመርያው ሳይሆን አይቀርም። አዲሱ የግብር ትመና በንግዱ ህብረተሰብድ ከባድ ቁጣ ቀስቅሷል። ከጫፍ እስከጫፍ የተነሳው የሥራ ማቆም አድማ የት ላይ እንደሚቆም አይታወቅም። በአስቸኳይ ግዜ በምትተዳደር ሃገር የተነሳው ይህ አድማ ቀድሞ የተጀመረው የመብት እና የነጻነት ትግል ቅጣይ ይመስላል። ቀድሞ የተነሳው የሕዝብ ጥያቄ ምላሽ አላገኘም።  የህወሃት የአፈና ሰንሰለትም እንደቀጠለ ነው። ዛሬ ነጋዴው ህብረተሰብ የሰለባው ባለሳምንት ይሁን እንጂ የኢትዮጵያ ሕዝብ መሰረታዊ ችግር ኢ-ፍትሃዊ የሆነ የግብር ፖሊሲ አይደለም። ችግሩ ስርዓቱ ራሱ ነው። ዛሬ የንግድ ቤቶች ቢዘጉ ሌላ የንግድ ቤቶችን የመክፈት አቅም ያላቸው የህወሃት ሰዎች በደስታ መፈንጠዛቸው አይቀርም። …አሜካላው ሳይነሳ መፍትሄ አይታሰብም።

ዋናው ነገር ወዲህ ነው። ግብር ለመክፈልም እኮ የህዝብ ውክልና ያለው ስርዓት መኖር ግድ ይላል። የሀዝቡን ይሁንታ ያላገኘ መንግስት፣ በሕዝብ ያልተመረጠ መንግሥት ግብር የማስከፈል መብት የለውም፣ ሕዝቡም ላልወከለው መንግስት ግብር ለመክፈል አይገደድም።

እ.ኤ.አ. በ1750ቹ እና 1760ቹ አስራ ሶስቱ የአሜሪካ ቅኝ ግዛቶች ይዘውት የተነሱት መፈክርን ያስተውሏል። “No Taxation Without Representation” ይላል። “ውክልና ከሌለ ግብር አይኖርም” እንደማለት ነው።  አሜሪካኖች በዚያ የነጻነት ትግላቸው ወቅት አቋማቸውን ለመግለጽ የተጠቀሙበት መሪ ቃል ነበር።  አመሪካውያኑ ይህንን መፈክር ይዘው በማመጽ የብሪትሽን ኤምፓየር እንዳናፈጡት የታሪክ ማህደር ያወሳናል።

ህወሃት የህዝብ ይሁንታም የለው፣ መረጃም የለው። ሃይለማርያም ደሳለኝ በብሄራዊ ቴሌቭዥን ለይ ወጥተው እንዲህ አሉ። ስራችንን የምንሰራው፣ ውሳኔም የምንወስነው መረጃ ሳንይዝ እንዲሁ በግምት ነው። “መረጃ የሚጠናከርበት ስርዓት የለም።” አሉ።  እኚህ ሰው አንዳንዴ አውቀውም ይሁን ሳያውቁ  እውነትን ይለቁልናል። ንግግራቸው እኝህ ሰው ነጻ ያለመሆናቸውን ይጠቁመናል።   ሃገሪቱ ነጻ መውጣት ካለባት በመጀመርያ ነጻነትን ማወጅ ያለበቸው እሳቸው ናቸው። እውነት ነው።  ህወሃት እየመራ ያለው በግምት እና በጥይት ነው።

የሃይለማርያም ንግግር አጉልቶ የሚያሳየን ነገር አለ። ስርዓቱ ችግር ፈጣሪ ብቻ ሳይሆን፣ ስርዓቱ ራሱ ችግር መሆኑን ግልጽ ያደርግልናል።

ትግራይ “ክልል” ፕሬዝዳንት እና የመቐሌ ከንቲባ ላይ ከሰሞኑ የተፈጠረው ሕዝባዊ ተቃውሞ የሚሰብቀን ነገር ይኖራል። ከሰሞኑ በመቀሌ ስታድዮም የገባው ህዝብ በዝግጅቱላይ በተገኙ የህወሓት አመራሮችን “ሌባ ሌባ ሌባ .. ሃሳዊ (ውሸታም) መሲህ ሲሉ ተደምጠዋል። እንግዲህ የትግራይ ህዝብ ራሱ ተወክያለው ያለውን አመራር “ሌባ ሌባ ” ካለ ምን ቀረ?… እንደኔ ግምት የቀረ የለም። ሃገር እየተመራች ያለችው መረጃ በሌላቸው፣ ራዕይ በሌላቸውና የህዝብ ይሁንታ ባላገኙ ሌቦች ነው።

ከትግራይ ውጭ ያለውም ሕዝብ እንዲህ ነው የሚለው። “ወያኔ ሌባ ነው! ለሌባ ግብር አንከፍልም!”

“ኢትዮጵያንና ህዝቧን በጉልበት አፍኖ ለያዘ ዘራፊ ቡድን አንገብርም!!” ብለዋል ጊንጪዎች። ይህ የግብር አመጽ የፍጻሜው ጦርነት ይሆን? እድሜ ከሰጠን እናየዋለን።

ለዛሬ በዚህ ላብቃ በመጪው ጽሁፌ ስለ “ኳስ እና ፖለቲካ” የምለው አለኝ።

ክንፉ አሰፋ


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule