• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ቱሪዝም ቢሮ የቀድሞ ውሳኔውን በመሻር ሎምባርዲያ የሚገኝበት ሕንፃ ቅርስ አይደለም አለ

September 3, 2014 04:34 pm by Editor Leave a Comment

የአዲስ አበባ ከተማ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ጥንታዊው የሼክ አህመድ ሳለህ አልዛህሪ (ሎምባርዲያ ሬስቶራንት የሚገኝበት) ሕንፃ ቅርስ መሆኑን በባለሙያዎች አረጋግጦ ክብካቤና ጥበቃ እንዲደረግለት ሲያሳስብ ቢቆይም፣ ሰሞኑን ባወጣው ሰርኩላር ሕንፃው ቅርስ አይደለም በማለት የቀድሞውን ውሳኔ ሽሯል፡፡

ቢሮው ታህሳስ 25 ቀን 2006 ዓ.ም. ለአዲስ አበባና ዙርያዋ ኦሮሚያ ልዩ ዞን የተቀናጀ የጋራ ልማት ፕላን ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ጽፎ በነበረው ደብዳቤ፣ ሕንፃው ቅርስ መሆኑን ገልጾ በማስተር ፕላኑ በቅርስነት እንዲያዝ አስታውቆ ነበር፡፡

ቢሮው በጻፈው ደብዳቤ ከፌዴራል ቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለሥልጣን፣ ከቅርስ ምዝገባ፣ ቁጥጥርና ደረጃ ማውጣት ዳይሬክቶሬትና ከቅርስ ጥገናና እንክብካቤ ዳይሬክቶሬት፣ እንዲሁም ከራሱ ቢሮ በተውጣጡ ባለሙያዎች በዝርዝር ተጠንቶ የቅርስ መሥፈርት እንደሚያሟላ መረጋገጡን አስታውቆ ነበር፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የኢትዮጵያ ቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለሥልጣን፣ ታህሳስ 17 ቀን 2006 ዓ.ም. በጻፈው ደብዳቤ የሕንፃውን ቅርስነት ያረጋገጠ መሆኑን ቢሮው ገልጾ፣ የማስተር ፕላን ጽሕፈት ቤቱ ሕንፃውን በቅርስነት እንዲያዝ ጠይቆ ነበር፡፡

በዚህ መሠረት የማስተር ፕላን ጽሕፈት ቤቱ እያዘጋጀ ባለው ማስተር ፕላን ላይ ሕንፃው ቅርስ ሆኖ እንዲመዘገብ አድርጓል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የአዲስ አበባ ከተማ ፕላን ኢንስቲትዩት በባህል ቢሮው ውሳኔ ላይ ተመሥርቶ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በሙሉ ሕንፃው ቅርስ መሆኑን አውቀው አስፈላጊው ጥበቃና እንክብካቤ እንዲያደርጉለት ማሳሰቢያ ሰጥቶ ነበር፡፡

ነገር ግን ከወራት ቆይታ በኋላ የከተማው ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ቀደም ሲል የደረሰበትን ውሳኔ በመሻር፣ ይህ ጥንታዊ ሕንፃ ቅርስ አለመሆኑን ጠቅሶ አዲስ ሰርኩላር ሰሞኑን አስተላልፏል፡፡

ቢሮው ለማስተር ፕላን ጽሕፈት ቤት፣ በግልባጭ ደግሞ ለከተማው መረጃ ፕላን ኢንስቲትዩት በላከው ደብዳቤ ሕንፃው ቅርስ በመሆኑ በማስተር ፕላኑ በቅርስነት እንዲመዘገብ መጠየቁን አስታውሷል፡፡ ነገር ግን ቢሮው፣ “በከተማችን እየተካሄደ ያለው ልማት መደናቀፍ የሌለበት በመሆኑና ሕንፃውም የቅርስነት መስፈርት የማያሟላ ስለሆነ በቅርስነት እንዳይመዘገብ የተወሰነ መሆኑን አውቃችሁ፣ እየተዘጋጀ ባለው ማስተር ፕላን ላይ በቅርስነት እንዳይመዘገብ፤” በማለት ጉዳዩን በጥልቀት መርምሮ የደረሰበት ነጥብ መሆኑን ገልጿል፡፡

በዚህ መነሻ የአዲስ አበባ ከተማ መሬት ልማትና ከተማ ማደስ ኤጀንሲ ይህን ሕንፃ ጨምሮ በአካባቢው የሚገኙ ልዩ ልዩ ግንባታዎችን በማንሳት፣ በ10.6 ሔክታር መሬት ላይ የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ለማካሄድ ዝግጅቱን አጠናቋል፡፡ የመሬት ልማትና ከተማ ማደስ ኤጀንሲ ለሪፖርተር በላከው መግለጫ፣ የባህልና ቱሪዝም ቢሮ ውሳኔ መነሻ በማድረግ ቦታውን ለማልማት መዘጋጀቱን አስታውቋል፡፡

“ይህንኑ ደብዳቤ መነሻ በማድረግ ለክፍለ ከተሞችና ለሚመለከታቸው አካላት እንዲያውቁት በማድረግ የመልሶ ማልማት ሥራው ቀጥሏል፤” በማለት ኤጀንሲው በመግለጫው አስታውቋል፡፡

የክፍለ ከተማው መሬት ልማትና ከተማ ማደስ ጽሕፈት ቤት ለሕንፃው ነዋሪዎች የሰጠው የመጨረሻ ቀነ ገደብ በመጠናቀቁ በሕንፃው ላይ የሚገኙ አብዛኛዎቹን ቤቶች አሽጓል፡፡ ነገር ግን በሕንፃው ላይ የሚገኙ ተከራዮችና የሼክ አህመድ ወራሾች ሕንፃው መፍረስ እንደሌለበት ብሎም እንዳይታሸግ ለማድረግ ወደ ፍርድ ቤት ሄደዋል፡፡ ሜክሲኮ አካባቢ ዋቢ ሸበሌ ሆቴል አጠገብ የሚገኘው የሼክ አህመድ ሕንፃ በ1926 ዓ.ም. ነው የተገነባው፡፡ (ምንጭ: ሪፖርተር)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule