• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ድሆች በደሃ ወገኖቻቸው ላይ ዘመቱ!!

December 15, 2015 02:16 pm by Editor Leave a Comment

“…. የመከላከያ ሰራዊት አባላት የተገነባው በደሃ ልጆች ነው። እባካችሁን እንደናንተው የድሃ ልጆች ወገኖቻቹህን አትግደሉ። ተንደላቃችሁ የምትኖሩም ለዚህ ህዝብ ራሩለት። ለራሳችሁ ጥቅም ስትሉ ይህን ህዝብ አታስፈጁት…” ሲሉ አቶ በቀለ ገርባ ለኢህአዴግ የመከላከያ ሰራዊትና ለህወሃት ታማኝ አገልጋይ ሹመኞች ጥሪ አስተላለፉ። አሁን በተያዘው መንገድ ከተቀጠለ ለማንም አይበጅም ሲሉ በግልም ሆነ በጋራ ህዝብን የሚያከብር ታሪካዊ ውሳኔ እንዲወስኑ ተማጸኑ። አቶ ኦባንግ ሜቶና አርቲስት ታማኝ በየነ “የሞቱት ዜጎች ሞት የሁላችንም ሞት ነው” ሲሉ ሁሉም ያገባኛል በሚል ስሜት ድጋፍ እንዲሰጥ ጥሪ አቀረቡ።

አቶ በቀለ በዲሰምበር ፩፫ ቀን ፳፩፮ ከኢሳት ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንዳስታወቁት፣ መከላከያ ሰራዊት ማለት ህዝቡን ከአምባገነኖች የሚታደግ እንጂ የራሱን ህዝብ የሚገድል ባዕድ ሃይል አይደለም ብለዋል፡፡ “ለምን እንደ ባዕድ መታየት ትፈልጋላችሁ” በማለት የጠየቁት አቶ በቀለ “እባካችሁ ራሩ” ሲሉ ለምነዋል።

“የድሃ ልጅ በድሃ ላይ እንዲዘምት መደረጉ ያሳዝናል” ሲሉ ሃዘን በተሞላበት ስሜት የተናገሩት የኦፌኮ ምክትል ሊቀመንበር “በአሰቃቂ ሁኔታ ልጆቻቸውን እየመገቡ ጦማቸውን የሚውሉ ወላጆች በሚኖሩበት አገር እናንተ ተንደላቃችሁ የምትኖሩ ራሩ” በማለት ሁሉም ጊዜና ወቅቱን በመመርመር ወደ ልባቸው እንዲመለሱ አሳስበዋል። አያይዘውም “እባካችሁ እግዚአብሔርን ፍሩ” ሲሉ ከራሳችን አገርና ከሌሎች አገራት ትምህርት እንዲወስዱ ተማልደዋል።

armyለህዝብ ርህራሄ የሌላቸው አንድ ቀን በሃላፊነት እንደሚጠየቁ ያሳሰቡት አቶ በቀለ አጠንክረው ተናግረዋል። ከ፶ በላይ ዜጎች መገደላቸውን፣ መረጃው ሲሰበሰብ የሟቾች ቁጥር እንደሚጨምር በመግለጽ የችግሩን ስፋት አሳይተዋል።

በተመሳሳይ ርዕስ ኢሳት ያወያያቸው አቶ ኦባንግ ሜቶና አርቲስት ታማኝ በየነ የአንድ ኢትዮጰያዊ ሞት የሁላችንም ሞት ሆኖ ሊሰማን እስካልቻለ ድረስ ኢትዮጵያዊነት መገለጫው ምን ሊሆን ነው ሲሉ ጠይቀዋል። የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዋና ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ “ህወሃት ገና ከጅምሩ መግደል ሲጀምር ሌሎች በኅብረት ቢቃወሙ ኖሮ ዛሬ ደረጃ ላይ አይደረስም ነበር” ሲሉ የህብረትን አስፈላጊነት አስምረውበታል።

አርቲስት ታማኝ በየነ በበኩሉ ዋቢ መረጃዎችን በማጣቀስ የህወሃትን ገበና ካስታወሰ በኋላ “አንዱ ሲሞት ሌላው ዝም የሚል ከሆነ ሞት በእያንዳንዳችን ደጅ ትመጣለች፤ ባርነቱም ይቀጥላል” ሲል በሰውነት ደረጃ ብቻ እንኳን ሃዘኔታችንን ልንገልጽ እንደሚገባ አመልክቷል። “መቃወም እንዴት ያስገድላል” ሲል ጠይቆ “ጥቂቶች ይሉናል፣ እነሱ ናቸው ወይስ የሚቃወሟቸው ናቸው ጥቂቶች” በማለት ይመልሳል። እንደገናም “የሚመሩን ፲፻ አይሞሉም” ይልና በመገረም በ፻ ሺህ የሚቆጠርን ህዝብ “ጥቂቶች” ሲሉ መስማት በህዝብ ላይ የመዛበት አይነት እንደሆነ ያሳያል። ህብረት አስፈላጊ ነው ሲል ጥሪውን አቅርቧል።

“ነጻ መውጣት መብት ነው” የሚል የቆየ እምነት ያላቸው የሰላማዊ ትግል አራማጁ አቶ ኦባንግ “ከሳጥናችን ካልወጣን ዋጋ የለንም” ሲሉ አሁን ሁሉም ያለው “ምን አገባኝ” በሚል ሳጥን ውስጥ እንደሆነ አስረድተዋል። አንዱ ላይ ጉዳት ሲደርስ፣ አንዱ ሲገደል፣ አንዱ ሲነካ ዝም ማለት የህወሃትን እድሜ እንዳረዘመው የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ኦባንግ አመልክተዋል።

“ቅኝ ወራሪዎች መጀመሪያ የሚወሩትን አገር ይከፋፍላሉ” ያሉት አቶ ኦባንግ “አሁን ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው አገዛዝ፣ የቅኝ ገዢዎቹ ቀለም ተመሳሳይ ከመሆኑ በቀር ከደቡብ አፍሪካ አፓርታይድ አገዛዝ ተለይቶ አይታይም” ሲሉ አገሪቱን እየገዛ ያለውን የትግራይ ህዝብ ተገንጣይ ቡድን ተመሳሳይ ስልት እየተጠቀመ መሆኑን ተናግረዋል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የሲኖዶሱ ውዝግብ አካሄድና መጪው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ February 6, 2023 02:03 am
  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule