• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በኮሞሮስ ባንዲራ የሚቀዝፉት የሜቴክ መርከቦች እና በካሪቢያን ስም የምትቀዝፈው የኢትዮጵያ መርከብ

November 23, 2018 04:50 am by Editor Leave a Comment

የፌደራል ዋና አቃቢ ህግ ሜቴክ ከተቋቋመበት ዓላማ ውጪ በገዛቸው ሁለት መርከቦች አማካኝነት በህግወጥ የንግድ እንቅስቃሴ መሰማራቱን ገልፆ እንደነበር ይታወሳል። ሆኖም ግን በሜቴክ ዋና ዳይሬክተር ሜ/ጄ ክንፈ ዳኘው ላይ የቀረበው ክስ ድርጅቱ ከተቋቋመበት ዓላማ ውጪ አባይ እና ህዳሴ የተባሉትን ሁለት መርከቦች በመግዛት ከፍተኛ የገንዘብ ብክነት የሀገርና ህዝብን ሃብት ያለ አግባብ አባክኗል የሚል ነው። ሆኖም ግን ለድረገፃች አዘጋጅ በደረሰው መረጃ መሠረት ሜቴክ የገዛቸው ሁለት መርከቦች እ.አ.አ. እስከ 02 – 07/-01-2016 በምስራቅ አፍሪካዊቷ የኮሞሮስ (Comoros) ደሴት ሰንደቅ ዓላማ አያውለበልቡ በህገወጥ ንግድ ተሰማርተው እንደነበር ለማወቅ ተችሏል።

ከጉዳዩ ጋር ተያይዞ በቀረበው የቴሌቪዥን ዶክመንተሪ ሜቴክ እ.አ.አ. በ2014 ዓ.ም አባይ እና ህዳሴ የተባሉን መርከቦች ከኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርት እና ሎጂስቲክ አገልግሎት ኢንተርፕራይዝ ያለ አግባብ መግዛቱና ለጥገና ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ ማውጣቱ ተገልጿል። በመጨረሻም እ.አ.አ. በ2016 ዓ.ም ሁለቱን መርከቦች በዝቅተኛ ዋጋ ለሌላ ድርጅት መሸጡን ተገልጿል። በዚህ መልኩ ሜቴክ ከፍተኛ ገንዘብ ያለ አግባብ ከማውጣቱ በተጨማሪ ሁለቱን መርከቦች የኮሞሮስ ሰንደቅ ዓላማን እንዲያውለበልቡ በማድረግ በህገወጥ የባህር ትራንስፖርትና ንግድ ተሰማርቶ እንደነበር ለማወቅ ተችሏል።

1) “አባይ” እና “ህዳሴ” እንደ “Padma” እና “Tika”

በመጀመሪያ እ.አ.አ. በ2016 ዓ.ም ከመላው ከአገልግሎት ውጪ በመሆናቸው ምክንያት ተቆራርጠው ለሌላ ነገር መስሪያ እንዲውሉ የተደረጉ መርከቦችን ዝርዝር (2016-List-of-all-ships-scrapped-all-over-the-world) አገኘን። በዚህ መረጃ መሰረት ተጠቀሰው አመት 862 መርከቦች አካላቸው ተቆራርጦ ለሌላ መርከብ ወይም ዕቃ መስሪያ ውሏል። ከእነዚህ ውስጥ ደግሞ በተራ-ቁጥር 172 እና 173 ላይ ሁለት የኢትዮጵያ መርከቦች ተዘርዝረዋል። በዝርዝሩ መሰረት አባይ እና ህዳሴ የተባሉት መርከቦች “Padma” እና “Tika” የሚል ስም ተሰጥቷቸው በኮሞሮስ ሀገር ሰንደቅ ዓላማ ሲንቀሳቀሱ እንደነበር መረጃው ይጠቁማል።

በመጨረሻም እ.አ.አ. በ07-01-2016 ዓ.ም “Padma” የተባለችው መርከብ እንድትቆራረጥ በህንድ ሀገር ለሚገኝ “Alang” የተባለ ኩባንያ ተሸጣለች። “Tika” የተባለችው መርከብ ደግሞ በ02-02-2016 ዓ.ም በፓኪስታን ሀገር ለሚገኝ “Gadani” የተባለ ኩባኒያ መሸጧ ተጠቅሷል። ይሁን እንጂ በኮሞሮስ ሰንደቅ ዓላማ የሚንቀሳቀሱት እነዚህ ሁለት መርከቦች እስከተሸጡበት ዕለት ድረስ ባለቤታቸው፣ ለሥራ የሚያንቀሳቅሳቸው እና ተጠቃሚ ተብሎ የተጠቀሰው አካል ሜቴክ ሳይሆን “የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርት እና ሎጂስቲክ አገልግሎት ኢንተርፕራይዝ” (Ethiopian Shipping and Logistics Service Enterprise) ነው።

በዚህ መሰረት ሜቴክ የሁለቱን መርከቦች ስምና ሰንደቅ ዓላማ ቀይሮ “የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርት እና ሎጂስቲክ አገልግሎት ኢንተርፕራይዝ” ግን የመርከቦቹ ህጋዊ ባለቤት፣ ተጠቃሚና ተጠያቂ አድርጎ በሀገርና ድርጅቱ ስም በህገወጥ ንግድ ተሰማርቶ እንደነበር መገንዘብ ይቻላል። ስለሁለቱ መርከቦች የቀረበውን መረጃ ከታች ካለው ምስል መመልከት ይቻላል። በ2016 ዓ.ም በመላው ዓለም እንዲቆራረጡ የተሸጡት 862 መርከቦች ሙሉ ዝርዝር መረጃን ይህን ሊንክ (Excel) በመጫን ማውረድ ይቻላል።

“Padma” እና “Tika” የሚል ስም ተሰጥቷቸው በኮሞሮስ ሀገር ሰንደቅ ዓላማ ሲንቀሳቀሱ የነበሩት አባይ እና ህዳሴ

2) ከኮሞሮስ ደሴት ወደ ካሪቢያን ደሴት

ከቅርብ አመታት በፊት ዊኪሊክስ (WikiLeaks) የተባለው ድረገፅ ባወጣው መረጃ መሰረት የተለያዩ ዓለም አቀፍ ድርጅቶችና ባለሃብቶች ገንዘባቸውን ወደ ካሪቢያን ደሴቶች በማሸሽ ከፍተኛ የሆነ የታክስ ማጭበርበር እንደሚፈፅሙ ማጋለጡ ይታወሳል። በእርግጥ በወቅቱ የፈትልኮ የወጣውን መረጃ በተወሰነ ደረጃ ለማየት ሞክሬ ነበር። ከዚያ በፊት ድረገጹ አስፈትልኮ ባወጣው የሚስጥር ሰነድ በአዲስ አበባ የቀድሞ የአሜሪካው አምባሳደር የነበሩት ዶናልድ ያማማቶ ስለ ቀድሞ ጠ/ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የግል ስብዕና እና ባህሪ፣ ከቀድሞ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት ኃላፊ ከነበረው አቶ ጌታቸው አሰፋ ጋር ስላደረጉት ውይይት እና ሌሎች መረጃዎችን ማንበቤን አስታውሳለሁ።

በወቅቱ አፈትልኮ ከወጣው የሚስጥር መረጃ ውስጥ “Ethiopia” የሚለውን ቃል በመፈለግ ከሀገራችን ጋር በተያያዘ ያለውን መረጃ ማንበብ ችዬ ነበር። ከካሪቢያን ደሴቶች ጋር ተያያዞ የሚስጥር መረጃ በድረገፅ ሲለቀቅ በተመሳሳይ መንገድ ከኢትዮጵያ ጋር ተያያዥነት ያለውን መረጃ ለመፈለግ ሞክሬ ነበር። ነገር ግን የምፈልገውን ዓይነት መረጃ ስላላገኘሁ ነገሩን ችላ ብዬው ነበር። ባለፉት አመታት በሀገራችን ሲፈፀሙ የነበሩ የዘረፋና ሌብነት ተግባራትን አስመልክቶ በጅቡቲ የኢትዮጵያ አምባሳደር የነበሩት አባምሳደር ሱሊማን ደደፎ ስለ ሜቴክ የተናገሩት ነገር ትኩረቴን ሳበው።

አምባሳደር ሱሌማን ሜቴክ ሁለት ያረጁ መርከቦችን ከኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርት እና ሎጂስቲክ አገልግሎት ኢንተርፕራይዝ በመግዛት በህገወጥ ንግድ፣ ምንአልባት በጦር መሳሪያ ንግድ፣ ተሰማርቶ እንደነበር ጠቁመዋል። ሁለቱ መርከቦች በእርጅና ምክንያት የአገልግሎት ዘመናቸው ያበቃ በመሆኑ የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ እያውለበለቡ በዓለም አቀፍ የባህር ንግድ መስመር መንቀሳቀስ አይችሉም። በመሆኑም እንደ አምባሳደር ሱሌማን አገላለፅ ሜቴክ በካሪቢን ደሴቶች ከሚገኙ ሀገራት ሰንደቅ ዓላማ ለመግዛት ሲንቀሳቀስ እንደነበር ጠቅሰዋል፡፡ በዚህ መሠረት ሜቴክ “ትሬንዳድ እና ቴቤጎ” ከተባለችው ሀገር ሰንደቅ ዓላማ በመግዛት በህገወጥ ንግድ ተግባር ሳይሰማራ እንዳልቀረ ጥርጣሬያቸውን መግለፃቸው ይታወሳል። ነገር ግን ሜቴክ ሰንደቅ ዓላማ ለመግዛት ከምስራቅ አፍሪካ ተነስቶ ካሪቢያን ደሴቶች ድረስ ለምን ሄደ? ይህን ጥያቄ ለመመለስ በቅድሚያ የካሪቢያን ደሴቶች ለምን የህገወጥ ንግድ እና የገንዘብ ዝውውር መዳረሻ እንደሆኑ ማወቅ ያስፈልጋል።

3) በፖስታ ሳጥን የሚገዛ ዜግነት እና የባንክ አካውንት

ትናንሽ የሆኑት የካሪቢያን ደሴቶች ኢኮኖሚ በቱሪዝምና በፋይናንስ ዘርፍ ላይ የተመሰረተ ነው። በመሆኑም አብዛኞቹ የካሪቢያን ደሴቶች ቱሪስቶችን ወደ ሀገራቸው ለመሳብ ከፍተኛ ጥረት ያደርጋሉ። በዚህ መሰረት ጎብኚዎች በሀገራቱ ለረጅም ግዜ እንዲቆዩ፣ በተደጋጋሚ ወደ ሀገሪቱ ተመላልሰው እንዲመጡ የዜግነት መታወቂያና የመኖሪያ ፍቃድ ማግኘት እጅግ በጣም ቀላል ነው። ለምሳሌ በአንድ የካሪቢያን ደሴት ዜግነት ለማግኘት በሀገሪቱ የፖስታ አገልግሎት ድርጅት ውስጥ አንድ የመልዕክት ሳጥን መግዛት ብቻ በቂ ነው። በደሴቱ ላይ እግሩ ያረፈ ሁሉ ወደ በፖስታ አገልግሎት ድርጅት በመሄድ የመልዕክት ሳጥን መግዛት ይችላል። ይህን የፖስታ ሳጥን ቁጥር በመጠቀም በሀገሪቱ በሚገኙ ባንኮች የራሱን የባንክ ሂሳብ ይከፍታል። ከዚያ በኋላ ወደመጣበት ሀገር ተመልሶ መሄድ ይችላል።

ስለዚህ አንድ ግዜ ወደ ካሪቢን ደሴቶች በሄደ የፖስታ ሳጥን የገዛ ግለሰብ የአገልግሎት ክፍያ በአግባቡ እስከከፈለ ድረስ የሀገሪቱ ዜጋ ሆኖ ይቀጥላል። ከዚህ በተጨማሪ በየትኛውም የዓለም ክፍል ሆኖ በካሪቢያን ባንኮች ውስጥ ያለውን ሂሳብ ማንቀሳቀስ ይችላል። ቀደም ሲል በተገለፀው መሰረት፣ ከተለያዩ የዓለም ሀገራት የመጡ ባለሃብቶች፣ የአደንዛዥ ዕፅ አዘዋዋሪዎች፣ በዘረፋና ሌብነት ተግባር የተሰማሩ የመንግስት ባለስልጣናትና ሌሎች በህገወጥ ተግባር የተሰማሩ ሰዎች ወደ ካሪያቢያን ደሴቶች የሚሄዱት በቀላሉ ዜግነት ለማግኘት እና የባንክ ሂሳብ ለመክፈት ነው። ከዚያ በኋላ በህገውጥ ንግድ እና ዘረፋ የጋበሱትን ገንዘብ ወደ እነዚህ ሀገራት ባንኮች ያሸሻሉ፣ እንዲሁም በትክክለኛው መንገድ ሰርተው ያገኙትን ገንዘብ ከሀገራቸው የታክስ መስሪያ ቤት በመደበቅ ታክስ ያጭበረብራሉ። የሜቴክ ደግሞ ከሁሉም የተለየ ነው።

4) የጠፋችው የኢትዮጵያ መርከብ ተገኘች!

ለኢትዮጵያ የመርከብ ድርጅት ቀረቤታ ያላቸው ሰዎች በሰጡኝ መረጃ መሰረት የደርግ መንግስት፤ ነፃነት፣ አንድነት፣ አብዮት እና መንግስቱ ኃይለማሪያም የተባሉ አራት መርከቦችን መግዛቱን ይገልፃሉ። የህወሓት/ኢህአዴግ መንግስት ወደ ስልጣን ከመጣ በኋላ “አብዮት” የተባለውን መርከብ “ህዳሴ” የሚል ስያሜ ሰጥቶታል። መንግስቱ ኃይለማሪያም የተባለውን መርከብ ደግሞ “የአባይ ወንዝ” ወይም በአጭሩ “አባይ” የሚል ስያሜ እንደሰጠው ይጠቀሳል። በመጨረሻም “ህዳሴ” እና “አባይ” የተባሉትን መርከቦች ሜቴክ ደግሞ “Padma” እና “Tika” የሚል ስያሜ በመስጠት በኮሞሮስ ባንዲራ ህገወጥ ንግድ ሲያከናውንባቸው እንደነበር ከላይ ተገልጿል።

የደርግ መንግስት የገዛው “ነፃነት” የተባለው መርከብ ያለበት ሁኔታ ለግዜው አልታወቀም። “አንድነት” የሚባለው መርከብ ግን “አንዲ” (ANDI) የሚል ስያሜ ተሰጥቶት “St. Kitts Nevis” በምትባል በጣም ትንሽ የካሪቢያን ደሴት ሰንደቅ ዓላማ ይዞ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል። ዓለም አቀፉን የባህር ትራንስፖርት ለመቆጣጠር የሚያገለግለው የMarinetraffic.com በተሰኘው ድረገፅ መሰረት “አንድነት” የተባለችው መርከብ ከአገልግሎት ውጪ ወይም የጠፋች መሆኑን ይገልፃል።

መርከቧ በባህር ትራንስፖርት ትራፊክ እይታ ውስጥ ገብታ የነበረው እ.አ.አ. በ2015 ዓ.ም እንደሆነ ተጠቅሷል። ሆኖም ግን መርከቧ እስካሁን ድረስ እንድትቆራረጥ አልተሸጠችም። በድረገፁ ላይ የመርከቧን እንቅስቃሴ ለመከታተል ባደረኩት ጥረት አሁንም ድረስ በህገወጥ የንግድ እንቅስቃሴ እንደሆነች ለመረዳት ችያለሁ። ከታች ያለው ምስል የአንድነት መርከብን እንቅስቃሴ በካርታ ያሳያል።

በዚህ መሰረት ከሜቴክ በተጨማሪ አንድነት የተባለች ሌላ የኢትዮጵያ መርከብ በመሬት ካርታ ላይ እንኳን በግልፅ በማትታይ “St. Kitts Nevis” የምትባል ትንሽዬ ሀገር ሰንደቅ ዓላማ በማውለብለብ በህገወጥ የንግድ እንቅስቃሴ እንደ ተሰማራ መገንዘብ ይቻላል።

Ethiopian Think Thank Group ስዩም ተሾመ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions, Politics Tagged With: andinet, Full Width Top, metec, Middle Column, ship, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule