• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ዉሃ በሌለበትና ቱሃን በበዛበት ጣቢያ እያንገላቱኝ ነው”

February 23, 2017 07:56 am by Editor Leave a Comment

  • ዳንኤል ሺበሺ ከወህኒ ያስተላለፈው መልእክት

ከቤተሰቡ በተገኘው መረጃ መሰረት ዳንኤል የተወለደው በደቡብ ኢትዮጵያ ነው፡፡ ያደገው እንደአብዛኛው ኢትዮጵያዊ በለምለሟ ቁጫ ወረዳ አረንጓዴ መስክ ሮጦና ተራራና አቀበት ወጥቶ ነው፡፡ ከልጅነቱ ጀምሮ ንቁ ነበርና ቤተሰቡ ወደ ትምህርት ቤት ሰደደው፡፡ ተማረ፡፡ እስከ ዩኒቨርስቲ በመዝለቅም ቀጠለ፡፡ ከዚያም ሳይማር ወዳስተማረው ህብረተሰብ በመመለስ ማገልገሉን ተያያዘው፡፡ ግና ትምህርት የአለማችንን ተጨባጭ ሁኔታ እንዲለይ አስችሎት ነበርና በሚሰራው ስራ ብቻ ሊረካ አልቻለም፡፡ ህዝቡ ላይ የማህበራዊ፤ ኢኮኖሚያዊና የማህበራዊ ፍትህ እጦት እንደሚያሰቃየው ተመለከተ፡፡

ወጣቱ ዳኒ በተደጋጋሚ እንደሚናገረው ‹‹ህዝቡ ላይ እየደረሰ ያለውን በደልና ግፍ ከንፈር በመምጠጥ ብቻ ማቆም እንደማይቻል አውቅ ነበር፡፡ እንደ አንድ ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ ምን ማድረግ እንዳለብኝ እጨነቅ ነበር፡፡ ወቅቱ ደግሞ ደርግ ወድቆ፣ ኢህአዴግ ስልጣን ይዞ የሚንደፋደፍበት ስለነበር ሁኔታዎች ወዴት ሊያመሩ እንደሚችሉ ለመገመት ሁሉ አይቻልም ነበር›› ይላል፡፡

ነገር ግን ‹‹ነፃ አውጭዎቹ›› ስልጣንና ሀብትን በሚለማመዱበት በዚያ ጊዜ መራራ ትግል ያካሄዱት በደርግ አገዛዝ መከራ የሚበላውን የኢትዮጵያ ህዝብ ነፃ ለማውጣት እንደሆነ በመስበካቸውና ከመንገድ ስለተቀበሉት ዴሞክራሲ በማውራታቸው ‹‹እስኪ እንያቸው!›› የሚል ስሜት መፈጠሩ አልቀረም፡፡ ይሄ ስሜትም ወጣቱ ዳንኤል ሺበሺ ላይ በማደሩ የኢህአዴግን ሁኔታ በአንክሮ ይከታተል እንደነበር ተናግሯል፡፡ በመቀጠልም ከታጋዮቹ ሌላ ጥሪ መጣለት ‹‹እናንተ ወጣቶች እኮ ዴሞክራሲያዊ ስርኣት ለመገንባት የምናደርገውን ትግል ብትደግፉን ይችን ሀገር መቀየር እንችላለን!›› የሚል ነበር፡፡

ዳንኤል ከዚህ በፊት በተለያዩ መድረኮች ይናገር እንደነበረው ‹‹ብታግዙን ጥሩ ነው›› የሚለውን ሀሳብ በወቅቱ ብዙ ወጣቶች በቀናነት በመውሰድ ‹‹ለሀገራችን መስራት ከቻልን ብናግዛቸው ጥሩ ነው›› በሚል ኢህአዴግን ተቀላቀሉ፡፡ ዳንኤል ሺበሺም በደኢህዴን በኩል የኢህአዴግ አባል ሆነ፡፡ አቶ ሃይለማሪያምን ጨምሮ ከአሁን አሳሪዎቹ ጋርም አብሮ ሰራ፡፡ የተባለው ዴሞክራሲ የማስፈን ነገር ከልብ አይደለምና ልዩነቶች እየተፈጠሩ መጡ፡፡ ዳንኤልና ሌሎች አንዳንድ ወጣቶች የምንላችሁን ብቻ ተቀበሉ፤ የምንላችሁን ብቻ ስሩ . . . የሚለው የህወሃት/ኢህአዴግ ትዕዛዝ መጀመሪያ ከተባሉት ጋር የሚጋጭ ነበርና የመርህ ጥያቄ ማንሳት ጀመሩ፡፡ የውስጥ ትግልም አደረጉ፡፡ ከኢህአዴግ ጋር ለመስራት ያደረገው ሙከራም ብዙ ርቀት ሳይሄድ በአጭሩ ተቀጨ፡፡ የስርዓቱን ውስጣዊ አፋኝ አሰራር ያየው ዳንኤልም በአደባባይ እንደማይጠቅም በመናገር በሰላማዊ መንገድ ለማስወገድ የሚደረገውን ትግል ተቀላቀለ፡፡

ዳንኤል ሺበሺ የኢዴፓ አባል የነበረ ሲሆን ቅንጅት ላይ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ካደረጉና እስካሁን ድረስ የሚያሰቃይ ድብደባ ከደረሰባቸው ወጣቶች አንዱ ነው፡፡ የአንድነት ፓርቲ መስራችና የደቡብ ቀጠና ኃላፊ በመሆን ከተመሰረተ ጀምሮ የሰራ ሲሆን በቅርቡ ደግሞ የድርጅት ጉዳይ ምክትል ኃላፊ በመሆን በትጋት የሚታገል የዴሞክራሲ አርበኛ ነው፡፡ ዳኒ ባለትዳርም ነው፡፡ የሚያምንበትን ፊት ለፊት የሚናገር፤ ደፋር ነገርግን ፈገግታ የማይለየው ዳኒ በትግል አጋሮቹ ዘንድ (ዳኒ ደቡብ) በመባል በቁልምጫ ይጠራል፡፡ ዳኒ ደቡብ በአጠቃላይ በኢትዮጵያ የሚፈፀሙ የሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብት ጥሰቶችን በማጋለጥ ይታወቃል፡፡ በቅርቡ ደግሞ የመብት ጥያቄ ባነሳው የቁጫ ህዝብ ላይ የተወሰደውን የጅምላ እስር በማውገዝ ያጋለጠና ይህንንም በተለያዩ ሚዲያዎች ይፋ ያደረገ እንዲሁም ለሚታገሉ ሁሉ መልካም አርአያ ሊሆን የሚችል ወጣት ነው፡፡

በዚህ አስከፊ ስርዓት ጥርስ የተነከሰበት ዳኒ ሐምሌ 1 ቀን 2006 ዓ.ም አገር አማን ብሎ ወደ ስራ ሲሄድ በፖሊሶች ተከቦ በካቴና ከታሰረ በኋላ ቤቱ ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት እስከ ምሽቱ 2፡00 ሰዓት ተፈትሾ ወደ ማሰቃያው ማዕከላዊ ተወስዷል፡፡ ከሃያ ወር ግፍና እንግልት በኋላ ዳንኤል ሺበሺ ከወህኒ ይለቀቃል። አገዛዙ በርሱ ላይ ላቀረበው የፈጠራ የሽብርተኝነት ክስ ማስረጃ ማቅረብ ባለመቻሉ።

ብዙም አልቆየም የአገዛዙ ኮማንድ ፖስት እንደገና ወደ ወህኒ አወረደው። ዳኒ በአሁኑ ወቅት ባላጠፋው ጥፋት ፣ ባልሰራው ወንጀል፣ እንደገና አገሩን እና ሕዝቡን በዉደዱ፣ ኢትዮጵያን በመዉደዱ ከሌሎች በመቶ ሺሆች ከሚቆጠሩ ኢትዮጵያዉያን ጋር በወህኒ እየማቀቀ ነው።

አገዛዙ ዳንኤል ወደ ወህኒ መዉሰድ ብቻ ሳይሆን፣ በወህኒ አንድ እስረኛ ማግኘት የሚገባውን መሰረታዊ መብት ተነፍጎ፣ ከፍተኛ የዉሃ እጥረት ያለበት፣ ቱሃን የበዛበት እሥር ቤት ነው እየተሰቃየ ያለው።

እነ ዳንኤል ሺበሺን በማሰር ግን ህጋዊና ሰላማዊ ትግሉን ማስቆም አይቻልም፡፡ ዛሬ ትግሉ ብዙ አንዷለሞችን፤ ብዙ አናኒያ ሶሪዎችን፤ ብዙ ኤሊያሶች ፣ ብዙ እዮኤሎችን፣ ብዙ ዶ/ር መረራ ጉዲናዎችም፣ ብዙ ዳንኤሎችን፣ ብዙ አስቴሮችን፣ ብዙ ንግስት ይርጋዎችን፣ ብዙ ኮሎኔል ደመቀ ዘዉዴዎችን ያፈራና ትግሉን በቁርጠኝነት የሚቀጥል ነው፡፡ እንደሚባለው ሊነጋ ሲል መጨለሙ አይቀርም፡፡

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

የሚሊዮኖች ድምጽ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule