• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የነፍስ ስደተኞች (the immigrants of survival)

November 16, 2013 12:56 am by Editor Leave a Comment

ባገሩ የሚኮራ ፤ ሀገሩን አፍቃሪ

ለወገን ሟች ስፍሱፍ ፤ አብሮነት ዘማሪ

የነፍስ ስደተኛ ፤ እውነት አስመስካሪ

የሀገሩ ነገር ፤ የወገኑ እጣ

ሁሌ የሚያስጨንቀው ፤ ሲበዛ ግፍ ጣጣ

ስለተገለለ ፤ አማራጭ ስላጣ

እኛን ካልሆንክ ተብሎ ፤ ሕሊናው ተሸጣ

ደሞ ስለተገፋ ፤ ታይቶ እንደ ባላንጣ

አላፈናፍን ተብሎ ፤ ጅቡ እየተቆጣ

አላቃምስ ተብሎ ፤ በራብ እየተቀጣ

ወገን ሲለይበት ፤ ሆኖ ዘር መረጣ

ቢብሰው ተነሣ ፤ ለስደት ጎረፈ

ከሞት ጋር ተፋጦ ፤ ሞትን እያለፈ

ግፍ እየተጋተ ፤ እየተቀሰፈ

ገና ባልጸናለት ፤ በጨቅላ ትከሻ

ስንት ስቃይ ዐየ ፤ የጣር መጨረሻ

ወገኑን እያጣ ፤ የዓሣ ሲሳይ ሆኖ

በአራዊት ተበልቶ ፤ በድንገት ታድኖ

ስለተደፈረ ፤ እራሱን ኮንኖ

በራብ በውኃ ጥም ፤ እየቀረ ደብኖ

በኢሰብአዊ ግፍ ፤ በአውሬ አረመኔ

ለኩላሊት ልቡ ፤ ታርዶ በጭካኔ

ከዚህ የተረፈው ፤ ሲደርስ ያ ወገኔ

ከገባበት ሀገር ፤ ተአምር እያስጻፈ

ጎኑን ሳያሳርፍ ፤ ሳይዝ የተረፈ

አንቀው ሊመልሱት ፤ እየተጠረፈ

ባዶ እጁን ሊጥሉት ፤ እየተገፈፈ

ሊይዙት ሲያሳዱት ፤ ሲሮጥ እየከነፈ

ሀገር እንደጠላ ፤ እንደተጸየፈ

መመለስን ጠልቶ ፤ ዋ! ተንገፈገፈ

ወደ ሲዖል ባሕር ፤ እንደሚጣል ቆጥሮ

ለማምለጥ ሲሯሯጥ ፤ በነፍሴ አውጭኝ በሮ

ከገሃነም ጭፍራ ፤ ጽድቅ ከጨነገፈ

ትናንትን ከረሳ ፤ ነገን ካከሸፈ

ሊያመልጥ ሲበረግግ ፤ ዋ! ተንዘፈዘፈ

መንገድ ላይ ወደቀ ፤ ተደነቃቀፈ

በእሳት ጥይት አረር ፤ እየተገረፈ

የሞት ስደተኛው ፤ እየሮጠ ዐረፈ

ስንትን ሞት ተሻግሮ ፤ ሊያልፍለት አለፈ

ባዶ እጀን አልሄድም ፤ ቃሌ ካልሠመረ

አላሳፍራትም ፤ ብሎ እንደፎከረ

በናፍቆት ተቆልቶ ፤ ፍቅሯን እያዜመ

ተደፍቶ ቀረላት ፤ አስከሬን ተመመ

የሚታደግ አጥቶ ፤ ታፋሪ ተፈሪ

የኛ ብሎ የሚለው ፤ መንግሥት ተቆርቋሪ ፡፡

ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው
ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው

ሀገር እርምሽን አውጭ ፤ ይብቃሽ ይቅር ምጡ

እናት አባት ወገን ፤ ሐዘን ተቀመጡ

ሳተና ልጆችሽ ፤ የአንችን ቀን ሊያመጡ

መልሰው ላያዩሽ ፤ ቀሩ እንደወጡ  ፡፡

ኅዳር 3 / 2006 ዓ.ም.

amsalugkidan@gmail.com

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule