• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የዜጎች የፍትሕ ጥያቄ በሸገር – መቀሌ የፖለቲካ ጡዘት እንዳይጠለፍ!

December 17, 2018 08:28 am by Editor Leave a Comment

የጠቅላይ ሚንስትሩ ጥረት ወንጀል ፈጽመው የተደበቁትን ብቻ ሳይሆን ወንጀል ፈጽመው በአደባባይ የሚንጎማለሉትንም ሆነ ወንጀለኞችን የሸሸጉትን መጨመር አለበት።

ኢትዮጵያ ውስጥ ባለፉት አሥርት አመታት የሰብአዊ መብቶች የተፈጸመው እና ሰዎች በግፍና አስከፊ በሆነ ሁኔታ እንዲሰቃዩ የተደረጉት በሁሉም የአገሪቱ ክፍሎች ነው። አድራጊዎቹም በሁሉም ድረጃ የሚገኙ ሹማምንት እና የጸጥታ ሰራተኞች ናቸው። የተለየ ቀለም፣ ዘር፣ ኃይማኖት ወይም ሌላ የማንነት መገለጫ የላቸውም። እንደተበዳዩ ስብጥር ሁሉ በደል አድራሾቹም የተሰባጠሩ ናቸው።

በማዕከላዊ እስር ቤት ከተፈጸመው ባልተናነሰ መልኩ ከጋንቤላ እስከ ዑጋዴን፣ ከጎንደር እስከ ሞያሌ፣ ከአፋር እስከ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ ከትግራይ እስከ ኮንሶ ባሉት የአገሪቱ ግዛቶች ሁሉ ግፍ በገፍ ተፈጽሟል።

ይህን ሰፊ እና ውስብስብ ችግር በይቅርታም ይታለፍ ወይም አጥፊዎችን ለፍርድ በማቅረብ ጉዳዩ በጥንቃቄ ተይዞና በገለልተኛ አካል ተመርምሮ፣ ማስረጃ ተጠናክሮ እና የአጥፊዎቹ ማንነት በስም እና በኃላፊነት ደረጃ ተገልጾ ለሕዝብ እና ለአገሪቱ ፓርላማ መቅረብ አለበት።

አሁን በመገናኛ ብዙሃን በተዝረከረከና ደረጃውን ባልጠበቀ መልኩ እየቀረበ ያለው የግፈኞች ስንክ ሳር እና የተበዳዮች ሰቆቃ እንዲሁም ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢሮ ትላንት የወጣው ዛቻና ማሰራሪያ ያዘለ መግለጫ የዜጎችን የፍትሕ ጥያቄ በአግባቡ ከመመልስ ይልቅ ሌሎች ችግሮችን ሊያስከትል ይችላል። በጥቂቱ ለመጥቀስ ያህል፤

– ከፍተኛ የመብት ጥሰት የፈጸሙ እና ከተጠያቂነት ማምለጥ የሌለባቸው ሰዎች ከወዲሁ አገር ጥለው እንዲሸሹ እድል ይፈጥራል። የተወሰኑትም በቅርቡ አገር ጥለው መሸሻቸው እየተገለጸ ነው። መንግስት በወንጀል ተጠርጣሪዎች ላይ የፍርድ ቤት የመያዣ ትእዛዝ አውጥቶ እና ሰዎቹን በቁጥጥር ስር ካዋለ በኋላ ለሚዲያ ዘገባው ቀስ ብሎ ይደረስበት ነበር። ከዛ ይልቅ በሙስናውም ጉዳይ ጠቅላይ አቃቤ ሕጉ የማሰሪያ ማዘዣውን ይዞ መጀመሪያ የሚሮጠው ወደ ሚዲያዎች ነው። እነ እገሌን ለማሰር ማዘዣ ወጥቷል እየተባለ በየሚዲያው በሰነድ በተደገፈ መልኩ የሰዎች ስም ተዘርዝሮ ይወጣል። ይህ ማለት ልንይዛችው ስለሆነ ከቻላችው አምልጡ ማለትም ነው። ከዛ በኋላ ያለው ሰዶ ማሳደድ የቶም እና ጄሪ አይነት ጨዋታ ነው የሚሆነው። መንግስት በሕግ አንድን ሰው ለመያዝ የሚያስፈልጉትን ቅደ ዝግጅቶች ያድርግ እንጂ የሚዲያ ልፈፋው ለምን አስፈለገ?

– አብዛኛው በደል አድራሽ በመንግስት ቁጥጥር ስር ባልዋለበት፤ ገሚሶቹም የመንግስት ተሿሚዎች ሆነው እየሰሩ ባለበት በዚህ ወቅት ተበዳዮች ፊታቸው እየታየ እና ማንነታቸው እየተገለጸ በመገናኛ ብዙሃን በዚህ መልኩ መቅረባቸው ለበለጠ ስጋት እና አደጋ እንዲጋለጡ ያደርጋል። ወንጀላቸውን ለመደበቅ የሚጥሩ ባለሥልጣናት የስቃይ ሰለባዎቹን ለማስፈራራትም ሆን ለማስወገድ አቅም እንዳላቸው ይታወቃል። አንዳንዶቹ በመገናኛ ብዙሃን ቀርበው በደላቸውን ከገለጹ በኋላ ዛቻ እና ማስፈራሪያ የደረሰባቸው መሆኑን እየገለጹ ነው። እነዚህ በመገናኛ ብዙሃን ወጥተው ምስክርነት የሰጡት ሰዎች ተጠርጣሪዎቹ ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ስር እስኪውሉ ድረስ የመንግሥት ጥበቃ ሊደረግላቸው ይገባል። ይህ አይነቱ አሰራር በብዙ አገሮች የተለመደ ነው። ምስክር ሊሆኑ የሚችሉ እና ተበዳይ የሆኑ አቤቱታ አቅራቢዎችን በቀላሉ በማስወገድ ወንጀለኞች ከተጠያቂነት ለመዳን ሙከራ እንደሚያደርጉ ይታወቃል።

– እጅግ ሙያዊ ስነ-ምግባር በጎደለው መልኩ አኬልዳማ፣ አረካዊ አራፋት እና ሌሎች የሃሰት ዶክመንተሪ ፊልሞችን እያቀናበሩ በእነዚሁ ግፉዋን ላይ ስም ሲያጠፉ እና ሲያጠለሹ ለነበሩ መገናኛ ብዙሃን ይህን አይነት አሳሳቢ እና ጥንቃቄ የሚጠይቅ አገራዊ ጉዳይ አሳልፎ መስጠት ሌላው አላፊነት የጎደለው የመንግስት እርምጃ ነው። እነዚህ ጉዳዮች የቀረቡበት ሁኔታ ከፍትህ ፍላጎት ይልቅ የፖለቲካ ፕሮፓጋንዳ ለማሳካት በሚመስል መልኩ ነው የቀረቡት። ይህ ደግሞ ብዙ ሰው አገሪቱ ውስጥ ይፈጸም ለነበረው የመብት ጥሰት መጠን፣ ባህሪ እና የፈጻሚዎች ማንነት ላይ እጅግ የተዛባ ግንዛቤ እንዲይዝ አድርጎታል።

– የዛሬዎቹ ተደማሪ ባለሥልጣናት እና የክልል ፖሊስ እና የደህንነት ሹሞች በአብዛኛው የመብት ጥሰት ወንጀል ተሳታፊዎች ናቸው። ናዝሬት ላይ የወንድ ብልት ያኮላሹት፣ አንቦ ላይ ጥፍር የነቀሉት፣ ደብረ ማርቆስ ላይ እስረኛን በቁሙ አንገቱ ድረስ ቀብረው ከነነፍሱ በላዩ ላይ ፕላስቲክ በእሳት እያቀለጡ ያሰቃዩት፣ በደቡብ ክልል የተለያዩ እስር ቤቶች በድብደባ ብዛት ታሳሪዎችን አሰቃይተው የገደሉት፣ በድሬደዋ፣ በሐረር፣ በጋምቤላ፣ በአሳይታ እና ሌሎች የአገሪቱ ክፍሎች በእሥረኞች ላይ ይህ ነው የማይባል ግፍና ስቃይ የፈጸሙት የየክልሉ ተሿሚዎች እና የደህንነት ሠራተኞች ናቸው። አዲስ አበባ ፌዴራል ኮሚሽኑ ቢሮ ውስጥ በሚገኝ እስር ቤት ሌሊቱን ሙሉ ሲገረፍ አድሮ ነፍሱ ስታልፍ የራሱን ልብስ ተልትለው ከሰቀሉት በኋላ እራሱን እንደሰቀለ አድርገው አስከሬኑን ለቤተሰቡ የሰጡት የሳሪስ አካባቢ ነዋሪና የአምስት ልጆች አባት የሆነውን የአበራ ይሄን በደለና ድምጽስ ማን በኢቲቪ መጥቶ ይንገርለት። አበራ ይሄ የታሰረው በኦነግ አባልነት ተጠርጥሮ ነው።

መንግስት ፍትህ ለማስፈን የጀመረው ጥረት እንዲሳካ እና ሂደቱም በፖለቲካ ሸር ተጠልፎ የታለመለትን ግብ ሳያሳካ ከመንገድ እንዳይቀር ከተፈለገ ተገቢውን ጥንቃቄ ሁሉ ከወዲሁ ሊደረግ ይገባል።

አምቦ እና ባህርዳር ላይ የሰው ብልት ያኮላሸ እና ስቃይ የፈጸመ ገራፊን ወንጀለኛ ለውጡን እልል እያለ ስለተቀበለ እና ሰለተደመረ ባላየ እያለፍን ማዕከላዊ ላይ ካተኮርን አካሄዳችን ላይ ሽግር አለ። ማዕከላዊን ባልታሰርበትም ውስጡ ያለውን አደረጃጀት በደንብ አውቀዋለሁ። የመብት ጥሰት ለማጣራት እና በሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ኃላፊዎቹ ቢሮም በተደጋጋሚ ገብቼ ያለውን ሁኔታ ለማየት እድል አግኝቻለው። ቦታው አዲስ አበባ ላይ ቢሆንም ግቢው ውስጥ ያለው መንፈስ ግን መቀሌ ያለህ ነው የሚመስለው። ከፈታሽ ፖሊስ እስከ ከፍተኛ ኃላፊ ድረስ ያሉት ሰዎች ነባር ተጋዳላይ እና የህውሃት ደህንነት ኃይሎች ናቸው። ከሌላ ብሔር የመጡ ሰዎች አልፎ አልፎ ቢኖሩም ቁጥራቸው ከግምት የሚገባ አይደለም። እዚህ እስር ቤት ውስጥ አሳሪውም፣ መርማሪውም ሆነ ደብዳቢው ከአንድ አካባቢ የመጡ ሰዎች ናቸው። ይሁን እና መዘንጋት የሌለበት እዚህ እስር ቤት የሚመጡት ከፍ ያለ ፖለቲካ ነክ ጉዳዮች ጋር በተያያዘ የታሰሩ ሰዎች ብቻ ናቸው።

በመንግስት መገናኛ ብዙሃን የተገለጹትም ሆነ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማስፈራሪያነት ወንጀለኞችን ከተደበቁበት እንይዛለን በሚል የለቀቁት የትላንቱ መግለጫ በግልጽ የሚያሳዩት አልደመር ብሎና አኩርፎ መቀሌ በመሸገው የወያኔ የወንጀል ግብረ ኃይል ላይ ነው። ይህ ኃይል ከፍተኛውን የወንጀል አድራጎት መፈጸሙ የሚጠራጠር የለም። በቁጥጥር ስር ውለው ለፍርት እንዲቀርቡ ስንወተውት ቆይተናል። ወንጀል ከሰሩት ውስጥ የተደበቀው ይህ ቡድን ብቻ ነው። ሌላው በነጻነት እየተንጎማለለና ሹመት ያጽና ተብሎም ቀጥሏል። ይህ አይነቱ አካሄድ የመንግስትን ጥረት ለፍትህ ሳይሆን የፖለቲካ ፍትጊያውን ለማሸነፍ ብቻ እንደ ስልት የተወሰደ እርምጃ ተደርጎ እንዲታይ ያደርገዋል።

መቀሌ የመሸገው እና እፍረት በተፈጥሮው የማያውቀው የወያኔ ቡድንም ይህን ክፍተት ተጠቅሞ እየተወሰዱ ያሉትን እርምጃዎች በትግራይ ሕዝብ ላይ እንደተሰነዘረ ጥቃት በማስመሰል ዛሬም በሕዝቦች ቅራኔ ለመነገድ የሚችለውን ሁሉ እያደረገ ነው። አሁን የተጀመረው የፖለቲካ መጓተት እና የተዘበራረቀ የፍትህ ሂደት ለእነዚህ የወንጀል ተጠርጣሪዎች መደበቂያ ዋሻ እንዲፈጥሩና ገሚሶቹም ከአገር እንዲሸሹ ሁኔታዎችን እያመቻቸ ነው።

አሁንም የዶ/ር አብይ አስተዳደር ይህን ችግር በቅጡ ቢይዘው ይሻላል።

በቸር እንሰንብት!

yhailema@gmail.com


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule