
ስለተከሰተው ሚስጢርና የሚስጢሩን ቀላል መደረግ አሁን የሚጠይቁኝ አይመስለኝም።ይልቁንም አጠቃቀሙ እንዴት ነው? ይሉኝ ይሆናል።ለዚህ በክፍል ሶስት ጽሁፌ መልስ ይዣለሁ።ከዛ በፊት ግን ታላቁ መጽሐፍ በዚህ ጉዳይ ላይ ምን ይላል?የሚስጢሩ ተጠቃሚዎችስ ምን ይነግሩናል?ይሄን አንብበው ወደ ሚስጢሩ አጠቃቀም ይሻገሩ።
“አምናችሁም፤ በፀሎት፤ የምትለምኑትን፤ ሁሉ ትቀበላላችሁ።” ማቴዎስ፤ ፳፩-፳፪
“የፀለያችሁትን፤ የለመናችሁትንም፤ እንዳገኛችሁት እመኑ። ይሆንላችሁማል።” ማርቆስ፤ ፲፩-፳፬
“ነገሮች ሁሉ፤ ይለወጡልህ ዘንድ ዓለም እንደገና ራሷን ታዘጋጃለች።” ዶ/ር ጆ ቫይታል
“የመጀመሪያው መነሻህ ታማኒነት ይሁን።የደረጃውን መጨረሻ አጠቃለህ ማየት አያስፈልግህም።ዝም ብለህ ወደ መጀመሪያው ደረጃ ውጣ።” ዶ/ር ማርቲን ሉተር ኪንግ
የሚስጢሩ አጠቃቀም
የምትፈልገውን ለመፍጠር ስታስብ
ሶስት ደረጃዎች እንዳሉ ተገንዘብ
ጥያቄህን አቅርብ አምነህ ሳትወላውል
የፈለከው ነገር ይመጣል ተቀበል
ለማየት ከፈለክ ይሄንን በተግባር
ፊት ለፊትህ ባለ ትንሽ ነገር ሞክር
መኪና ማቆሚያ አንድ ስኒ ቡና
የምትፈልግ ሆነህ ጥያቄ አቅርብና
ነገሩ ተሳክቶ ለማየት ስትችል
አቅምህን አዳብረህ ሌላ ደግሞ ቀጥል
ጠይቅ፣ እመን፣ አግኝ ይሄ ነው ሚስጢሩ
እጀህ ላይ ተቀምጧል መክፈቻው የበሩ
እንግዲህ ህይወትህ በየአንዳንዱ ቀናት
በስኬት አጊጣ ትርጉም እንዲኖራት
የተዘጋባትን መንገድ ክፈትላት።
***
መልዕክትና አስተያየት ካለዎት
Welelaye2@yahoo.com
The Secret (ሚስጢሩ…) ክፍል አንድን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ፡፡
The Secret (ሚስጢሩ…) ክፍል ሁለትን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ፡፡
Leave a Reply