• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ድሆች በደሃ ወገኖቻቸው ላይ ዘመቱ!!

December 15, 2015 02:16 pm by Editor Leave a Comment

“…. የመከላከያ ሰራዊት አባላት የተገነባው በደሃ ልጆች ነው። እባካችሁን እንደናንተው የድሃ ልጆች ወገኖቻቹህን አትግደሉ። ተንደላቃችሁ የምትኖሩም ለዚህ ህዝብ ራሩለት። ለራሳችሁ ጥቅም ስትሉ ይህን ህዝብ አታስፈጁት…” ሲሉ አቶ በቀለ ገርባ ለኢህአዴግ የመከላከያ ሰራዊትና ለህወሃት ታማኝ አገልጋይ ሹመኞች ጥሪ አስተላለፉ። አሁን በተያዘው መንገድ ከተቀጠለ ለማንም አይበጅም ሲሉ በግልም ሆነ በጋራ ህዝብን የሚያከብር ታሪካዊ ውሳኔ እንዲወስኑ ተማጸኑ። አቶ ኦባንግ ሜቶና አርቲስት ታማኝ በየነ “የሞቱት ዜጎች ሞት የሁላችንም ሞት ነው” ሲሉ ሁሉም ያገባኛል በሚል ስሜት ድጋፍ እንዲሰጥ ጥሪ አቀረቡ።

አቶ በቀለ በዲሰምበር ፩፫ ቀን ፳፩፮ ከኢሳት ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንዳስታወቁት፣ መከላከያ ሰራዊት ማለት ህዝቡን ከአምባገነኖች የሚታደግ እንጂ የራሱን ህዝብ የሚገድል ባዕድ ሃይል አይደለም ብለዋል፡፡ “ለምን እንደ ባዕድ መታየት ትፈልጋላችሁ” በማለት የጠየቁት አቶ በቀለ “እባካችሁ ራሩ” ሲሉ ለምነዋል።

“የድሃ ልጅ በድሃ ላይ እንዲዘምት መደረጉ ያሳዝናል” ሲሉ ሃዘን በተሞላበት ስሜት የተናገሩት የኦፌኮ ምክትል ሊቀመንበር “በአሰቃቂ ሁኔታ ልጆቻቸውን እየመገቡ ጦማቸውን የሚውሉ ወላጆች በሚኖሩበት አገር እናንተ ተንደላቃችሁ የምትኖሩ ራሩ” በማለት ሁሉም ጊዜና ወቅቱን በመመርመር ወደ ልባቸው እንዲመለሱ አሳስበዋል። አያይዘውም “እባካችሁ እግዚአብሔርን ፍሩ” ሲሉ ከራሳችን አገርና ከሌሎች አገራት ትምህርት እንዲወስዱ ተማልደዋል።

armyለህዝብ ርህራሄ የሌላቸው አንድ ቀን በሃላፊነት እንደሚጠየቁ ያሳሰቡት አቶ በቀለ አጠንክረው ተናግረዋል። ከ፶ በላይ ዜጎች መገደላቸውን፣ መረጃው ሲሰበሰብ የሟቾች ቁጥር እንደሚጨምር በመግለጽ የችግሩን ስፋት አሳይተዋል።

በተመሳሳይ ርዕስ ኢሳት ያወያያቸው አቶ ኦባንግ ሜቶና አርቲስት ታማኝ በየነ የአንድ ኢትዮጰያዊ ሞት የሁላችንም ሞት ሆኖ ሊሰማን እስካልቻለ ድረስ ኢትዮጵያዊነት መገለጫው ምን ሊሆን ነው ሲሉ ጠይቀዋል። የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዋና ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ “ህወሃት ገና ከጅምሩ መግደል ሲጀምር ሌሎች በኅብረት ቢቃወሙ ኖሮ ዛሬ ደረጃ ላይ አይደረስም ነበር” ሲሉ የህብረትን አስፈላጊነት አስምረውበታል።

አርቲስት ታማኝ በየነ በበኩሉ ዋቢ መረጃዎችን በማጣቀስ የህወሃትን ገበና ካስታወሰ በኋላ “አንዱ ሲሞት ሌላው ዝም የሚል ከሆነ ሞት በእያንዳንዳችን ደጅ ትመጣለች፤ ባርነቱም ይቀጥላል” ሲል በሰውነት ደረጃ ብቻ እንኳን ሃዘኔታችንን ልንገልጽ እንደሚገባ አመልክቷል። “መቃወም እንዴት ያስገድላል” ሲል ጠይቆ “ጥቂቶች ይሉናል፣ እነሱ ናቸው ወይስ የሚቃወሟቸው ናቸው ጥቂቶች” በማለት ይመልሳል። እንደገናም “የሚመሩን ፲፻ አይሞሉም” ይልና በመገረም በ፻ ሺህ የሚቆጠርን ህዝብ “ጥቂቶች” ሲሉ መስማት በህዝብ ላይ የመዛበት አይነት እንደሆነ ያሳያል። ህብረት አስፈላጊ ነው ሲል ጥሪውን አቅርቧል።

“ነጻ መውጣት መብት ነው” የሚል የቆየ እምነት ያላቸው የሰላማዊ ትግል አራማጁ አቶ ኦባንግ “ከሳጥናችን ካልወጣን ዋጋ የለንም” ሲሉ አሁን ሁሉም ያለው “ምን አገባኝ” በሚል ሳጥን ውስጥ እንደሆነ አስረድተዋል። አንዱ ላይ ጉዳት ሲደርስ፣ አንዱ ሲገደል፣ አንዱ ሲነካ ዝም ማለት የህወሃትን እድሜ እንዳረዘመው የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ኦባንግ አመልክተዋል።

“ቅኝ ወራሪዎች መጀመሪያ የሚወሩትን አገር ይከፋፍላሉ” ያሉት አቶ ኦባንግ “አሁን ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው አገዛዝ፣ የቅኝ ገዢዎቹ ቀለም ተመሳሳይ ከመሆኑ በቀር ከደቡብ አፍሪካ አፓርታይድ አገዛዝ ተለይቶ አይታይም” ሲሉ አገሪቱን እየገዛ ያለውን የትግራይ ህዝብ ተገንጣይ ቡድን ተመሳሳይ ስልት እየተጠቀመ መሆኑን ተናግረዋል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
Copyright © 2026 · Goolgule