• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የነፍስ ስደተኞች (the immigrants of survival)

November 16, 2013 12:56 am by Editor Leave a Comment

ባገሩ የሚኮራ ፤ ሀገሩን አፍቃሪ

ለወገን ሟች ስፍሱፍ ፤ አብሮነት ዘማሪ

የነፍስ ስደተኛ ፤ እውነት አስመስካሪ

የሀገሩ ነገር ፤ የወገኑ እጣ

ሁሌ የሚያስጨንቀው ፤ ሲበዛ ግፍ ጣጣ

ስለተገለለ ፤ አማራጭ ስላጣ

እኛን ካልሆንክ ተብሎ ፤ ሕሊናው ተሸጣ

ደሞ ስለተገፋ ፤ ታይቶ እንደ ባላንጣ

አላፈናፍን ተብሎ ፤ ጅቡ እየተቆጣ

አላቃምስ ተብሎ ፤ በራብ እየተቀጣ

ወገን ሲለይበት ፤ ሆኖ ዘር መረጣ

ቢብሰው ተነሣ ፤ ለስደት ጎረፈ

ከሞት ጋር ተፋጦ ፤ ሞትን እያለፈ

ግፍ እየተጋተ ፤ እየተቀሰፈ

ገና ባልጸናለት ፤ በጨቅላ ትከሻ

ስንት ስቃይ ዐየ ፤ የጣር መጨረሻ

ወገኑን እያጣ ፤ የዓሣ ሲሳይ ሆኖ

በአራዊት ተበልቶ ፤ በድንገት ታድኖ

ስለተደፈረ ፤ እራሱን ኮንኖ

በራብ በውኃ ጥም ፤ እየቀረ ደብኖ

በኢሰብአዊ ግፍ ፤ በአውሬ አረመኔ

ለኩላሊት ልቡ ፤ ታርዶ በጭካኔ

ከዚህ የተረፈው ፤ ሲደርስ ያ ወገኔ

ከገባበት ሀገር ፤ ተአምር እያስጻፈ

ጎኑን ሳያሳርፍ ፤ ሳይዝ የተረፈ

አንቀው ሊመልሱት ፤ እየተጠረፈ

ባዶ እጁን ሊጥሉት ፤ እየተገፈፈ

ሊይዙት ሲያሳዱት ፤ ሲሮጥ እየከነፈ

ሀገር እንደጠላ ፤ እንደተጸየፈ

መመለስን ጠልቶ ፤ ዋ! ተንገፈገፈ

ወደ ሲዖል ባሕር ፤ እንደሚጣል ቆጥሮ

ለማምለጥ ሲሯሯጥ ፤ በነፍሴ አውጭኝ በሮ

ከገሃነም ጭፍራ ፤ ጽድቅ ከጨነገፈ

ትናንትን ከረሳ ፤ ነገን ካከሸፈ

ሊያመልጥ ሲበረግግ ፤ ዋ! ተንዘፈዘፈ

መንገድ ላይ ወደቀ ፤ ተደነቃቀፈ

በእሳት ጥይት አረር ፤ እየተገረፈ

የሞት ስደተኛው ፤ እየሮጠ ዐረፈ

ስንትን ሞት ተሻግሮ ፤ ሊያልፍለት አለፈ

ባዶ እጀን አልሄድም ፤ ቃሌ ካልሠመረ

አላሳፍራትም ፤ ብሎ እንደፎከረ

በናፍቆት ተቆልቶ ፤ ፍቅሯን እያዜመ

ተደፍቶ ቀረላት ፤ አስከሬን ተመመ

የሚታደግ አጥቶ ፤ ታፋሪ ተፈሪ

የኛ ብሎ የሚለው ፤ መንግሥት ተቆርቋሪ ፡፡

ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው
ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው

ሀገር እርምሽን አውጭ ፤ ይብቃሽ ይቅር ምጡ

እናት አባት ወገን ፤ ሐዘን ተቀመጡ

ሳተና ልጆችሽ ፤ የአንችን ቀን ሊያመጡ

መልሰው ላያዩሽ ፤ ቀሩ እንደወጡ  ፡፡

ኅዳር 3 / 2006 ዓ.ም.

amsalugkidan@gmail.com

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Literature

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “የገቡበት ገብተን አንድ ሰው አናስቀርም – በተለይ አመራሩን” ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ February 15, 2021 11:46 pm
  • የትግራይ ገበሬና የከተማ ነዋሪ በሠራዊታችን ላይ አንድ ጥይት አልተኮሰም – ሪር አድሚራል ክንዱ February 4, 2021 01:51 pm
  • ኢንተርፖል፤ የህወሃት ሳምሪዎች የማይካድራ ጭፍጭፋ ከቦኮሃራም የከፋ ነው February 4, 2021 11:10 am
  • ጄኔራሎች “ተገድለዋል” በሚል የሀሰት መረጃ ሲያሰራጭ የነበረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ February 4, 2021 08:48 am
  • በትግራይ ክልል በሴቶች ላይ ተፈጸመ የተባለውን ጥቃት የሚያጣራ ግብረ ኃይል መቀሌ ገባ February 3, 2021 12:06 pm
  • ፓርቲዎች የምርጫ መወዳደሪያ ምልክቶቻቸውን ወሰዱ February 3, 2021 10:29 am
  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule