• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የመጨረሻዋ ጥይት” የወያነ ጣት ከምላጩ ላይ!!

February 23, 2018 10:55 am by Editor Leave a Comment

ያልተጠበቀ ባይሆንም እንዲህ ተጣድፎ የሚጠፋበትን ፈንጂ ለመርገጥ ማሰቢያ ያጣል ብየ አልገመትኩም ነበር፤ ግን ሆነ፤ ወያኔ የቀረችውን የመጨረሻ ጥይት ለመተኮስ ሌባ ጣቱን ምላጩ ላይ አስረግጧል። ቀድሞም ከቦታ ጠባቂነት የዘለለ ድርሻ ያልነበራቸውን ጠቅላይ ሚንስትር ገፋ አድርጎ በትረስልጣኑን የነጠቀው ወራሪው የወያኔ ጦር መሪዎች ቡድን እንደ ዘመነ መሳፍንቱ ሚካኤል ስሁል የፈቀደውን ሊያነግስ የጠላውን ሊያወርድ ከምንይልክ ቤተ መንግስት ገብቷል።

ቀድሞውንም በራሱ በፈጣሪው የተናቀውና የተናደው የይስሙላ “ህገ መንግስት “ ተብየ ባዶ ሰነድ ሙሉ በሙሉ በጠመንጃ ነካሾቹ የሰራዊት መሪዎች በፈረሰበት አገር የወያኔ ሰራዊት የሚከላከለው ሰነድ ሳይኖረው ቤት መንግስቱን መውረሩ የመሪዎቹን የዘረፋ ንብረት ከመከላከል የዘለለ ህዝባዊ ተለዕኮ የለውም።

በፈረሰና ህልውና በሌለው ሚንስትሮች ምክር ቤት ስም “ያስቸኳይ ጊዜ አዋጅ” በሚል አምባገነናዊና ፋሽስታዊ አዋጅ አገሪቷ ሙሉ በሙሉ በወያነ ሰራዊት መዳፍ ስር ስትወድቅ ከምስለ ሰውነት የዘለለ ነፍስ የሌለው ፓርላማ ተብዬ ጉድ ፤ አንዳች ማለት አለመቻሉ የይስሙላውም ህገ መንግስት ግባተ መሬት መፈጸሙን በይፋ በማብሰር የጥፋቷ የመጨረሻ ቀለህ መቀባበሏንም አረጋግጦልናል።

ስለዚህ የሚጠብቁትም፤ የሚከላከሉለትም ህግና መንግስት በሌለበት ከተሸከሙት ጠብመንጃ ውጭ ህጋዊም ሆነ ህዝባዊ መሰረት የሌላቸው ወራሪ ወያኔዎች በመጭው ጊዜ ባንቀልባቸው አዝለው የሚያሾሩት “ጠቅላይ ሚንስትር” የሚባል አፈ-ወያነ ሊሰጡን ወይም ሙልጭ ብለው በለመደው ፈጣጣ አይናቸው እንደለመዱት በጠመንጃቸው ሊነዱን እያመቻቹን ነው።

ጨርሶ ያልገባቸው ወይም ፈቅደው ሊቀበሉት ያልቻሉት ፍርሀትን በሞት ጥሶ የወጣ ሁልቆ መሳፍርት ኢትዮጵያዊ ከፊታቸው እየጠበቃቸው መሆኑን ነው። ስለዚህ ጉልበተኞቹ የኢትዮጵያን ህዝብ በሌለና በፈራረሰ ህግና መንግስት ስም የሚያስፈራሩበት የህግም ሆነ የሞራል ብቃት ሊኖራቸው አይችልም፤ ራሳቸው ህገ-ወጥ ናቸውና።

ይልቁንስ የዘመናችን “ስሁሎች” ሊረዱት የሚገባቸው እውነት ከዚህ በኋላ የኢትዮጵያ እጣ ሳይሆን የወያነ እጣ የሚወሰነው በጉልበታቸው ወንበር ላይ በሚሰቅሉት “ጠቅላይ ሚንስትር” አንደበትና ድርጊት መሆኑን ነው። እንደ እስከዛሬው በፈራረሰና በማይሰራ ህገ-መንግስት ስም እያሳበቡ ኮርኩመውና ሸብበው ሲረግጡትና ሲመዘብሩት የነበረው ህዝብ ግርዶሹን ጥሶ ፍርህቱን አራግፎ የነጻነት ጎዳና ላይ መግባቱን እየጎፈነናቸውም ቢሆን መቀበል ነው። ያሻቸውን እየሾሙና እየሻሩ በህዝብ ቁስል እንጨት እየሰነቀሩ በሞቱ እያላገጡ መቀጠል ፈጽሞ እንዳበቃለት መረዳት ከተሳናቸው ሊስቧት በተዘጋጁት የመጨረሻ ጥይት ቀለህ የጣፈንታቸውን መራራ ጽዋ ለመጎንጨት ተዘጋጅተዋል ማለት ነው።

ማንም ይሁን ማን በባለነፍጦቹ ወያኔዎች የሚሾመው “ጠቅላይ ሚንስትር” ህጋዊ መሰረት የሌለው መሆኑን ተገንዝቦ በበዓለ ሲመቱ በሚያደርገው ንግግር “የኢትዮጵያ ህዝብ የጠየቀውን የስርዓት ለውጥ ጥያቄ የሚያስተናግድ ብሄራዊ እርቅና ሁሉን አቀፍ የሽግግር መንግስት ጥሪ በድፍረት በማድረግ ራሱን ከምስለ-ሰውነት የዘለለ ባይምሮው የሚመራ ሰው መሆኑን እንደሚያሳየን ተስፋ እናድርግ። ካንደበቱ የሚውጡት ቃላቶችም መጭውን የኢትዮጵያ ህዝቦች የትግል አቅጣጫና የወያነን የመጨረሻ ጥይት መዳረሻ እንደሚያመላክቱ ልብ ሊለው ይገባል!!

ጌዲዮን በቀለ (Gedionbe56@yahoo.com)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule