• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ዉሃ በሌለበትና ቱሃን በበዛበት ጣቢያ እያንገላቱኝ ነው”

February 23, 2017 07:56 am by Editor Leave a Comment

  • ዳንኤል ሺበሺ ከወህኒ ያስተላለፈው መልእክት

ከቤተሰቡ በተገኘው መረጃ መሰረት ዳንኤል የተወለደው በደቡብ ኢትዮጵያ ነው፡፡ ያደገው እንደአብዛኛው ኢትዮጵያዊ በለምለሟ ቁጫ ወረዳ አረንጓዴ መስክ ሮጦና ተራራና አቀበት ወጥቶ ነው፡፡ ከልጅነቱ ጀምሮ ንቁ ነበርና ቤተሰቡ ወደ ትምህርት ቤት ሰደደው፡፡ ተማረ፡፡ እስከ ዩኒቨርስቲ በመዝለቅም ቀጠለ፡፡ ከዚያም ሳይማር ወዳስተማረው ህብረተሰብ በመመለስ ማገልገሉን ተያያዘው፡፡ ግና ትምህርት የአለማችንን ተጨባጭ ሁኔታ እንዲለይ አስችሎት ነበርና በሚሰራው ስራ ብቻ ሊረካ አልቻለም፡፡ ህዝቡ ላይ የማህበራዊ፤ ኢኮኖሚያዊና የማህበራዊ ፍትህ እጦት እንደሚያሰቃየው ተመለከተ፡፡

ወጣቱ ዳኒ በተደጋጋሚ እንደሚናገረው ‹‹ህዝቡ ላይ እየደረሰ ያለውን በደልና ግፍ ከንፈር በመምጠጥ ብቻ ማቆም እንደማይቻል አውቅ ነበር፡፡ እንደ አንድ ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ ምን ማድረግ እንዳለብኝ እጨነቅ ነበር፡፡ ወቅቱ ደግሞ ደርግ ወድቆ፣ ኢህአዴግ ስልጣን ይዞ የሚንደፋደፍበት ስለነበር ሁኔታዎች ወዴት ሊያመሩ እንደሚችሉ ለመገመት ሁሉ አይቻልም ነበር›› ይላል፡፡

ነገር ግን ‹‹ነፃ አውጭዎቹ›› ስልጣንና ሀብትን በሚለማመዱበት በዚያ ጊዜ መራራ ትግል ያካሄዱት በደርግ አገዛዝ መከራ የሚበላውን የኢትዮጵያ ህዝብ ነፃ ለማውጣት እንደሆነ በመስበካቸውና ከመንገድ ስለተቀበሉት ዴሞክራሲ በማውራታቸው ‹‹እስኪ እንያቸው!›› የሚል ስሜት መፈጠሩ አልቀረም፡፡ ይሄ ስሜትም ወጣቱ ዳንኤል ሺበሺ ላይ በማደሩ የኢህአዴግን ሁኔታ በአንክሮ ይከታተል እንደነበር ተናግሯል፡፡ በመቀጠልም ከታጋዮቹ ሌላ ጥሪ መጣለት ‹‹እናንተ ወጣቶች እኮ ዴሞክራሲያዊ ስርኣት ለመገንባት የምናደርገውን ትግል ብትደግፉን ይችን ሀገር መቀየር እንችላለን!›› የሚል ነበር፡፡

ዳንኤል ከዚህ በፊት በተለያዩ መድረኮች ይናገር እንደነበረው ‹‹ብታግዙን ጥሩ ነው›› የሚለውን ሀሳብ በወቅቱ ብዙ ወጣቶች በቀናነት በመውሰድ ‹‹ለሀገራችን መስራት ከቻልን ብናግዛቸው ጥሩ ነው›› በሚል ኢህአዴግን ተቀላቀሉ፡፡ ዳንኤል ሺበሺም በደኢህዴን በኩል የኢህአዴግ አባል ሆነ፡፡ አቶ ሃይለማሪያምን ጨምሮ ከአሁን አሳሪዎቹ ጋርም አብሮ ሰራ፡፡ የተባለው ዴሞክራሲ የማስፈን ነገር ከልብ አይደለምና ልዩነቶች እየተፈጠሩ መጡ፡፡ ዳንኤልና ሌሎች አንዳንድ ወጣቶች የምንላችሁን ብቻ ተቀበሉ፤ የምንላችሁን ብቻ ስሩ . . . የሚለው የህወሃት/ኢህአዴግ ትዕዛዝ መጀመሪያ ከተባሉት ጋር የሚጋጭ ነበርና የመርህ ጥያቄ ማንሳት ጀመሩ፡፡ የውስጥ ትግልም አደረጉ፡፡ ከኢህአዴግ ጋር ለመስራት ያደረገው ሙከራም ብዙ ርቀት ሳይሄድ በአጭሩ ተቀጨ፡፡ የስርዓቱን ውስጣዊ አፋኝ አሰራር ያየው ዳንኤልም በአደባባይ እንደማይጠቅም በመናገር በሰላማዊ መንገድ ለማስወገድ የሚደረገውን ትግል ተቀላቀለ፡፡

ዳንኤል ሺበሺ የኢዴፓ አባል የነበረ ሲሆን ቅንጅት ላይ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ካደረጉና እስካሁን ድረስ የሚያሰቃይ ድብደባ ከደረሰባቸው ወጣቶች አንዱ ነው፡፡ የአንድነት ፓርቲ መስራችና የደቡብ ቀጠና ኃላፊ በመሆን ከተመሰረተ ጀምሮ የሰራ ሲሆን በቅርቡ ደግሞ የድርጅት ጉዳይ ምክትል ኃላፊ በመሆን በትጋት የሚታገል የዴሞክራሲ አርበኛ ነው፡፡ ዳኒ ባለትዳርም ነው፡፡ የሚያምንበትን ፊት ለፊት የሚናገር፤ ደፋር ነገርግን ፈገግታ የማይለየው ዳኒ በትግል አጋሮቹ ዘንድ (ዳኒ ደቡብ) በመባል በቁልምጫ ይጠራል፡፡ ዳኒ ደቡብ በአጠቃላይ በኢትዮጵያ የሚፈፀሙ የሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብት ጥሰቶችን በማጋለጥ ይታወቃል፡፡ በቅርቡ ደግሞ የመብት ጥያቄ ባነሳው የቁጫ ህዝብ ላይ የተወሰደውን የጅምላ እስር በማውገዝ ያጋለጠና ይህንንም በተለያዩ ሚዲያዎች ይፋ ያደረገ እንዲሁም ለሚታገሉ ሁሉ መልካም አርአያ ሊሆን የሚችል ወጣት ነው፡፡

በዚህ አስከፊ ስርዓት ጥርስ የተነከሰበት ዳኒ ሐምሌ 1 ቀን 2006 ዓ.ም አገር አማን ብሎ ወደ ስራ ሲሄድ በፖሊሶች ተከቦ በካቴና ከታሰረ በኋላ ቤቱ ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት እስከ ምሽቱ 2፡00 ሰዓት ተፈትሾ ወደ ማሰቃያው ማዕከላዊ ተወስዷል፡፡ ከሃያ ወር ግፍና እንግልት በኋላ ዳንኤል ሺበሺ ከወህኒ ይለቀቃል። አገዛዙ በርሱ ላይ ላቀረበው የፈጠራ የሽብርተኝነት ክስ ማስረጃ ማቅረብ ባለመቻሉ።

ብዙም አልቆየም የአገዛዙ ኮማንድ ፖስት እንደገና ወደ ወህኒ አወረደው። ዳኒ በአሁኑ ወቅት ባላጠፋው ጥፋት ፣ ባልሰራው ወንጀል፣ እንደገና አገሩን እና ሕዝቡን በዉደዱ፣ ኢትዮጵያን በመዉደዱ ከሌሎች በመቶ ሺሆች ከሚቆጠሩ ኢትዮጵያዉያን ጋር በወህኒ እየማቀቀ ነው።

አገዛዙ ዳንኤል ወደ ወህኒ መዉሰድ ብቻ ሳይሆን፣ በወህኒ አንድ እስረኛ ማግኘት የሚገባውን መሰረታዊ መብት ተነፍጎ፣ ከፍተኛ የዉሃ እጥረት ያለበት፣ ቱሃን የበዛበት እሥር ቤት ነው እየተሰቃየ ያለው።

እነ ዳንኤል ሺበሺን በማሰር ግን ህጋዊና ሰላማዊ ትግሉን ማስቆም አይቻልም፡፡ ዛሬ ትግሉ ብዙ አንዷለሞችን፤ ብዙ አናኒያ ሶሪዎችን፤ ብዙ ኤሊያሶች ፣ ብዙ እዮኤሎችን፣ ብዙ ዶ/ር መረራ ጉዲናዎችም፣ ብዙ ዳንኤሎችን፣ ብዙ አስቴሮችን፣ ብዙ ንግስት ይርጋዎችን፣ ብዙ ኮሎኔል ደመቀ ዘዉዴዎችን ያፈራና ትግሉን በቁርጠኝነት የሚቀጥል ነው፡፡ እንደሚባለው ሊነጋ ሲል መጨለሙ አይቀርም፡፡

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

የሚሊዮኖች ድምጽ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በወልቃይት 1.1ሚሊዮን ኩንታል ሰሊጥ ለመሰብሰብ ከ1 ሚሊዮን በላይ ሠራተኛ ይፈለጋል September 27, 2023 10:42 am
  • በአማራ ክልል ሰላም ዕጦት ከ90.5 ቢሊዮን ብር በላይ ፕሮጀክቶች ቆመዋል September 27, 2023 08:41 am
  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am
  • ከያቤሎ አዲስ አበባ የተላከ ኮንትሮባንድ ጉለሌ ተያዘ September 7, 2023 01:40 pm
  • “እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መሻገር አቅቶናል” September 7, 2023 01:31 am
  • ራሱን መሪ አልባ የሚያደርገው አማራ ክልል August 24, 2023 11:50 pm
  • ጀብደኛው August 24, 2023 10:06 am
  • ጎንደርና ባሕር ዳር ከተሞች ወደ ቀድሞ ሰላማቸው ተመልሰዋል August 13, 2023 10:55 pm
  • ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያውን ግዙፍ ወታደራዊ ኃይል አስመረቀች August 13, 2023 10:26 pm
  • ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ August 13, 2023 09:11 pm
  • ወደ ኤርትራ በኮንትሮባንድ የሚሻገሩ ቆሳቁሶች እየተያዙ ነው August 11, 2023 12:52 pm
  • የአማራ ክልል ትልልቅ ከተሞች ተኩስ ዓልባ ሆነው ውለዋል August 10, 2023 04:31 pm
  • “አንድ ሰው ለመግደል ኅንፃውን ማቃጠል” የኢ-ዲሞክራሲና ጽንፈኛ ኃይሎች ቅዠት፤ (ክፍል ሁለት) August 10, 2023 09:44 am
  • “አርበኛ” መሳይ – “የድል ዜና” ሳይበርድ 50ሺህ ዶላር በጎፈንድሚ August 10, 2023 09:08 am
  • በሕዝቡ ድጋፍ ከተሞች ከዘራፊው መንጋ ሥጋት ነጻ መሆናቸው ይፋ ሆነ August 9, 2023 11:47 am
  • ትህነግ አራተኛውን ሞት ሞተ  August 8, 2023 05:47 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule