• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የመጨረሻዋ ጥይት” የወያነ ጣት ከምላጩ ላይ!!

February 23, 2018 10:55 am by Editor Leave a Comment

ያልተጠበቀ ባይሆንም እንዲህ ተጣድፎ የሚጠፋበትን ፈንጂ ለመርገጥ ማሰቢያ ያጣል ብየ አልገመትኩም ነበር፤ ግን ሆነ፤ ወያኔ የቀረችውን የመጨረሻ ጥይት ለመተኮስ ሌባ ጣቱን ምላጩ ላይ አስረግጧል። ቀድሞም ከቦታ ጠባቂነት የዘለለ ድርሻ ያልነበራቸውን ጠቅላይ ሚንስትር ገፋ አድርጎ በትረስልጣኑን የነጠቀው ወራሪው የወያኔ ጦር መሪዎች ቡድን እንደ ዘመነ መሳፍንቱ ሚካኤል ስሁል የፈቀደውን ሊያነግስ የጠላውን ሊያወርድ ከምንይልክ ቤተ መንግስት ገብቷል።

ቀድሞውንም በራሱ በፈጣሪው የተናቀውና የተናደው የይስሙላ “ህገ መንግስት “ ተብየ ባዶ ሰነድ ሙሉ በሙሉ በጠመንጃ ነካሾቹ የሰራዊት መሪዎች በፈረሰበት አገር የወያኔ ሰራዊት የሚከላከለው ሰነድ ሳይኖረው ቤት መንግስቱን መውረሩ የመሪዎቹን የዘረፋ ንብረት ከመከላከል የዘለለ ህዝባዊ ተለዕኮ የለውም።

በፈረሰና ህልውና በሌለው ሚንስትሮች ምክር ቤት ስም “ያስቸኳይ ጊዜ አዋጅ” በሚል አምባገነናዊና ፋሽስታዊ አዋጅ አገሪቷ ሙሉ በሙሉ በወያነ ሰራዊት መዳፍ ስር ስትወድቅ ከምስለ ሰውነት የዘለለ ነፍስ የሌለው ፓርላማ ተብዬ ጉድ ፤ አንዳች ማለት አለመቻሉ የይስሙላውም ህገ መንግስት ግባተ መሬት መፈጸሙን በይፋ በማብሰር የጥፋቷ የመጨረሻ ቀለህ መቀባበሏንም አረጋግጦልናል።

ስለዚህ የሚጠብቁትም፤ የሚከላከሉለትም ህግና መንግስት በሌለበት ከተሸከሙት ጠብመንጃ ውጭ ህጋዊም ሆነ ህዝባዊ መሰረት የሌላቸው ወራሪ ወያኔዎች በመጭው ጊዜ ባንቀልባቸው አዝለው የሚያሾሩት “ጠቅላይ ሚንስትር” የሚባል አፈ-ወያነ ሊሰጡን ወይም ሙልጭ ብለው በለመደው ፈጣጣ አይናቸው እንደለመዱት በጠመንጃቸው ሊነዱን እያመቻቹን ነው።

ጨርሶ ያልገባቸው ወይም ፈቅደው ሊቀበሉት ያልቻሉት ፍርሀትን በሞት ጥሶ የወጣ ሁልቆ መሳፍርት ኢትዮጵያዊ ከፊታቸው እየጠበቃቸው መሆኑን ነው። ስለዚህ ጉልበተኞቹ የኢትዮጵያን ህዝብ በሌለና በፈራረሰ ህግና መንግስት ስም የሚያስፈራሩበት የህግም ሆነ የሞራል ብቃት ሊኖራቸው አይችልም፤ ራሳቸው ህገ-ወጥ ናቸውና።

ይልቁንስ የዘመናችን “ስሁሎች” ሊረዱት የሚገባቸው እውነት ከዚህ በኋላ የኢትዮጵያ እጣ ሳይሆን የወያነ እጣ የሚወሰነው በጉልበታቸው ወንበር ላይ በሚሰቅሉት “ጠቅላይ ሚንስትር” አንደበትና ድርጊት መሆኑን ነው። እንደ እስከዛሬው በፈራረሰና በማይሰራ ህገ-መንግስት ስም እያሳበቡ ኮርኩመውና ሸብበው ሲረግጡትና ሲመዘብሩት የነበረው ህዝብ ግርዶሹን ጥሶ ፍርህቱን አራግፎ የነጻነት ጎዳና ላይ መግባቱን እየጎፈነናቸውም ቢሆን መቀበል ነው። ያሻቸውን እየሾሙና እየሻሩ በህዝብ ቁስል እንጨት እየሰነቀሩ በሞቱ እያላገጡ መቀጠል ፈጽሞ እንዳበቃለት መረዳት ከተሳናቸው ሊስቧት በተዘጋጁት የመጨረሻ ጥይት ቀለህ የጣፈንታቸውን መራራ ጽዋ ለመጎንጨት ተዘጋጅተዋል ማለት ነው።

ማንም ይሁን ማን በባለነፍጦቹ ወያኔዎች የሚሾመው “ጠቅላይ ሚንስትር” ህጋዊ መሰረት የሌለው መሆኑን ተገንዝቦ በበዓለ ሲመቱ በሚያደርገው ንግግር “የኢትዮጵያ ህዝብ የጠየቀውን የስርዓት ለውጥ ጥያቄ የሚያስተናግድ ብሄራዊ እርቅና ሁሉን አቀፍ የሽግግር መንግስት ጥሪ በድፍረት በማድረግ ራሱን ከምስለ-ሰውነት የዘለለ ባይምሮው የሚመራ ሰው መሆኑን እንደሚያሳየን ተስፋ እናድርግ። ካንደበቱ የሚውጡት ቃላቶችም መጭውን የኢትዮጵያ ህዝቦች የትግል አቅጣጫና የወያነን የመጨረሻ ጥይት መዳረሻ እንደሚያመላክቱ ልብ ሊለው ይገባል!!

ጌዲዮን በቀለ (Gedionbe56@yahoo.com)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule