• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሐመሯ ቆንጆ

May 13, 2014 07:51 am by Editor 6 Comments

ደራሲና ጋዜጠኛ አበራ ለማ የሬድዮ ጋዜጠኛ በነበረበት ጊዜ ወደ ጋሞ ጎፋ ለስራ ሲሄድ፣ በድንገት ካጋጠመችው የሐመር ቆንጆ ጋር የተነሳው ፎቶ ነው።

ምልልሱን ያንብቡ።

      በደመቀ ፀሐይ

      ከወለላዬ

በቀን አጋማሽ ላይ – በደመቀ ፀሐይ

አካሏ ተጋልጦ – በግማሽ የሚታይ፣

የተዋበች ሐመር – መንገድ ላይ ብትወጣ

አዬ ጋዜጠኛው – የመጣበት ጣጣ፣

እሷ ግን እቀፊው – ሳሚው ሳሚው ብሏት

ጎኑ ብትጠጋው – አሹላ ያንን ጡት፣

የሱም አጉል ፍራት – የሷም አጉል ድፍረት

በደመቀ ፀሐይ

———-

ሰውም ይፈራል ወይ?

ከአበራ ለማ

ጌታ ወለላዬ – ምነዋ አልፈራ

መትረየስ ደግና – ፊቴ ተገትራ፤

ደ’ሞኮ አወጣጧ – ከጫካው ከዱሩ

መፍራት ይነሰኝ ወይ – እንግዳው ላገሩ፤

አያድርስ እንጂ ነው – touch down ብትለኝ

በዚህ በጠራራ – መጋኛስ ቢመታኝ፤

———-

hamer1ታዝቤህ ነበረ

ከወለላዬ

ዘምተህ የተመለስክ – በናቅፋ ተራራ

መሳሪያ የጨበክ – ከጀግኖቹ ጋራ፣

ባዶዋን የመጣች – ትንሽ ልጅ ስትፈራ፣

ታዝቤህ ነበረ – ጋዜጠኛ አበራ።

አሁን ግን ሳስበው – ነገሩን በትኩረት

ጠላትን ሰብስቦ – ማርኮ ለማስቀረት፣

ወታደር መልምሎ – ጦር ሜዳ ከማዝመት

ሳትሻል አትቀርም – አንዷ የሀመር ሴት፣

———-

ያልተነካ …

ከአበራ ለማ

አወይ አለመያዝ – አለመነካት

ጡር ነው ወለላዬ – በነፍሴስ መምጣት፤

ጥግብ ፍርጥም ያለች – ደንደሮ ወጣት

ታስጨፍረኝ ነበር – ኢቫንጋዲ ስልት፤

ናቅፋ ቢበረታም – ይሄ ጋዜጠኛ

ከመሆን አልዳነም – የሐመር ምርኮኛ!!!

—— ||||||||||| ——

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    May 13, 2014 04:36 pm at 4:36 pm

    “ታመመልሽ ደነገጠልሽ ከቶ በዐይን ብቻ ሳይነካው አካልሽ
    ቀረጥ የሌለበት ወረት ያልዳሰሰው ደህና አንቴና ሰቅለሽ
    መሳሪያ ሳይዙ መማረኪያ ማን አስታጠቀሽ?
    አንቺ የሐመር ቆንጆ እንደምንድነሽ?
    ፍራቻው በርትቶ ብርክ ቢይዘው
    ዛፍ የለ አካባቢው መቋሚያ የሚሆነው
    እጁን ጀርባዋ ላይ ደገፍ ቢያደርገው
    ንዝርት በፈገግታ ፀሀይ መብረቅ አለው
    ፎቶም ይናገራል ፅፈውም አስታውሰው
    የሐመሯ ወለላዬ ውበትሽ ማራኪ አበራ ለማነው!?
    በለው!

    Reply
    • MINILIK says

      May 14, 2014 01:02 am at 1:02 am

      THANK YOU BELEW FOR YOUR POETIC EXPRESSION!…. I LIKED YOUR REACTION.

      Reply
  2. Bombu says

    May 15, 2014 03:42 pm at 3:42 pm

    ፈረሱም ሜዳውም ይሐው ከተባለ
    አስተያየት መስጠት ልብ እንደማለለ
    ተፈቅዶ ከሆነ ትዝብት በደፈናው
    የ ቦምቡ ማጠፊያ መዘርጊያውም ይሕው»

    የሐመርዋን ቆንጆ መሐል አስገብቶ
    ሰጣ ገባ መግባት ቃላተን አስማምቶ
    የጥንት ማስታወሻ እውጥቶ በፎቶ
    ትዛዝ ከተስጠ ከተባለ ጎልጉል
    ታሪክ መቼ ጠፍቶ ሁሌም የሚያማልል

    ስለዚሕ ይቀጠል ፈረሱና ጋሪ
    ጎልጉል እንደሜዳ በተዘዋዋሪ»

    ወለላዬ ያቅርብ ከማሕደር ፎቶ
    አበራም ይመልስ ብድሩን አሳክቶ

    Reply
  3. welelaye says

    May 19, 2014 11:50 am at 11:50 am

    ጌታው አቶ ቦንቡ – አድፍጠው አድፍጠው
    ያቀረቡት ሐሳብ – ፍላጎቴን ሳበው
    በዚህ አቀራረብ – ቃላት አፈሳሰስ
    ምንድነው ችግሩ – ቢሳተፉ እርስዎስ
    ታሪክ ገላልጨ – ማህደር ፈትሼ
    በቅርቡ እመጣለሁ – ዳግም ተመልሼ
    ስለዚህ ለመልሱ – ቀድመው ይሰናዱ
    ለግጥም ጨዋታ – ታጭተዋል እንዳንዱ

    Reply
  4. welelaye says

    May 19, 2014 11:54 am at 11:54 am

    የላይኛው ወደ ስድ ንባብነት ስለተቀየረ ነው የደገምኩት በለው ግሩም ቅኔ አዘል ግጥም ጽፈዋል በተለይ የመጨረሻው ማሰሪያዎ ሁላችንንም የሚአጣቅስ በመሆኑ ወስጥ አወቅ ሳይሆኑ አይቀሩም ብዬ ገመትኩ ከአክብሮት ምስጋና ጋር

    Reply
  5. በለው ! says

    May 21, 2014 04:38 am at 4:38 am

    ******************
    ኢትዮጵያዊነት ፅድቅ ክብር ድንቅ ነው
    ሐመርን ያላየ ሀመር ነዳሁ ያለው እንደ አበራ ለማ ነክቶ ይሞክረው !
    ውስጥ አወቅ ባልሆንም ዓይን ምሥክር ነው
    ወለላ የመሰለች የሚያበራ እያየሁ እንደምን ልለፈው? ከንፈሮቿን ገጥማ አንቴና ብትወጥር
    ምንይልክ ተደንቆ በለው! ቢል ቦንብ አድፍጦ ቢወረውር
    ወለላዋ ለማ አበራም ስንገጥም እየው ሲያምር!!
    ******************
    ከሰላምታ ጋር!! በቸር ይግጠመን በለው!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule