• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የመጨረሻዋ ጥይት” የወያነ ጣት ከምላጩ ላይ!!

February 23, 2018 10:55 am by Editor Leave a Comment

ያልተጠበቀ ባይሆንም እንዲህ ተጣድፎ የሚጠፋበትን ፈንጂ ለመርገጥ ማሰቢያ ያጣል ብየ አልገመትኩም ነበር፤ ግን ሆነ፤ ወያኔ የቀረችውን የመጨረሻ ጥይት ለመተኮስ ሌባ ጣቱን ምላጩ ላይ አስረግጧል። ቀድሞም ከቦታ ጠባቂነት የዘለለ ድርሻ ያልነበራቸውን ጠቅላይ ሚንስትር ገፋ አድርጎ በትረስልጣኑን የነጠቀው ወራሪው የወያኔ ጦር መሪዎች ቡድን እንደ ዘመነ መሳፍንቱ ሚካኤል ስሁል የፈቀደውን ሊያነግስ የጠላውን ሊያወርድ ከምንይልክ ቤተ መንግስት ገብቷል።

ቀድሞውንም በራሱ በፈጣሪው የተናቀውና የተናደው የይስሙላ “ህገ መንግስት “ ተብየ ባዶ ሰነድ ሙሉ በሙሉ በጠመንጃ ነካሾቹ የሰራዊት መሪዎች በፈረሰበት አገር የወያኔ ሰራዊት የሚከላከለው ሰነድ ሳይኖረው ቤት መንግስቱን መውረሩ የመሪዎቹን የዘረፋ ንብረት ከመከላከል የዘለለ ህዝባዊ ተለዕኮ የለውም።

በፈረሰና ህልውና በሌለው ሚንስትሮች ምክር ቤት ስም “ያስቸኳይ ጊዜ አዋጅ” በሚል አምባገነናዊና ፋሽስታዊ አዋጅ አገሪቷ ሙሉ በሙሉ በወያነ ሰራዊት መዳፍ ስር ስትወድቅ ከምስለ ሰውነት የዘለለ ነፍስ የሌለው ፓርላማ ተብዬ ጉድ ፤ አንዳች ማለት አለመቻሉ የይስሙላውም ህገ መንግስት ግባተ መሬት መፈጸሙን በይፋ በማብሰር የጥፋቷ የመጨረሻ ቀለህ መቀባበሏንም አረጋግጦልናል።

ስለዚህ የሚጠብቁትም፤ የሚከላከሉለትም ህግና መንግስት በሌለበት ከተሸከሙት ጠብመንጃ ውጭ ህጋዊም ሆነ ህዝባዊ መሰረት የሌላቸው ወራሪ ወያኔዎች በመጭው ጊዜ ባንቀልባቸው አዝለው የሚያሾሩት “ጠቅላይ ሚንስትር” የሚባል አፈ-ወያነ ሊሰጡን ወይም ሙልጭ ብለው በለመደው ፈጣጣ አይናቸው እንደለመዱት በጠመንጃቸው ሊነዱን እያመቻቹን ነው።

ጨርሶ ያልገባቸው ወይም ፈቅደው ሊቀበሉት ያልቻሉት ፍርሀትን በሞት ጥሶ የወጣ ሁልቆ መሳፍርት ኢትዮጵያዊ ከፊታቸው እየጠበቃቸው መሆኑን ነው። ስለዚህ ጉልበተኞቹ የኢትዮጵያን ህዝብ በሌለና በፈራረሰ ህግና መንግስት ስም የሚያስፈራሩበት የህግም ሆነ የሞራል ብቃት ሊኖራቸው አይችልም፤ ራሳቸው ህገ-ወጥ ናቸውና።

ይልቁንስ የዘመናችን “ስሁሎች” ሊረዱት የሚገባቸው እውነት ከዚህ በኋላ የኢትዮጵያ እጣ ሳይሆን የወያነ እጣ የሚወሰነው በጉልበታቸው ወንበር ላይ በሚሰቅሉት “ጠቅላይ ሚንስትር” አንደበትና ድርጊት መሆኑን ነው። እንደ እስከዛሬው በፈራረሰና በማይሰራ ህገ-መንግስት ስም እያሳበቡ ኮርኩመውና ሸብበው ሲረግጡትና ሲመዘብሩት የነበረው ህዝብ ግርዶሹን ጥሶ ፍርህቱን አራግፎ የነጻነት ጎዳና ላይ መግባቱን እየጎፈነናቸውም ቢሆን መቀበል ነው። ያሻቸውን እየሾሙና እየሻሩ በህዝብ ቁስል እንጨት እየሰነቀሩ በሞቱ እያላገጡ መቀጠል ፈጽሞ እንዳበቃለት መረዳት ከተሳናቸው ሊስቧት በተዘጋጁት የመጨረሻ ጥይት ቀለህ የጣፈንታቸውን መራራ ጽዋ ለመጎንጨት ተዘጋጅተዋል ማለት ነው።

ማንም ይሁን ማን በባለነፍጦቹ ወያኔዎች የሚሾመው “ጠቅላይ ሚንስትር” ህጋዊ መሰረት የሌለው መሆኑን ተገንዝቦ በበዓለ ሲመቱ በሚያደርገው ንግግር “የኢትዮጵያ ህዝብ የጠየቀውን የስርዓት ለውጥ ጥያቄ የሚያስተናግድ ብሄራዊ እርቅና ሁሉን አቀፍ የሽግግር መንግስት ጥሪ በድፍረት በማድረግ ራሱን ከምስለ-ሰውነት የዘለለ ባይምሮው የሚመራ ሰው መሆኑን እንደሚያሳየን ተስፋ እናድርግ። ካንደበቱ የሚውጡት ቃላቶችም መጭውን የኢትዮጵያ ህዝቦች የትግል አቅጣጫና የወያነን የመጨረሻ ጥይት መዳረሻ እንደሚያመላክቱ ልብ ሊለው ይገባል!!

ጌዲዮን በቀለ (Gedionbe56@yahoo.com)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule