• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የደቡብ አፍሪካዊያን ዕዳ!

January 30, 2015 04:01 am by Editor Leave a Comment

የማንዴላ ልጆች ወገኖቹ ፤ የዋልንላቸው ውለታ

ይህች አፍሪካ በነጻነት ፤ እንድታገኝ እፎይታ

ጥረታችን ሁሉ ሰምሮ ፤ አገኙና ነጻነት

በእኛ ቀን ሲዘነብል ፤ ብንሔድባቸው ስደት

ከቅኝ ግዛት እስከ አፓርታይድ ፤ የረገጣቸው እያለ

ወንድም ጓዱን ሐበሻ ፤ ስለ እሱ ዋጋ የከፈለ

ከሀገር ይውጣ ብሎ ጮኸ ፤ ጎዳናው ላይ እያቃጠለ፡፡

ምን ነው ወገኔ ምን ነው? ፤ አእምሮም የለህ ማሰቢያ?

ምን እንደሆነች አታውቅም? ፤ ውዷ የኔ ሀገር ኢትዮጵያ?

በከፈልንላቹህ ዋጋ ፤ በእናንተ የተነሣ

እንዲህ ሆና እንደቀረች ፤ በነጫጭ ጅቦች ተነክሳ?

ታወክን ታመስን እንጅ ፤ በነጭ ሰይጣናት እከይ

ወደ እናንተ የተመምነው ፤ መች አጥተን ነበር ሲሳይ

ስለእናንተ ባደረግነው ፤ ከዲፕሎማሲው ማሳደም

መሪዎችህን አሠልጥኖ ፤ በግንባር እስከ ማፋለም

በእኛ ጥረት ነበርና ፤ ነጻነትህ የተገኘ

ጥርስ ነከሱ በእኛ ላይ ፤ ልባቸው በቀል ተቃኘ

እርስ በርሳችን ብንባላ ፤ እንድንሆን ከንቱ መና

ያለእነሱ ማንም የለም ፤ የሴራው ምንጭ ሲጠና

ላንተ ስንል በከፈልነው ፤ ለዚህ ብንበቃ ብናጣ

ማስጠጋት ሲገባህ በክብር ፤ የጠላትህን ባላንጣ

የክፉ ቀንህን አጋር ፤ የተሰጠህን ዕጣ

እሳት በላዩ እየለቀክ ፤ ማባረሩ ነው የሱ ዋጋ?

ከቶ በምን ሒሳብ ነው? ፤ ሕሊናም የለ አንተ ጋ?

ፍዳ ያስቆጠረህ ባዕዱ ፤ እየኖረ ተንቀባሮ

ላንተም ኢምንት ያልከፈለው ፤ መጥቶ ከህንድ ተሸግሮ

በምቾት ድሎት እየኖረ ፤ ሞጃ ሆኖ ገኖ ከብሮ

በገዛ የራስ ሀገርህ ፤ አንተን ባዶ አርጎ ገፍትሮ

የገዛ ሀገርክን ከተማ ፤ እያስቋመጠህ አማልሎ

ነጻነትህ ትርጉም አጥቶ ፤ ገብተህ ለመርገጥ ከልክሎ

ይሄ ሳያምህ ሳይቆጭህ ፤ ወኔህ ተሰልቦ ተገሎ

ሀሞትህ ፈሶ ፈራርሶ ፤ ጉልበትህ ከድቶህ ሰልሎ

ይሄንን የሚያህል ውርደት ፤ ተሸክመኸው እያለ

በዚህ ዘመን አሁን ዛሬ ፤ ነጻ ነኝ እያልክ ታደለ

ምስኪኑ ደሀው ወንድምህ ፤ ምን አረገ? ምን በደለ?

ያንተን ቀንበር ተሸክሞ ፤ በሞተልህ በቆሰለ?

ሀገሬን ካልክ መብቴን ፤ የራሴን ሀብት እንጀራ

የወሰደብህ እያለ ፤ ድልቡን ዋናውን ጎተራ

ፍርፋሪውን ለቃሚው ፤ ወንድም ሐበሻው ምን ሠራ?

እንዴት ነው እሱ ነገሩ ፤ የባሕል ወጋቹህ ዕይታ?

ተገላቢጦሽ ነው እንዴ? ፤ ለወዳጅ ክፉን መልሶ

ዘርፎ እራቁቱን ማስቀረት ፤ ካገር ማባረር አስለቅሶ?

ገድሎ መንገድ ላይ መጎተት? ፤ መልካም ምግባሩን አርክሶ?

መልካሙን ለጠላት በማቅረብ ፤ ባርነትን መኖር መልሶ?

ይሄነው ባሕላ ወጋቹህ? ፤ የማሰብ ልካቹህ ተሐድሶ?

እኛ እኮ እንደዚያ የደከምን ፤ ከዲፕሎማሲም ኃይል እርዳታ

እንድትኖሩ አልነበረም ፤ በእንደዚህ ዓይነት ሁኔታ

ወይ ከዳር ደርሶ አላየን ፤ የነጻነቱን ፍልሚያ

ድካማችንን ከንቱ አረገው ፤ ዛሬ ያለብህ ግሊያ

እንዲህ በአድሎ እየኖርክ ፤ ከማዶ ከኬላ ወዲያ

አፓርታይድ የለም ትላለህ? ፤ በዚህ አናፍርም ታዲያ?

ዕያየነው በመሆኑ ፤ ዛሬም ሆናቹህ ባሪያ::

ወገኔ ማጥፋት ማስወገድ ፤ ድል ማድረግ ያለብህ እኮ!

ይሄንን ውርደትህን ነው ፤ ያስቀረህን አንበርክኮ

ሀገርህን ማስመለስ ነው ፤ ከተወሰደብህ ምርኮ፡፡

የኔስ ግምት የነበረው ፤ ወገኔ ሆኖ ስደተኛ

ወዳገርህ ስጎርፍ ሲተም ፤ ሆኖ ሊኖር ጥገኛ

ያለውን ህልም ያውቃሉና ፤ ዓላማ ምኞቱን ለአንተ

የፈራሁ ነጮቹን ነበር ፤ ግምት ሥጋቴ ሳተ

ጭራሽማ እዚህ ገብቶ ፤ አብሮ ሆኖ እየኖረ

በምክር እያነሣሣ ፤ ገፋፍቶ እያዳፈረ

መፈጸሙ አይቀር ብለው ፤ የቀረውን የቤት ሥራ

ያነቃብናል ዋ! ኋላ ፤ መንገድ ጠቁሞ እየመራ

አይሆንም ሐበሻ ይውጣ ፤ ብየ እንዳያሴሩ ሴራ

እንጅ አንተንማ እንደምን? ፤ እኮ እንዴት ብየ ጠርጥሬ?

ወንድም ነው ዕዳም አለበት ፤ ባልኩት እንዳይን አሳሬ?

ግን ምንም ያለህ አልነበረም  ፤ እሱ አባትህ ማንዴላ

ዕዳ አለብን አላለህም? ፤ ያንን ዕዳ እንዳትበላ?

ወይስ ነው ችግሩ ያንተ? ፤ ቃሉን ያልሰማህ አደራ

ማዲባዬ እያልክ አባቴ ፤ የነጻነት ታጋይ አውራ

ኧረ ተው አባትህን ስማ ፤ ሰምተናል ብዙ እንዳለ

ጠብቅ እንጅ ቃል አደራን ፤ ምን ነው? በማን ተማለ?

ይሄንን ቃል ባትሰማ ፤ በሰማይ ባንተ ፍርድ አለ!

ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው

ጥር 19 2007ዓ.ም.

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule