• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ዉሃ በሌለበትና ቱሃን በበዛበት ጣቢያ እያንገላቱኝ ነው”

February 23, 2017 07:56 am by Editor Leave a Comment

  • ዳንኤል ሺበሺ ከወህኒ ያስተላለፈው መልእክት

ከቤተሰቡ በተገኘው መረጃ መሰረት ዳንኤል የተወለደው በደቡብ ኢትዮጵያ ነው፡፡ ያደገው እንደአብዛኛው ኢትዮጵያዊ በለምለሟ ቁጫ ወረዳ አረንጓዴ መስክ ሮጦና ተራራና አቀበት ወጥቶ ነው፡፡ ከልጅነቱ ጀምሮ ንቁ ነበርና ቤተሰቡ ወደ ትምህርት ቤት ሰደደው፡፡ ተማረ፡፡ እስከ ዩኒቨርስቲ በመዝለቅም ቀጠለ፡፡ ከዚያም ሳይማር ወዳስተማረው ህብረተሰብ በመመለስ ማገልገሉን ተያያዘው፡፡ ግና ትምህርት የአለማችንን ተጨባጭ ሁኔታ እንዲለይ አስችሎት ነበርና በሚሰራው ስራ ብቻ ሊረካ አልቻለም፡፡ ህዝቡ ላይ የማህበራዊ፤ ኢኮኖሚያዊና የማህበራዊ ፍትህ እጦት እንደሚያሰቃየው ተመለከተ፡፡

ወጣቱ ዳኒ በተደጋጋሚ እንደሚናገረው ‹‹ህዝቡ ላይ እየደረሰ ያለውን በደልና ግፍ ከንፈር በመምጠጥ ብቻ ማቆም እንደማይቻል አውቅ ነበር፡፡ እንደ አንድ ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ ምን ማድረግ እንዳለብኝ እጨነቅ ነበር፡፡ ወቅቱ ደግሞ ደርግ ወድቆ፣ ኢህአዴግ ስልጣን ይዞ የሚንደፋደፍበት ስለነበር ሁኔታዎች ወዴት ሊያመሩ እንደሚችሉ ለመገመት ሁሉ አይቻልም ነበር›› ይላል፡፡

ነገር ግን ‹‹ነፃ አውጭዎቹ›› ስልጣንና ሀብትን በሚለማመዱበት በዚያ ጊዜ መራራ ትግል ያካሄዱት በደርግ አገዛዝ መከራ የሚበላውን የኢትዮጵያ ህዝብ ነፃ ለማውጣት እንደሆነ በመስበካቸውና ከመንገድ ስለተቀበሉት ዴሞክራሲ በማውራታቸው ‹‹እስኪ እንያቸው!›› የሚል ስሜት መፈጠሩ አልቀረም፡፡ ይሄ ስሜትም ወጣቱ ዳንኤል ሺበሺ ላይ በማደሩ የኢህአዴግን ሁኔታ በአንክሮ ይከታተል እንደነበር ተናግሯል፡፡ በመቀጠልም ከታጋዮቹ ሌላ ጥሪ መጣለት ‹‹እናንተ ወጣቶች እኮ ዴሞክራሲያዊ ስርኣት ለመገንባት የምናደርገውን ትግል ብትደግፉን ይችን ሀገር መቀየር እንችላለን!›› የሚል ነበር፡፡

ዳንኤል ከዚህ በፊት በተለያዩ መድረኮች ይናገር እንደነበረው ‹‹ብታግዙን ጥሩ ነው›› የሚለውን ሀሳብ በወቅቱ ብዙ ወጣቶች በቀናነት በመውሰድ ‹‹ለሀገራችን መስራት ከቻልን ብናግዛቸው ጥሩ ነው›› በሚል ኢህአዴግን ተቀላቀሉ፡፡ ዳንኤል ሺበሺም በደኢህዴን በኩል የኢህአዴግ አባል ሆነ፡፡ አቶ ሃይለማሪያምን ጨምሮ ከአሁን አሳሪዎቹ ጋርም አብሮ ሰራ፡፡ የተባለው ዴሞክራሲ የማስፈን ነገር ከልብ አይደለምና ልዩነቶች እየተፈጠሩ መጡ፡፡ ዳንኤልና ሌሎች አንዳንድ ወጣቶች የምንላችሁን ብቻ ተቀበሉ፤ የምንላችሁን ብቻ ስሩ . . . የሚለው የህወሃት/ኢህአዴግ ትዕዛዝ መጀመሪያ ከተባሉት ጋር የሚጋጭ ነበርና የመርህ ጥያቄ ማንሳት ጀመሩ፡፡ የውስጥ ትግልም አደረጉ፡፡ ከኢህአዴግ ጋር ለመስራት ያደረገው ሙከራም ብዙ ርቀት ሳይሄድ በአጭሩ ተቀጨ፡፡ የስርዓቱን ውስጣዊ አፋኝ አሰራር ያየው ዳንኤልም በአደባባይ እንደማይጠቅም በመናገር በሰላማዊ መንገድ ለማስወገድ የሚደረገውን ትግል ተቀላቀለ፡፡

ዳንኤል ሺበሺ የኢዴፓ አባል የነበረ ሲሆን ቅንጅት ላይ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ካደረጉና እስካሁን ድረስ የሚያሰቃይ ድብደባ ከደረሰባቸው ወጣቶች አንዱ ነው፡፡ የአንድነት ፓርቲ መስራችና የደቡብ ቀጠና ኃላፊ በመሆን ከተመሰረተ ጀምሮ የሰራ ሲሆን በቅርቡ ደግሞ የድርጅት ጉዳይ ምክትል ኃላፊ በመሆን በትጋት የሚታገል የዴሞክራሲ አርበኛ ነው፡፡ ዳኒ ባለትዳርም ነው፡፡ የሚያምንበትን ፊት ለፊት የሚናገር፤ ደፋር ነገርግን ፈገግታ የማይለየው ዳኒ በትግል አጋሮቹ ዘንድ (ዳኒ ደቡብ) በመባል በቁልምጫ ይጠራል፡፡ ዳኒ ደቡብ በአጠቃላይ በኢትዮጵያ የሚፈፀሙ የሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብት ጥሰቶችን በማጋለጥ ይታወቃል፡፡ በቅርቡ ደግሞ የመብት ጥያቄ ባነሳው የቁጫ ህዝብ ላይ የተወሰደውን የጅምላ እስር በማውገዝ ያጋለጠና ይህንንም በተለያዩ ሚዲያዎች ይፋ ያደረገ እንዲሁም ለሚታገሉ ሁሉ መልካም አርአያ ሊሆን የሚችል ወጣት ነው፡፡

በዚህ አስከፊ ስርዓት ጥርስ የተነከሰበት ዳኒ ሐምሌ 1 ቀን 2006 ዓ.ም አገር አማን ብሎ ወደ ስራ ሲሄድ በፖሊሶች ተከቦ በካቴና ከታሰረ በኋላ ቤቱ ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት እስከ ምሽቱ 2፡00 ሰዓት ተፈትሾ ወደ ማሰቃያው ማዕከላዊ ተወስዷል፡፡ ከሃያ ወር ግፍና እንግልት በኋላ ዳንኤል ሺበሺ ከወህኒ ይለቀቃል። አገዛዙ በርሱ ላይ ላቀረበው የፈጠራ የሽብርተኝነት ክስ ማስረጃ ማቅረብ ባለመቻሉ።

ብዙም አልቆየም የአገዛዙ ኮማንድ ፖስት እንደገና ወደ ወህኒ አወረደው። ዳኒ በአሁኑ ወቅት ባላጠፋው ጥፋት ፣ ባልሰራው ወንጀል፣ እንደገና አገሩን እና ሕዝቡን በዉደዱ፣ ኢትዮጵያን በመዉደዱ ከሌሎች በመቶ ሺሆች ከሚቆጠሩ ኢትዮጵያዉያን ጋር በወህኒ እየማቀቀ ነው።

አገዛዙ ዳንኤል ወደ ወህኒ መዉሰድ ብቻ ሳይሆን፣ በወህኒ አንድ እስረኛ ማግኘት የሚገባውን መሰረታዊ መብት ተነፍጎ፣ ከፍተኛ የዉሃ እጥረት ያለበት፣ ቱሃን የበዛበት እሥር ቤት ነው እየተሰቃየ ያለው።

እነ ዳንኤል ሺበሺን በማሰር ግን ህጋዊና ሰላማዊ ትግሉን ማስቆም አይቻልም፡፡ ዛሬ ትግሉ ብዙ አንዷለሞችን፤ ብዙ አናኒያ ሶሪዎችን፤ ብዙ ኤሊያሶች ፣ ብዙ እዮኤሎችን፣ ብዙ ዶ/ር መረራ ጉዲናዎችም፣ ብዙ ዳንኤሎችን፣ ብዙ አስቴሮችን፣ ብዙ ንግስት ይርጋዎችን፣ ብዙ ኮሎኔል ደመቀ ዘዉዴዎችን ያፈራና ትግሉን በቁርጠኝነት የሚቀጥል ነው፡፡ እንደሚባለው ሊነጋ ሲል መጨለሙ አይቀርም፡፡

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

የሚሊዮኖች ድምጽ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule