• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የግፍ ሠንደቅ ወረደ!

July 11, 2015 04:20 am by Editor Leave a Comment

በአሜሪካ የደቡብ ካሮላይና ጠቅላይ ግዛት ዋና ከተማ የሸንጎ ሕንጻ ላይ ከ50 በላይ ሲውለበለብ የነበረው ሠንደቅ አርብ ወረደ፡፡ “ውሸት ለዘላለም መቆየት አይችልም፤ የዘረኝነት ምልክት እና ዘረኝነት መፍረስ ይገባቸዋል” በማለት የሠንደቁን መውረድ የደገፉ ተናገሩ፡፡

በእንግሊዝኛው አጠራር “የኮንፌዴሬት” ሠንደቅ የሚባለው በአሜሪካ የእርስበርስ ጦርነት ወቅት ከኅብረቱ ለመለየት የፈለጉ ግዛቶች የራሳቸውን ፕሬዚዳንት መርጠው ከኅብረቱ ደጋፊዎችና አብርሃም ሊንከን ጋር ጦር በገጠሙበት የተጠቀሙበት ሠንደቅ ነው፡፡ ፕሬዚዳንት አብርሃም በአሜሪካ ውስጥ የተንሰራፋውን በዘር ላይ የተመሠረተውን ባርነት ለመደምሰስ ህግጋትን እያወጡ በነበሩበት ወቅት በባሪያ ፈንጋይነት የሚታወቁት የደቡብ ጠቅላይ ግዛቶች የባርነትን መወገድ በመቃወም ከኅብረቱ ለመገንጠል በመፈለጋቸው በአሜሪካ የእርስበርስ ጦርነት ተቀሰቀሰ፡፡

ጥቁሮችን እጅግ አሠቃቂና ፍጹም ኢሰብዓዊ በሆነ መልኩ ሲያሰቃዩ፤ በግፍ ሲገድሉ፤ ከነህይወታቸው በእሣት ሲያቃጥሉ፤ ሴቶቻቸውን ቀን በጥጥ ለቀማና በመሳሰለው ሥራ በሃሩር በግፍ ሲያሰሩ ቆይተው ማታ ደግመው ይደፍሩ የነበሩ፤ የተወሰነላቸውን ጥጥ በቀኑ መልቀም ያልቻሉ ሌሊቱን ጀርባቸው እስኪተለተል ሲገርፉ የነበሩ፤ በነጋታው ልብሳቸው በደም ርሶ ከቆዳቸው እንደተጣበቀ በጥጥ ለቀማ እንደገና እንዲሰማሩ ግፍ ሲፈጽሙ የነበሩ፤ በነጮች ሰፈር መንገድ ላይ ሲሄዱ በመገኘታቸው ብቻ ከነህይወታቸው በእንጨት አስረው በእሣት እያቃጠሉ የደስታ መጠጥ ሲጠጡ እና የፍም ጥብስ እየበሉ በሰው ስቃይ ሲዝናኑ የነበሩ፤ … ጥቁሮች ነጻ መውጣት የለባቸውም በማለት ለጦርነት ሲሄዱ የተጠቀሙት ሠንደቅ ነበር ይህ “የኮንፌዴሬት” ሠንደቅ የተባለው፡፡

በደቡብ ካሮላይና ግዛት በቅርቡ በቤተክርስቲያን በጸሎትና መጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ላይ የነበሩ ጥቁሮችን የገደለው ነጭ ወጣት ይህንን የግፍ ሠንደቅ ይዞ የበላይነቱን ማሳያ አድርጎ የተነሳበት ፎቶ ከተለቀቀ ወዲህ ይህ ሠንደቅ ከመንግሥት ሕንጻ ላይ እንዲነሳ የቀረበው ሃሳብ ከፍተኛ ክርክር አስነስቶ ነበር፡፡ የጠቅላይ ግዛቱ ገዥ በውሳኔው ላይ ፊርማቸውን በማስቀመጥ ካጸደቁት በኋላ የግፍና የደም እንዲሁም የሰቆቃ መለያ የሆነው ሠንደቅ አርብ በይፋ ወርዷል፡፡

በሥነሥርዓቱ ላይ የነበሩ የግፉ ሰለባዎች አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡ “ይህ ሠንደቅ የክፍፍል፣ የዘር፣ የወገንተኝነት፣ አንዱ ከሌላው የበለጠ ወርቅ ዘር ስለሆነ ገዢ መሆኑን የሚያሳይበት፣ የርኩሰት መለያ ነው፤ መውረዱ ተገቢ ነው” ብለዋል የጥቁር ሰብዓዊ መብት ተከራካሪ፡፡

“አሜሪካ የተገነባችው በዘር ላይ ነው፤ የዘረኝነት ሥርዓት እና ምልክቱ ሁሉ ደግሞ መፍረስ አለበት” በማለት የጥቁር ወጣቶች ኅብረት ሃላፊ ተናግሯል፡፡ “ውሸት ለዘላለም መኖር አይችልም፤ ይህ ሠንደቅ የውሸት መለያ ነው” በማለት ለጥቁሮች መብት የሚከራከረው ድርጅት ኃላፊ ተናግረዋል፡፡

“ግፍ፣ ሰቆቃ፣ ሃዘን፣ ስቃይ፣ መታሰር፣ መገደል፣ አምባገነንነት፣ ዘረኝነት፣ ከፋፋይነት፣ እና እነዚህን የሚወክሉ መለያዎችና ምልክቶች ሁሉ የፈለገ ቢያደርጓቸው ቀናቸውን ጠብቀው ከተሰቀሉበት ከነሰቃዮቹ መውረዳቸው አይቀርም” በማለት የሠንደቁን መውረድ አስመልክቶ አንድ አዛውንት ጥቁር የተናገሩት አሁንም በተመሳሳይ ሠንደቅ ዓላማ ምልክትነት እየተጨቆኑ ለሚገኙ ሁሉ ተስፋን የሚፈነጥቅ ሆኗል፡፡

ይህንን ሠንደቅ ዓላማ ከሌሎች የአሜሪካ ደቡባዊ ጠቅላይ ግዛቶች የማውረድ እንቅስቃሴ በሰፊው ተጀምሯል፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule