• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የግፍ ሠንደቅ ወረደ!

July 11, 2015 04:20 am by Editor Leave a Comment

በአሜሪካ የደቡብ ካሮላይና ጠቅላይ ግዛት ዋና ከተማ የሸንጎ ሕንጻ ላይ ከ50 በላይ ሲውለበለብ የነበረው ሠንደቅ አርብ ወረደ፡፡ “ውሸት ለዘላለም መቆየት አይችልም፤ የዘረኝነት ምልክት እና ዘረኝነት መፍረስ ይገባቸዋል” በማለት የሠንደቁን መውረድ የደገፉ ተናገሩ፡፡

በእንግሊዝኛው አጠራር “የኮንፌዴሬት” ሠንደቅ የሚባለው በአሜሪካ የእርስበርስ ጦርነት ወቅት ከኅብረቱ ለመለየት የፈለጉ ግዛቶች የራሳቸውን ፕሬዚዳንት መርጠው ከኅብረቱ ደጋፊዎችና አብርሃም ሊንከን ጋር ጦር በገጠሙበት የተጠቀሙበት ሠንደቅ ነው፡፡ ፕሬዚዳንት አብርሃም በአሜሪካ ውስጥ የተንሰራፋውን በዘር ላይ የተመሠረተውን ባርነት ለመደምሰስ ህግጋትን እያወጡ በነበሩበት ወቅት በባሪያ ፈንጋይነት የሚታወቁት የደቡብ ጠቅላይ ግዛቶች የባርነትን መወገድ በመቃወም ከኅብረቱ ለመገንጠል በመፈለጋቸው በአሜሪካ የእርስበርስ ጦርነት ተቀሰቀሰ፡፡

ጥቁሮችን እጅግ አሠቃቂና ፍጹም ኢሰብዓዊ በሆነ መልኩ ሲያሰቃዩ፤ በግፍ ሲገድሉ፤ ከነህይወታቸው በእሣት ሲያቃጥሉ፤ ሴቶቻቸውን ቀን በጥጥ ለቀማና በመሳሰለው ሥራ በሃሩር በግፍ ሲያሰሩ ቆይተው ማታ ደግመው ይደፍሩ የነበሩ፤ የተወሰነላቸውን ጥጥ በቀኑ መልቀም ያልቻሉ ሌሊቱን ጀርባቸው እስኪተለተል ሲገርፉ የነበሩ፤ በነጋታው ልብሳቸው በደም ርሶ ከቆዳቸው እንደተጣበቀ በጥጥ ለቀማ እንደገና እንዲሰማሩ ግፍ ሲፈጽሙ የነበሩ፤ በነጮች ሰፈር መንገድ ላይ ሲሄዱ በመገኘታቸው ብቻ ከነህይወታቸው በእንጨት አስረው በእሣት እያቃጠሉ የደስታ መጠጥ ሲጠጡ እና የፍም ጥብስ እየበሉ በሰው ስቃይ ሲዝናኑ የነበሩ፤ … ጥቁሮች ነጻ መውጣት የለባቸውም በማለት ለጦርነት ሲሄዱ የተጠቀሙት ሠንደቅ ነበር ይህ “የኮንፌዴሬት” ሠንደቅ የተባለው፡፡

በደቡብ ካሮላይና ግዛት በቅርቡ በቤተክርስቲያን በጸሎትና መጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ላይ የነበሩ ጥቁሮችን የገደለው ነጭ ወጣት ይህንን የግፍ ሠንደቅ ይዞ የበላይነቱን ማሳያ አድርጎ የተነሳበት ፎቶ ከተለቀቀ ወዲህ ይህ ሠንደቅ ከመንግሥት ሕንጻ ላይ እንዲነሳ የቀረበው ሃሳብ ከፍተኛ ክርክር አስነስቶ ነበር፡፡ የጠቅላይ ግዛቱ ገዥ በውሳኔው ላይ ፊርማቸውን በማስቀመጥ ካጸደቁት በኋላ የግፍና የደም እንዲሁም የሰቆቃ መለያ የሆነው ሠንደቅ አርብ በይፋ ወርዷል፡፡

በሥነሥርዓቱ ላይ የነበሩ የግፉ ሰለባዎች አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡ “ይህ ሠንደቅ የክፍፍል፣ የዘር፣ የወገንተኝነት፣ አንዱ ከሌላው የበለጠ ወርቅ ዘር ስለሆነ ገዢ መሆኑን የሚያሳይበት፣ የርኩሰት መለያ ነው፤ መውረዱ ተገቢ ነው” ብለዋል የጥቁር ሰብዓዊ መብት ተከራካሪ፡፡

“አሜሪካ የተገነባችው በዘር ላይ ነው፤ የዘረኝነት ሥርዓት እና ምልክቱ ሁሉ ደግሞ መፍረስ አለበት” በማለት የጥቁር ወጣቶች ኅብረት ሃላፊ ተናግሯል፡፡ “ውሸት ለዘላለም መኖር አይችልም፤ ይህ ሠንደቅ የውሸት መለያ ነው” በማለት ለጥቁሮች መብት የሚከራከረው ድርጅት ኃላፊ ተናግረዋል፡፡

“ግፍ፣ ሰቆቃ፣ ሃዘን፣ ስቃይ፣ መታሰር፣ መገደል፣ አምባገነንነት፣ ዘረኝነት፣ ከፋፋይነት፣ እና እነዚህን የሚወክሉ መለያዎችና ምልክቶች ሁሉ የፈለገ ቢያደርጓቸው ቀናቸውን ጠብቀው ከተሰቀሉበት ከነሰቃዮቹ መውረዳቸው አይቀርም” በማለት የሠንደቁን መውረድ አስመልክቶ አንድ አዛውንት ጥቁር የተናገሩት አሁንም በተመሳሳይ ሠንደቅ ዓላማ ምልክትነት እየተጨቆኑ ለሚገኙ ሁሉ ተስፋን የሚፈነጥቅ ሆኗል፡፡

ይህንን ሠንደቅ ዓላማ ከሌሎች የአሜሪካ ደቡባዊ ጠቅላይ ግዛቶች የማውረድ እንቅስቃሴ በሰፊው ተጀምሯል፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
Copyright © 2026 · Goolgule