• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ቱሪዝም ቢሮ የቀድሞ ውሳኔውን በመሻር ሎምባርዲያ የሚገኝበት ሕንፃ ቅርስ አይደለም አለ

September 3, 2014 04:34 pm by Editor Leave a Comment

የአዲስ አበባ ከተማ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ጥንታዊው የሼክ አህመድ ሳለህ አልዛህሪ (ሎምባርዲያ ሬስቶራንት የሚገኝበት) ሕንፃ ቅርስ መሆኑን በባለሙያዎች አረጋግጦ ክብካቤና ጥበቃ እንዲደረግለት ሲያሳስብ ቢቆይም፣ ሰሞኑን ባወጣው ሰርኩላር ሕንፃው ቅርስ አይደለም በማለት የቀድሞውን ውሳኔ ሽሯል፡፡

ቢሮው ታህሳስ 25 ቀን 2006 ዓ.ም. ለአዲስ አበባና ዙርያዋ ኦሮሚያ ልዩ ዞን የተቀናጀ የጋራ ልማት ፕላን ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ጽፎ በነበረው ደብዳቤ፣ ሕንፃው ቅርስ መሆኑን ገልጾ በማስተር ፕላኑ በቅርስነት እንዲያዝ አስታውቆ ነበር፡፡

ቢሮው በጻፈው ደብዳቤ ከፌዴራል ቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለሥልጣን፣ ከቅርስ ምዝገባ፣ ቁጥጥርና ደረጃ ማውጣት ዳይሬክቶሬትና ከቅርስ ጥገናና እንክብካቤ ዳይሬክቶሬት፣ እንዲሁም ከራሱ ቢሮ በተውጣጡ ባለሙያዎች በዝርዝር ተጠንቶ የቅርስ መሥፈርት እንደሚያሟላ መረጋገጡን አስታውቆ ነበር፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የኢትዮጵያ ቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለሥልጣን፣ ታህሳስ 17 ቀን 2006 ዓ.ም. በጻፈው ደብዳቤ የሕንፃውን ቅርስነት ያረጋገጠ መሆኑን ቢሮው ገልጾ፣ የማስተር ፕላን ጽሕፈት ቤቱ ሕንፃውን በቅርስነት እንዲያዝ ጠይቆ ነበር፡፡

በዚህ መሠረት የማስተር ፕላን ጽሕፈት ቤቱ እያዘጋጀ ባለው ማስተር ፕላን ላይ ሕንፃው ቅርስ ሆኖ እንዲመዘገብ አድርጓል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የአዲስ አበባ ከተማ ፕላን ኢንስቲትዩት በባህል ቢሮው ውሳኔ ላይ ተመሥርቶ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በሙሉ ሕንፃው ቅርስ መሆኑን አውቀው አስፈላጊው ጥበቃና እንክብካቤ እንዲያደርጉለት ማሳሰቢያ ሰጥቶ ነበር፡፡

ነገር ግን ከወራት ቆይታ በኋላ የከተማው ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ቀደም ሲል የደረሰበትን ውሳኔ በመሻር፣ ይህ ጥንታዊ ሕንፃ ቅርስ አለመሆኑን ጠቅሶ አዲስ ሰርኩላር ሰሞኑን አስተላልፏል፡፡

ቢሮው ለማስተር ፕላን ጽሕፈት ቤት፣ በግልባጭ ደግሞ ለከተማው መረጃ ፕላን ኢንስቲትዩት በላከው ደብዳቤ ሕንፃው ቅርስ በመሆኑ በማስተር ፕላኑ በቅርስነት እንዲመዘገብ መጠየቁን አስታውሷል፡፡ ነገር ግን ቢሮው፣ “በከተማችን እየተካሄደ ያለው ልማት መደናቀፍ የሌለበት በመሆኑና ሕንፃውም የቅርስነት መስፈርት የማያሟላ ስለሆነ በቅርስነት እንዳይመዘገብ የተወሰነ መሆኑን አውቃችሁ፣ እየተዘጋጀ ባለው ማስተር ፕላን ላይ በቅርስነት እንዳይመዘገብ፤” በማለት ጉዳዩን በጥልቀት መርምሮ የደረሰበት ነጥብ መሆኑን ገልጿል፡፡

በዚህ መነሻ የአዲስ አበባ ከተማ መሬት ልማትና ከተማ ማደስ ኤጀንሲ ይህን ሕንፃ ጨምሮ በአካባቢው የሚገኙ ልዩ ልዩ ግንባታዎችን በማንሳት፣ በ10.6 ሔክታር መሬት ላይ የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ለማካሄድ ዝግጅቱን አጠናቋል፡፡ የመሬት ልማትና ከተማ ማደስ ኤጀንሲ ለሪፖርተር በላከው መግለጫ፣ የባህልና ቱሪዝም ቢሮ ውሳኔ መነሻ በማድረግ ቦታውን ለማልማት መዘጋጀቱን አስታውቋል፡፡

“ይህንኑ ደብዳቤ መነሻ በማድረግ ለክፍለ ከተሞችና ለሚመለከታቸው አካላት እንዲያውቁት በማድረግ የመልሶ ማልማት ሥራው ቀጥሏል፤” በማለት ኤጀንሲው በመግለጫው አስታውቋል፡፡

የክፍለ ከተማው መሬት ልማትና ከተማ ማደስ ጽሕፈት ቤት ለሕንፃው ነዋሪዎች የሰጠው የመጨረሻ ቀነ ገደብ በመጠናቀቁ በሕንፃው ላይ የሚገኙ አብዛኛዎቹን ቤቶች አሽጓል፡፡ ነገር ግን በሕንፃው ላይ የሚገኙ ተከራዮችና የሼክ አህመድ ወራሾች ሕንፃው መፍረስ እንደሌለበት ብሎም እንዳይታሸግ ለማድረግ ወደ ፍርድ ቤት ሄደዋል፡፡ ሜክሲኮ አካባቢ ዋቢ ሸበሌ ሆቴል አጠገብ የሚገኘው የሼክ አህመድ ሕንፃ በ1926 ዓ.ም. ነው የተገነባው፡፡ (ምንጭ: ሪፖርተር)

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
Copyright © 2026 · Goolgule