• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የመጨረሻዋ ጥይት” የወያነ ጣት ከምላጩ ላይ!!

February 23, 2018 10:55 am by Editor Leave a Comment

ያልተጠበቀ ባይሆንም እንዲህ ተጣድፎ የሚጠፋበትን ፈንጂ ለመርገጥ ማሰቢያ ያጣል ብየ አልገመትኩም ነበር፤ ግን ሆነ፤ ወያኔ የቀረችውን የመጨረሻ ጥይት ለመተኮስ ሌባ ጣቱን ምላጩ ላይ አስረግጧል። ቀድሞም ከቦታ ጠባቂነት የዘለለ ድርሻ ያልነበራቸውን ጠቅላይ ሚንስትር ገፋ አድርጎ በትረስልጣኑን የነጠቀው ወራሪው የወያኔ ጦር መሪዎች ቡድን እንደ ዘመነ መሳፍንቱ ሚካኤል ስሁል የፈቀደውን ሊያነግስ የጠላውን ሊያወርድ ከምንይልክ ቤተ መንግስት ገብቷል።

ቀድሞውንም በራሱ በፈጣሪው የተናቀውና የተናደው የይስሙላ “ህገ መንግስት “ ተብየ ባዶ ሰነድ ሙሉ በሙሉ በጠመንጃ ነካሾቹ የሰራዊት መሪዎች በፈረሰበት አገር የወያኔ ሰራዊት የሚከላከለው ሰነድ ሳይኖረው ቤት መንግስቱን መውረሩ የመሪዎቹን የዘረፋ ንብረት ከመከላከል የዘለለ ህዝባዊ ተለዕኮ የለውም።

በፈረሰና ህልውና በሌለው ሚንስትሮች ምክር ቤት ስም “ያስቸኳይ ጊዜ አዋጅ” በሚል አምባገነናዊና ፋሽስታዊ አዋጅ አገሪቷ ሙሉ በሙሉ በወያነ ሰራዊት መዳፍ ስር ስትወድቅ ከምስለ ሰውነት የዘለለ ነፍስ የሌለው ፓርላማ ተብዬ ጉድ ፤ አንዳች ማለት አለመቻሉ የይስሙላውም ህገ መንግስት ግባተ መሬት መፈጸሙን በይፋ በማብሰር የጥፋቷ የመጨረሻ ቀለህ መቀባበሏንም አረጋግጦልናል።

ስለዚህ የሚጠብቁትም፤ የሚከላከሉለትም ህግና መንግስት በሌለበት ከተሸከሙት ጠብመንጃ ውጭ ህጋዊም ሆነ ህዝባዊ መሰረት የሌላቸው ወራሪ ወያኔዎች በመጭው ጊዜ ባንቀልባቸው አዝለው የሚያሾሩት “ጠቅላይ ሚንስትር” የሚባል አፈ-ወያነ ሊሰጡን ወይም ሙልጭ ብለው በለመደው ፈጣጣ አይናቸው እንደለመዱት በጠመንጃቸው ሊነዱን እያመቻቹን ነው።

ጨርሶ ያልገባቸው ወይም ፈቅደው ሊቀበሉት ያልቻሉት ፍርሀትን በሞት ጥሶ የወጣ ሁልቆ መሳፍርት ኢትዮጵያዊ ከፊታቸው እየጠበቃቸው መሆኑን ነው። ስለዚህ ጉልበተኞቹ የኢትዮጵያን ህዝብ በሌለና በፈራረሰ ህግና መንግስት ስም የሚያስፈራሩበት የህግም ሆነ የሞራል ብቃት ሊኖራቸው አይችልም፤ ራሳቸው ህገ-ወጥ ናቸውና።

ይልቁንስ የዘመናችን “ስሁሎች” ሊረዱት የሚገባቸው እውነት ከዚህ በኋላ የኢትዮጵያ እጣ ሳይሆን የወያነ እጣ የሚወሰነው በጉልበታቸው ወንበር ላይ በሚሰቅሉት “ጠቅላይ ሚንስትር” አንደበትና ድርጊት መሆኑን ነው። እንደ እስከዛሬው በፈራረሰና በማይሰራ ህገ-መንግስት ስም እያሳበቡ ኮርኩመውና ሸብበው ሲረግጡትና ሲመዘብሩት የነበረው ህዝብ ግርዶሹን ጥሶ ፍርህቱን አራግፎ የነጻነት ጎዳና ላይ መግባቱን እየጎፈነናቸውም ቢሆን መቀበል ነው። ያሻቸውን እየሾሙና እየሻሩ በህዝብ ቁስል እንጨት እየሰነቀሩ በሞቱ እያላገጡ መቀጠል ፈጽሞ እንዳበቃለት መረዳት ከተሳናቸው ሊስቧት በተዘጋጁት የመጨረሻ ጥይት ቀለህ የጣፈንታቸውን መራራ ጽዋ ለመጎንጨት ተዘጋጅተዋል ማለት ነው።

ማንም ይሁን ማን በባለነፍጦቹ ወያኔዎች የሚሾመው “ጠቅላይ ሚንስትር” ህጋዊ መሰረት የሌለው መሆኑን ተገንዝቦ በበዓለ ሲመቱ በሚያደርገው ንግግር “የኢትዮጵያ ህዝብ የጠየቀውን የስርዓት ለውጥ ጥያቄ የሚያስተናግድ ብሄራዊ እርቅና ሁሉን አቀፍ የሽግግር መንግስት ጥሪ በድፍረት በማድረግ ራሱን ከምስለ-ሰውነት የዘለለ ባይምሮው የሚመራ ሰው መሆኑን እንደሚያሳየን ተስፋ እናድርግ። ካንደበቱ የሚውጡት ቃላቶችም መጭውን የኢትዮጵያ ህዝቦች የትግል አቅጣጫና የወያነን የመጨረሻ ጥይት መዳረሻ እንደሚያመላክቱ ልብ ሊለው ይገባል!!

ጌዲዮን በቀለ (Gedionbe56@yahoo.com)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am
  • የኦነግ ሸኔ አባላትን ዕድሜ ለማሳጠር የጂፒኤስ ቴክኖሎጂ ጥቅም ላይ እየዋለ ነው December 7, 2020 12:38 am
  • የቆሰሉ ወታደሮች በጠቅላይ ሚኒስትሩ ተጎበኙ December 6, 2020 11:41 pm
  • “ከዚህ በኋላ ይዘን እንታገላለን እንጂ ሠጥተን አንጠይቅም” ኮሎኔል ደመቀ December 2, 2020 12:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule