• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ዉሃ በሌለበትና ቱሃን በበዛበት ጣቢያ እያንገላቱኝ ነው”

February 23, 2017 07:56 am by Editor Leave a Comment

  • ዳንኤል ሺበሺ ከወህኒ ያስተላለፈው መልእክት

ከቤተሰቡ በተገኘው መረጃ መሰረት ዳንኤል የተወለደው በደቡብ ኢትዮጵያ ነው፡፡ ያደገው እንደአብዛኛው ኢትዮጵያዊ በለምለሟ ቁጫ ወረዳ አረንጓዴ መስክ ሮጦና ተራራና አቀበት ወጥቶ ነው፡፡ ከልጅነቱ ጀምሮ ንቁ ነበርና ቤተሰቡ ወደ ትምህርት ቤት ሰደደው፡፡ ተማረ፡፡ እስከ ዩኒቨርስቲ በመዝለቅም ቀጠለ፡፡ ከዚያም ሳይማር ወዳስተማረው ህብረተሰብ በመመለስ ማገልገሉን ተያያዘው፡፡ ግና ትምህርት የአለማችንን ተጨባጭ ሁኔታ እንዲለይ አስችሎት ነበርና በሚሰራው ስራ ብቻ ሊረካ አልቻለም፡፡ ህዝቡ ላይ የማህበራዊ፤ ኢኮኖሚያዊና የማህበራዊ ፍትህ እጦት እንደሚያሰቃየው ተመለከተ፡፡

ወጣቱ ዳኒ በተደጋጋሚ እንደሚናገረው ‹‹ህዝቡ ላይ እየደረሰ ያለውን በደልና ግፍ ከንፈር በመምጠጥ ብቻ ማቆም እንደማይቻል አውቅ ነበር፡፡ እንደ አንድ ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ ምን ማድረግ እንዳለብኝ እጨነቅ ነበር፡፡ ወቅቱ ደግሞ ደርግ ወድቆ፣ ኢህአዴግ ስልጣን ይዞ የሚንደፋደፍበት ስለነበር ሁኔታዎች ወዴት ሊያመሩ እንደሚችሉ ለመገመት ሁሉ አይቻልም ነበር›› ይላል፡፡

ነገር ግን ‹‹ነፃ አውጭዎቹ›› ስልጣንና ሀብትን በሚለማመዱበት በዚያ ጊዜ መራራ ትግል ያካሄዱት በደርግ አገዛዝ መከራ የሚበላውን የኢትዮጵያ ህዝብ ነፃ ለማውጣት እንደሆነ በመስበካቸውና ከመንገድ ስለተቀበሉት ዴሞክራሲ በማውራታቸው ‹‹እስኪ እንያቸው!›› የሚል ስሜት መፈጠሩ አልቀረም፡፡ ይሄ ስሜትም ወጣቱ ዳንኤል ሺበሺ ላይ በማደሩ የኢህአዴግን ሁኔታ በአንክሮ ይከታተል እንደነበር ተናግሯል፡፡ በመቀጠልም ከታጋዮቹ ሌላ ጥሪ መጣለት ‹‹እናንተ ወጣቶች እኮ ዴሞክራሲያዊ ስርኣት ለመገንባት የምናደርገውን ትግል ብትደግፉን ይችን ሀገር መቀየር እንችላለን!›› የሚል ነበር፡፡

ዳንኤል ከዚህ በፊት በተለያዩ መድረኮች ይናገር እንደነበረው ‹‹ብታግዙን ጥሩ ነው›› የሚለውን ሀሳብ በወቅቱ ብዙ ወጣቶች በቀናነት በመውሰድ ‹‹ለሀገራችን መስራት ከቻልን ብናግዛቸው ጥሩ ነው›› በሚል ኢህአዴግን ተቀላቀሉ፡፡ ዳንኤል ሺበሺም በደኢህዴን በኩል የኢህአዴግ አባል ሆነ፡፡ አቶ ሃይለማሪያምን ጨምሮ ከአሁን አሳሪዎቹ ጋርም አብሮ ሰራ፡፡ የተባለው ዴሞክራሲ የማስፈን ነገር ከልብ አይደለምና ልዩነቶች እየተፈጠሩ መጡ፡፡ ዳንኤልና ሌሎች አንዳንድ ወጣቶች የምንላችሁን ብቻ ተቀበሉ፤ የምንላችሁን ብቻ ስሩ . . . የሚለው የህወሃት/ኢህአዴግ ትዕዛዝ መጀመሪያ ከተባሉት ጋር የሚጋጭ ነበርና የመርህ ጥያቄ ማንሳት ጀመሩ፡፡ የውስጥ ትግልም አደረጉ፡፡ ከኢህአዴግ ጋር ለመስራት ያደረገው ሙከራም ብዙ ርቀት ሳይሄድ በአጭሩ ተቀጨ፡፡ የስርዓቱን ውስጣዊ አፋኝ አሰራር ያየው ዳንኤልም በአደባባይ እንደማይጠቅም በመናገር በሰላማዊ መንገድ ለማስወገድ የሚደረገውን ትግል ተቀላቀለ፡፡

ዳንኤል ሺበሺ የኢዴፓ አባል የነበረ ሲሆን ቅንጅት ላይ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ካደረጉና እስካሁን ድረስ የሚያሰቃይ ድብደባ ከደረሰባቸው ወጣቶች አንዱ ነው፡፡ የአንድነት ፓርቲ መስራችና የደቡብ ቀጠና ኃላፊ በመሆን ከተመሰረተ ጀምሮ የሰራ ሲሆን በቅርቡ ደግሞ የድርጅት ጉዳይ ምክትል ኃላፊ በመሆን በትጋት የሚታገል የዴሞክራሲ አርበኛ ነው፡፡ ዳኒ ባለትዳርም ነው፡፡ የሚያምንበትን ፊት ለፊት የሚናገር፤ ደፋር ነገርግን ፈገግታ የማይለየው ዳኒ በትግል አጋሮቹ ዘንድ (ዳኒ ደቡብ) በመባል በቁልምጫ ይጠራል፡፡ ዳኒ ደቡብ በአጠቃላይ በኢትዮጵያ የሚፈፀሙ የሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብት ጥሰቶችን በማጋለጥ ይታወቃል፡፡ በቅርቡ ደግሞ የመብት ጥያቄ ባነሳው የቁጫ ህዝብ ላይ የተወሰደውን የጅምላ እስር በማውገዝ ያጋለጠና ይህንንም በተለያዩ ሚዲያዎች ይፋ ያደረገ እንዲሁም ለሚታገሉ ሁሉ መልካም አርአያ ሊሆን የሚችል ወጣት ነው፡፡

በዚህ አስከፊ ስርዓት ጥርስ የተነከሰበት ዳኒ ሐምሌ 1 ቀን 2006 ዓ.ም አገር አማን ብሎ ወደ ስራ ሲሄድ በፖሊሶች ተከቦ በካቴና ከታሰረ በኋላ ቤቱ ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት እስከ ምሽቱ 2፡00 ሰዓት ተፈትሾ ወደ ማሰቃያው ማዕከላዊ ተወስዷል፡፡ ከሃያ ወር ግፍና እንግልት በኋላ ዳንኤል ሺበሺ ከወህኒ ይለቀቃል። አገዛዙ በርሱ ላይ ላቀረበው የፈጠራ የሽብርተኝነት ክስ ማስረጃ ማቅረብ ባለመቻሉ።

ብዙም አልቆየም የአገዛዙ ኮማንድ ፖስት እንደገና ወደ ወህኒ አወረደው። ዳኒ በአሁኑ ወቅት ባላጠፋው ጥፋት ፣ ባልሰራው ወንጀል፣ እንደገና አገሩን እና ሕዝቡን በዉደዱ፣ ኢትዮጵያን በመዉደዱ ከሌሎች በመቶ ሺሆች ከሚቆጠሩ ኢትዮጵያዉያን ጋር በወህኒ እየማቀቀ ነው።

አገዛዙ ዳንኤል ወደ ወህኒ መዉሰድ ብቻ ሳይሆን፣ በወህኒ አንድ እስረኛ ማግኘት የሚገባውን መሰረታዊ መብት ተነፍጎ፣ ከፍተኛ የዉሃ እጥረት ያለበት፣ ቱሃን የበዛበት እሥር ቤት ነው እየተሰቃየ ያለው።

እነ ዳንኤል ሺበሺን በማሰር ግን ህጋዊና ሰላማዊ ትግሉን ማስቆም አይቻልም፡፡ ዛሬ ትግሉ ብዙ አንዷለሞችን፤ ብዙ አናኒያ ሶሪዎችን፤ ብዙ ኤሊያሶች ፣ ብዙ እዮኤሎችን፣ ብዙ ዶ/ር መረራ ጉዲናዎችም፣ ብዙ ዳንኤሎችን፣ ብዙ አስቴሮችን፣ ብዙ ንግስት ይርጋዎችን፣ ብዙ ኮሎኔል ደመቀ ዘዉዴዎችን ያፈራና ትግሉን በቁርጠኝነት የሚቀጥል ነው፡፡ እንደሚባለው ሊነጋ ሲል መጨለሙ አይቀርም፡፡

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

የሚሊዮኖች ድምጽ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule