• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሌቦቹ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ይፋ ሆኑ፤ 4 ቢሊዮን ብር ያህል ባክኗል

July 5, 2023 01:58 pm by Editor Leave a Comment

የፌደራል ዋና ኦዲተር ወ/ሮ መሠረት ዳምጤ የ2014 በጀት ዓመት የፌዴራል መንግሥት መሥሪያ ቤቶች የፋይናንስና ሕጋዊነት ኦዲትን በተመለከተ ተቋማቸው ያካሄደውን የኦዲት ሪፖርት፣ ማክሰኞ ሰኔ 20 ቀን 2015 ዓ.ም. ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅርበዋል፡፡

ለፓርላማው የቀረበው የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት ሪፖርት እንደሚያመለክተው፣ የ2014 ዓ.ም. በጀት አፈጻጸምን በተመለከተ በተደረገው የኦዲት ሥራ ስድስት ተቋማት አስተያየት ለመስጠት ያልተቻለባቸው ሲሆኑ፣ 19 ተቋማት ደግሞ የጎላ ችግር ያላባቸው ሆነው በመገኘታቸው ተቀባይነት የሚያሳጣ አስተያየት ተሰጥቶባቸዋል፡፡

ሒሳባቸው የጎላ ችግር ያለበት በመሆኑ ተቀባይነት የሚያሳጣ አስተያየት ከተሰጠባቸው ተቋማት መካከል

  • የፌዴራል ሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን፣
  • የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ፣
  • የኢንፎርሜሽንና መረብ ደኅንነት አገልግሎት
  • የፌዴራል ፖሊስ
  • ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ፣
  • ጂንካ ዩኒቨርሲቲ፣
  • ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ፣
  • ጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ፣
  • ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ፣
  • አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣
  • ቦሌሆራ ዩኒቨርሲቲና
  • የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ይገኙበታል፡፡

የፌዴራል ዋና ኦዲተር አስተያየት ለመስጠት አልቻልኩባቸውም ካላቸው ተቋማት መካከል

  • የሪፐብሊኩ የጥበቃ ኃይል፣
  • አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ፣
  • ብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት፣
  • የቀድሞው የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት፣
  • የአደጋ ሥጋትና ሥራ አመራር ኮሚሽንና
  • የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አሉበት፡፡

ከአንድ ዓመት እስከ ስድስት ዓመት ዕድሜ ያለውና ለመንግሥት ገቢ መደረግ የነበረበት 13.4 ቢሊዮን ብር ውዝፍ የጉምሩክ ቀረጥና ታክስ ዕዳ መኖሩ በሪፖርቱ ተመላክቷል፡፡

የተሟላ ወጪ ሳይቀርብ በወጪ መዝግበው የተገኙ መሥሪያ ቤቶች

  • የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ 124 ሚሊዮን ብር፣
  • የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር 65 ሚሊዮን ብር፣
  • የአደጋ ሥጋትና ሥራ አመራር ኮሚሽን 64 ሚሊዮን ብር፣
  • የሰመራ ጉምሩክ ቅርንጫፍ 7.9 ሚሊዮን ብር፣
  • የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን 5.6 ሚሊዮን ብር፣
  • ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ 4.8 ሚሊዮን ብር፣ በድምሩ 307.5 ሚሊዮን ብር የተሟላ ወጪ ሳይቀርብ በወጪ መዝግበው የተገኙ መሥሪያ ቤቶች ናቸው ተብሏል፡፡

በሌላ በኩል ከደንብና ከመመርያ ውጪ ያላግባብ ክፍያ ከፈጸሙ ተቋማት መካከል

  • የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ 30 ሚሊዮን ብር፣
  • የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ 22 ሚሊዮን ብር፣
  • የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ 11.8 ሚሊዮን ብር፣
  • የመንግሥት ግዥና ንብረት ባለሥልጣን 7.6 ሚሊዮን ብር፣
  • የቤተ መንግሥት አስተዳደር 6.5 ሚሊዮን ብር፣
  • አርሲ ዩኒቨርሲቲ 6.1 ሚሊዮን ብር፣ በድምሩ 134.2 ሚሊዮን ብር ተጠቃሽ ናቸው፡፡

የግዥን ሕግ የጣሰ ክፍያ 592.4 ሚሊዮን ብር

የመንግሥት የግዥ አዋጅ ደንብና መመርያ ያልተከተሉ ግዥዎችን የፈጸሙ 82 ተቋማት በሪፖርቱ የተጠቀሱ ሲሆን፣ ከእነዚህ መሥሪያ ቤቶች የተገኘው የግዥን ሕግ የጣሰ ክፍያ 592.4 ሚሊዮን ብር ነው፡፡ ተቋማቱ

  • ጉምሩክ ኮሚሽን፣
  • ጂንካ ዩኒቨርሲቲ፣
  • ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ፣
  • የኢንፎርሜሽን መረብና ደኅንነት አገልግሎት፣
  • የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካደሚና
  • ቡሌሆራ ዩኒቨርሲቲ ናቸው፡፡

የፌዴራል ዋና ኦዲተር ወ/ሮ መሠረት በተከፋይ ሒሳብ ተመዝግበው የተገኙ ነገር ግን ዝርዝር ማስረጃ ባለማቅረቡ የሒሳቡን ትክክለኛነት ለማረጋገጥ እንዳልቻለ ያቀረቡ ሲሆን፣ ከእነዚህ ተቋማት መካከል

  • የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት አንድ ቢሊዮን ብር፣
  • የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት 583 ሚሊዮን ብር፣
  • የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር 131.8 ሚሊዮን ብርና
  • ጉምሩክ ኮሚሽን 96.5 ሚሊዮን ብር ይገኙበታል፡፡ በድምሩ 1 ቢሊዮን 903.5 ሚሊዮን ብር ነው።

ከተደለደለላቸው በጀት በላይ የተጠቀሙ መሥሪያ ቤቶችም በሪፖርቱ የተጠቀሱ ሲሆን፣ ከእነዚህ መካከል

  • ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ 358.9 ሚሊዮን ብር፣
  • ዲላ ዩኒቨርሲቲ 125 ሚሊዮን ብር፣
  • ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ 139.9 ሚሊዮን ብር፣
  • ዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ 166.7 ሚሊዮን ብር፣
  • አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ 113 ሚሊዮን ብር ናቸው፡፡ በድምሩ 903.5 ሚሊዮን ብር ነው።

የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች በ2014 ዓ.ም የተፈቀደላቸውን በጀት መጠቀም ሲገባቸው ባለመጠቀማቸው የተገኘው አጠቃላይ ገንዘብ 35 ቢሊዮን ብር መሆኑ በሪፖርቱ ተጠቅሷል፡፡

በጀት ሥራ ላይ ካላዋሉ መሥሪያ ቤቶች

  • የመስኖና ቆላማ ሚኒስቴር 8.9 ቢሊዮን ብር፣
  • የገንዘብ ሚኒስቴር 6.3 ቢሊዮን ብር፣
  • የጤና ሚኒስቴር ሦስት ቢሊዮን ብር፣
  • ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን 1.2 ቢሊዮን ብር፣
  • የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አንድ ቢሊዮን ብር፣
  • የትምህርት ሚኒስቴር 915 ሚሊዮን ብር፣
  • የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር 599 ሚሊዮን ብር ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡

ዋና ኦዲተሯ በጀት ተከፈቀደ በኋላ አለመጠቀም የታቀዱ ሥራዎች ሳይከናወኑ ሊቀሩ ስለሚችሉና ተቋማትም ዓላማቸውን እንዳያሳኩ ስለሚያደርጋቸው፣ የበጀት ዝግጅትና የአጠቃቀም ጥንቃቄ እንዲደረግ አሳስበዋል፡፡

የተሽከርካሪ አጠቃቀምና አያያዝን በተመለከተ በሚያብራራው የኦዲት ሪፖርት በመንግሥት ተቋማት ውስጥ

  • 188 ተሽከርካዎች ሊብሬ ያልቀረበበባቸው
  • 694 ተሽከርካሪዎችና 56 ሞተር ብስክሌቶች ያለ አገልግሎት ወይም በብልሽት የቆሙ
  • የባለቤትነት መታወቂያ ደብተራቸው በሌሎች መሥሪያ ቤቶችና ድርጅቶች ስም የሆኑ 275 ተሽከርካሪዎች፣
  • የነዳጅ መቆጣጠሪያ (ጌጅ) የሌላቸው 44 ተሽከርካሪዎች፣
  • የመድን ዋስትና የሌላቸው ወይም ያልተገባላቸው አሥር መኪኖች ይገኙበታል ተብሎ በሪፖርቱ ተገልጿል፡፡

የኦዲት ሪፖርቱ ከተሰጠ በኋላ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የፓርላማ አባል አቶ ሙሉቀን አሰፋ፣ ‹‹በጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ አስተባባሪነት በሚመሩ የሜጋ ፕሮጀክቶች ጉዳይ የገንዘብ አሰባሰብና አወጣጥን በተመለከተ የመንግሥት የፋይናንስን አዋጅ ደንብና መመርያ ተከትሎ እየተሠራ ስለመሆኑ ኦዲት አድርጋችሁ ከሆነ የኦዲት ሪፖርቱ ቢገለጽልን፣ ካላደረጋችሁ ደግሞ ኦዲት ላለማድረግ ምክንያታችሁ ምንድነው?›› በማለት ጥያቄ አቅርበዋል፡፡

የፌዴራል ዋና ኦዲተሯ ወ/ሮ መሠረት ለተነሳው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ፣ ‹‹ኦዲት ኣላደረግንም፣ ያላደረግንበት ምክንያት ምንድነው? የፌደራል ዋና ኦዲተር ተግባርና ኃላፊነት የመጀመሪያው በተከበረው ምክር ቤት የፀደቀውን በጀት የክዋኔ ኦዲት ማድረግ፤›› ነው ብለዋል፡፡ በተጨማሪ ደግሞ የመንግሥት ተቋማትም ይሁኑ የልማት ድርጅቶች በአዋጅ በተሰጣቸው ሥልጣንና ኃላፊነት መሠረት የክዋኔ ኦዲት እንደሚደረግና ሪፖርት እንደሚቀርብ ተናግረዋል፡፡ ‹‹ስለዚህ ቅድሚያ በተሰጠን ሥልጣንና ኃላፊነት መሠረት እንሄዳለን፡፡ አሁንም ግን እነዚህን ፕሮጀክቶች በተመለከተ የተመዘበረና የጠፋ ነገር ካለ በኦዲት የሚታለፍ ተቋም ስለሌለ፣ የፕሮጀክቶቹ ስምና የጎደለው ገንዘብ በግልጽ ከቀረበልን ለማየት ዝግጁ ነን፤›› ብለዋል፡፡ (ሪፖርተር)

በተዘጋው የበጀት ዓመት የባከነው ገንዘብ ይህም ማለት የተሟላ ወጪ ሳይቀርብ በወጪ የተመገበው፤ ከደንብና ከመመርያ ውጪ ያላግባብ ክፍያ የተፈጸመው፤ የግዥን ሕግ የጣሰው ክፍያ፤ የሒሳቡን ትክክለኛነት ለማረጋገጥ ያልተቻለበት እና ከተደለደለላቸው በጀት በላይ የተጠቀሙ መሥሪያ ቤቶች በአጠቃላይ የባከነው ብር 3 ቢሊዮን 841 ሚሊዮን ብር ነው።

ከሁሉ የሚያስደንቀው ሒሳባቸው የጎላ ችግር ያለባቸው ተብለው ከተጠቀሱት መሥሪያ ቤቶች በቀዳሚነት የተጠቀሰው የፌዴራል ሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን መሆኑ ነው። መሥሪያ ቤቱ የድርጅቱ መፈክር አድርጎ የሚጠቀመው “ከሙስና የጸዳች ኢትዮጵያ” የሚል መሆኑ ይታወቃል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: corruption, Ethiopia corruption, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule