• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ቱሪዝም ቢሮ የቀድሞ ውሳኔውን በመሻር ሎምባርዲያ የሚገኝበት ሕንፃ ቅርስ አይደለም አለ

September 3, 2014 04:34 pm by Editor Leave a Comment

የአዲስ አበባ ከተማ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ጥንታዊው የሼክ አህመድ ሳለህ አልዛህሪ (ሎምባርዲያ ሬስቶራንት የሚገኝበት) ሕንፃ ቅርስ መሆኑን በባለሙያዎች አረጋግጦ ክብካቤና ጥበቃ እንዲደረግለት ሲያሳስብ ቢቆይም፣ ሰሞኑን ባወጣው ሰርኩላር ሕንፃው ቅርስ አይደለም በማለት የቀድሞውን ውሳኔ ሽሯል፡፡

ቢሮው ታህሳስ 25 ቀን 2006 ዓ.ም. ለአዲስ አበባና ዙርያዋ ኦሮሚያ ልዩ ዞን የተቀናጀ የጋራ ልማት ፕላን ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ጽፎ በነበረው ደብዳቤ፣ ሕንፃው ቅርስ መሆኑን ገልጾ በማስተር ፕላኑ በቅርስነት እንዲያዝ አስታውቆ ነበር፡፡

ቢሮው በጻፈው ደብዳቤ ከፌዴራል ቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለሥልጣን፣ ከቅርስ ምዝገባ፣ ቁጥጥርና ደረጃ ማውጣት ዳይሬክቶሬትና ከቅርስ ጥገናና እንክብካቤ ዳይሬክቶሬት፣ እንዲሁም ከራሱ ቢሮ በተውጣጡ ባለሙያዎች በዝርዝር ተጠንቶ የቅርስ መሥፈርት እንደሚያሟላ መረጋገጡን አስታውቆ ነበር፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የኢትዮጵያ ቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለሥልጣን፣ ታህሳስ 17 ቀን 2006 ዓ.ም. በጻፈው ደብዳቤ የሕንፃውን ቅርስነት ያረጋገጠ መሆኑን ቢሮው ገልጾ፣ የማስተር ፕላን ጽሕፈት ቤቱ ሕንፃውን በቅርስነት እንዲያዝ ጠይቆ ነበር፡፡

በዚህ መሠረት የማስተር ፕላን ጽሕፈት ቤቱ እያዘጋጀ ባለው ማስተር ፕላን ላይ ሕንፃው ቅርስ ሆኖ እንዲመዘገብ አድርጓል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የአዲስ አበባ ከተማ ፕላን ኢንስቲትዩት በባህል ቢሮው ውሳኔ ላይ ተመሥርቶ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በሙሉ ሕንፃው ቅርስ መሆኑን አውቀው አስፈላጊው ጥበቃና እንክብካቤ እንዲያደርጉለት ማሳሰቢያ ሰጥቶ ነበር፡፡

ነገር ግን ከወራት ቆይታ በኋላ የከተማው ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ቀደም ሲል የደረሰበትን ውሳኔ በመሻር፣ ይህ ጥንታዊ ሕንፃ ቅርስ አለመሆኑን ጠቅሶ አዲስ ሰርኩላር ሰሞኑን አስተላልፏል፡፡

ቢሮው ለማስተር ፕላን ጽሕፈት ቤት፣ በግልባጭ ደግሞ ለከተማው መረጃ ፕላን ኢንስቲትዩት በላከው ደብዳቤ ሕንፃው ቅርስ በመሆኑ በማስተር ፕላኑ በቅርስነት እንዲመዘገብ መጠየቁን አስታውሷል፡፡ ነገር ግን ቢሮው፣ “በከተማችን እየተካሄደ ያለው ልማት መደናቀፍ የሌለበት በመሆኑና ሕንፃውም የቅርስነት መስፈርት የማያሟላ ስለሆነ በቅርስነት እንዳይመዘገብ የተወሰነ መሆኑን አውቃችሁ፣ እየተዘጋጀ ባለው ማስተር ፕላን ላይ በቅርስነት እንዳይመዘገብ፤” በማለት ጉዳዩን በጥልቀት መርምሮ የደረሰበት ነጥብ መሆኑን ገልጿል፡፡

በዚህ መነሻ የአዲስ አበባ ከተማ መሬት ልማትና ከተማ ማደስ ኤጀንሲ ይህን ሕንፃ ጨምሮ በአካባቢው የሚገኙ ልዩ ልዩ ግንባታዎችን በማንሳት፣ በ10.6 ሔክታር መሬት ላይ የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ለማካሄድ ዝግጅቱን አጠናቋል፡፡ የመሬት ልማትና ከተማ ማደስ ኤጀንሲ ለሪፖርተር በላከው መግለጫ፣ የባህልና ቱሪዝም ቢሮ ውሳኔ መነሻ በማድረግ ቦታውን ለማልማት መዘጋጀቱን አስታውቋል፡፡

“ይህንኑ ደብዳቤ መነሻ በማድረግ ለክፍለ ከተሞችና ለሚመለከታቸው አካላት እንዲያውቁት በማድረግ የመልሶ ማልማት ሥራው ቀጥሏል፤” በማለት ኤጀንሲው በመግለጫው አስታውቋል፡፡

የክፍለ ከተማው መሬት ልማትና ከተማ ማደስ ጽሕፈት ቤት ለሕንፃው ነዋሪዎች የሰጠው የመጨረሻ ቀነ ገደብ በመጠናቀቁ በሕንፃው ላይ የሚገኙ አብዛኛዎቹን ቤቶች አሽጓል፡፡ ነገር ግን በሕንፃው ላይ የሚገኙ ተከራዮችና የሼክ አህመድ ወራሾች ሕንፃው መፍረስ እንደሌለበት ብሎም እንዳይታሸግ ለማድረግ ወደ ፍርድ ቤት ሄደዋል፡፡ ሜክሲኮ አካባቢ ዋቢ ሸበሌ ሆቴል አጠገብ የሚገኘው የሼክ አህመድ ሕንፃ በ1926 ዓ.ም. ነው የተገነባው፡፡ (ምንጭ: ሪፖርተር)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule