• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሐመሯ ቆንጆ

May 13, 2014 07:51 am by Editor 6 Comments

ደራሲና ጋዜጠኛ አበራ ለማ የሬድዮ ጋዜጠኛ በነበረበት ጊዜ ወደ ጋሞ ጎፋ ለስራ ሲሄድ፣ በድንገት ካጋጠመችው የሐመር ቆንጆ ጋር የተነሳው ፎቶ ነው።

ምልልሱን ያንብቡ።

      በደመቀ ፀሐይ

      ከወለላዬ

በቀን አጋማሽ ላይ – በደመቀ ፀሐይ

አካሏ ተጋልጦ – በግማሽ የሚታይ፣

የተዋበች ሐመር – መንገድ ላይ ብትወጣ

አዬ ጋዜጠኛው – የመጣበት ጣጣ፣

እሷ ግን እቀፊው – ሳሚው ሳሚው ብሏት

ጎኑ ብትጠጋው – አሹላ ያንን ጡት፣

የሱም አጉል ፍራት – የሷም አጉል ድፍረት

በደመቀ ፀሐይ

———-

ሰውም ይፈራል ወይ?

ከአበራ ለማ

ጌታ ወለላዬ – ምነዋ አልፈራ

መትረየስ ደግና – ፊቴ ተገትራ፤

ደ’ሞኮ አወጣጧ – ከጫካው ከዱሩ

መፍራት ይነሰኝ ወይ – እንግዳው ላገሩ፤

አያድርስ እንጂ ነው – touch down ብትለኝ

በዚህ በጠራራ – መጋኛስ ቢመታኝ፤

———-

hamer1ታዝቤህ ነበረ

ከወለላዬ

ዘምተህ የተመለስክ – በናቅፋ ተራራ

መሳሪያ የጨበክ – ከጀግኖቹ ጋራ፣

ባዶዋን የመጣች – ትንሽ ልጅ ስትፈራ፣

ታዝቤህ ነበረ – ጋዜጠኛ አበራ።

አሁን ግን ሳስበው – ነገሩን በትኩረት

ጠላትን ሰብስቦ – ማርኮ ለማስቀረት፣

ወታደር መልምሎ – ጦር ሜዳ ከማዝመት

ሳትሻል አትቀርም – አንዷ የሀመር ሴት፣

———-

ያልተነካ …

ከአበራ ለማ

አወይ አለመያዝ – አለመነካት

ጡር ነው ወለላዬ – በነፍሴስ መምጣት፤

ጥግብ ፍርጥም ያለች – ደንደሮ ወጣት

ታስጨፍረኝ ነበር – ኢቫንጋዲ ስልት፤

ናቅፋ ቢበረታም – ይሄ ጋዜጠኛ

ከመሆን አልዳነም – የሐመር ምርኮኛ!!!

—— ||||||||||| ——

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    May 13, 2014 04:36 pm at 4:36 pm

    “ታመመልሽ ደነገጠልሽ ከቶ በዐይን ብቻ ሳይነካው አካልሽ
    ቀረጥ የሌለበት ወረት ያልዳሰሰው ደህና አንቴና ሰቅለሽ
    መሳሪያ ሳይዙ መማረኪያ ማን አስታጠቀሽ?
    አንቺ የሐመር ቆንጆ እንደምንድነሽ?
    ፍራቻው በርትቶ ብርክ ቢይዘው
    ዛፍ የለ አካባቢው መቋሚያ የሚሆነው
    እጁን ጀርባዋ ላይ ደገፍ ቢያደርገው
    ንዝርት በፈገግታ ፀሀይ መብረቅ አለው
    ፎቶም ይናገራል ፅፈውም አስታውሰው
    የሐመሯ ወለላዬ ውበትሽ ማራኪ አበራ ለማነው!?
    በለው!

    Reply
    • MINILIK says

      May 14, 2014 01:02 am at 1:02 am

      THANK YOU BELEW FOR YOUR POETIC EXPRESSION!…. I LIKED YOUR REACTION.

      Reply
  2. Bombu says

    May 15, 2014 03:42 pm at 3:42 pm

    ፈረሱም ሜዳውም ይሐው ከተባለ
    አስተያየት መስጠት ልብ እንደማለለ
    ተፈቅዶ ከሆነ ትዝብት በደፈናው
    የ ቦምቡ ማጠፊያ መዘርጊያውም ይሕው»

    የሐመርዋን ቆንጆ መሐል አስገብቶ
    ሰጣ ገባ መግባት ቃላተን አስማምቶ
    የጥንት ማስታወሻ እውጥቶ በፎቶ
    ትዛዝ ከተስጠ ከተባለ ጎልጉል
    ታሪክ መቼ ጠፍቶ ሁሌም የሚያማልል

    ስለዚሕ ይቀጠል ፈረሱና ጋሪ
    ጎልጉል እንደሜዳ በተዘዋዋሪ»

    ወለላዬ ያቅርብ ከማሕደር ፎቶ
    አበራም ይመልስ ብድሩን አሳክቶ

    Reply
  3. welelaye says

    May 19, 2014 11:50 am at 11:50 am

    ጌታው አቶ ቦንቡ – አድፍጠው አድፍጠው
    ያቀረቡት ሐሳብ – ፍላጎቴን ሳበው
    በዚህ አቀራረብ – ቃላት አፈሳሰስ
    ምንድነው ችግሩ – ቢሳተፉ እርስዎስ
    ታሪክ ገላልጨ – ማህደር ፈትሼ
    በቅርቡ እመጣለሁ – ዳግም ተመልሼ
    ስለዚህ ለመልሱ – ቀድመው ይሰናዱ
    ለግጥም ጨዋታ – ታጭተዋል እንዳንዱ

    Reply
  4. welelaye says

    May 19, 2014 11:54 am at 11:54 am

    የላይኛው ወደ ስድ ንባብነት ስለተቀየረ ነው የደገምኩት በለው ግሩም ቅኔ አዘል ግጥም ጽፈዋል በተለይ የመጨረሻው ማሰሪያዎ ሁላችንንም የሚአጣቅስ በመሆኑ ወስጥ አወቅ ሳይሆኑ አይቀሩም ብዬ ገመትኩ ከአክብሮት ምስጋና ጋር

    Reply
  5. በለው ! says

    May 21, 2014 04:38 am at 4:38 am

    ******************
    ኢትዮጵያዊነት ፅድቅ ክብር ድንቅ ነው
    ሐመርን ያላየ ሀመር ነዳሁ ያለው እንደ አበራ ለማ ነክቶ ይሞክረው !
    ውስጥ አወቅ ባልሆንም ዓይን ምሥክር ነው
    ወለላ የመሰለች የሚያበራ እያየሁ እንደምን ልለፈው? ከንፈሮቿን ገጥማ አንቴና ብትወጥር
    ምንይልክ ተደንቆ በለው! ቢል ቦንብ አድፍጦ ቢወረውር
    ወለላዋ ለማ አበራም ስንገጥም እየው ሲያምር!!
    ******************
    ከሰላምታ ጋር!! በቸር ይግጠመን በለው!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የሲኖዶሱ ውዝግብ አካሄድና መጪው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ February 6, 2023 02:03 am
  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule