• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሐመሯ ቆንጆ

May 13, 2014 07:51 am by Editor 6 Comments

ደራሲና ጋዜጠኛ አበራ ለማ የሬድዮ ጋዜጠኛ በነበረበት ጊዜ ወደ ጋሞ ጎፋ ለስራ ሲሄድ፣ በድንገት ካጋጠመችው የሐመር ቆንጆ ጋር የተነሳው ፎቶ ነው።

ምልልሱን ያንብቡ።

      በደመቀ ፀሐይ

      ከወለላዬ

በቀን አጋማሽ ላይ – በደመቀ ፀሐይ

አካሏ ተጋልጦ – በግማሽ የሚታይ፣

የተዋበች ሐመር – መንገድ ላይ ብትወጣ

አዬ ጋዜጠኛው – የመጣበት ጣጣ፣

እሷ ግን እቀፊው – ሳሚው ሳሚው ብሏት

ጎኑ ብትጠጋው – አሹላ ያንን ጡት፣

የሱም አጉል ፍራት – የሷም አጉል ድፍረት

በደመቀ ፀሐይ

———-

ሰውም ይፈራል ወይ?

ከአበራ ለማ

ጌታ ወለላዬ – ምነዋ አልፈራ

መትረየስ ደግና – ፊቴ ተገትራ፤

ደ’ሞኮ አወጣጧ – ከጫካው ከዱሩ

መፍራት ይነሰኝ ወይ – እንግዳው ላገሩ፤

አያድርስ እንጂ ነው – touch down ብትለኝ

በዚህ በጠራራ – መጋኛስ ቢመታኝ፤

———-

hamer1ታዝቤህ ነበረ

ከወለላዬ

ዘምተህ የተመለስክ – በናቅፋ ተራራ

መሳሪያ የጨበክ – ከጀግኖቹ ጋራ፣

ባዶዋን የመጣች – ትንሽ ልጅ ስትፈራ፣

ታዝቤህ ነበረ – ጋዜጠኛ አበራ።

አሁን ግን ሳስበው – ነገሩን በትኩረት

ጠላትን ሰብስቦ – ማርኮ ለማስቀረት፣

ወታደር መልምሎ – ጦር ሜዳ ከማዝመት

ሳትሻል አትቀርም – አንዷ የሀመር ሴት፣

———-

ያልተነካ …

ከአበራ ለማ

አወይ አለመያዝ – አለመነካት

ጡር ነው ወለላዬ – በነፍሴስ መምጣት፤

ጥግብ ፍርጥም ያለች – ደንደሮ ወጣት

ታስጨፍረኝ ነበር – ኢቫንጋዲ ስልት፤

ናቅፋ ቢበረታም – ይሄ ጋዜጠኛ

ከመሆን አልዳነም – የሐመር ምርኮኛ!!!

—— ||||||||||| ——

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    May 13, 2014 04:36 pm at 4:36 pm

    “ታመመልሽ ደነገጠልሽ ከቶ በዐይን ብቻ ሳይነካው አካልሽ
    ቀረጥ የሌለበት ወረት ያልዳሰሰው ደህና አንቴና ሰቅለሽ
    መሳሪያ ሳይዙ መማረኪያ ማን አስታጠቀሽ?
    አንቺ የሐመር ቆንጆ እንደምንድነሽ?
    ፍራቻው በርትቶ ብርክ ቢይዘው
    ዛፍ የለ አካባቢው መቋሚያ የሚሆነው
    እጁን ጀርባዋ ላይ ደገፍ ቢያደርገው
    ንዝርት በፈገግታ ፀሀይ መብረቅ አለው
    ፎቶም ይናገራል ፅፈውም አስታውሰው
    የሐመሯ ወለላዬ ውበትሽ ማራኪ አበራ ለማነው!?
    በለው!

    Reply
    • MINILIK says

      May 14, 2014 01:02 am at 1:02 am

      THANK YOU BELEW FOR YOUR POETIC EXPRESSION!…. I LIKED YOUR REACTION.

      Reply
  2. Bombu says

    May 15, 2014 03:42 pm at 3:42 pm

    ፈረሱም ሜዳውም ይሐው ከተባለ
    አስተያየት መስጠት ልብ እንደማለለ
    ተፈቅዶ ከሆነ ትዝብት በደፈናው
    የ ቦምቡ ማጠፊያ መዘርጊያውም ይሕው»

    የሐመርዋን ቆንጆ መሐል አስገብቶ
    ሰጣ ገባ መግባት ቃላተን አስማምቶ
    የጥንት ማስታወሻ እውጥቶ በፎቶ
    ትዛዝ ከተስጠ ከተባለ ጎልጉል
    ታሪክ መቼ ጠፍቶ ሁሌም የሚያማልል

    ስለዚሕ ይቀጠል ፈረሱና ጋሪ
    ጎልጉል እንደሜዳ በተዘዋዋሪ»

    ወለላዬ ያቅርብ ከማሕደር ፎቶ
    አበራም ይመልስ ብድሩን አሳክቶ

    Reply
  3. welelaye says

    May 19, 2014 11:50 am at 11:50 am

    ጌታው አቶ ቦንቡ – አድፍጠው አድፍጠው
    ያቀረቡት ሐሳብ – ፍላጎቴን ሳበው
    በዚህ አቀራረብ – ቃላት አፈሳሰስ
    ምንድነው ችግሩ – ቢሳተፉ እርስዎስ
    ታሪክ ገላልጨ – ማህደር ፈትሼ
    በቅርቡ እመጣለሁ – ዳግም ተመልሼ
    ስለዚህ ለመልሱ – ቀድመው ይሰናዱ
    ለግጥም ጨዋታ – ታጭተዋል እንዳንዱ

    Reply
  4. welelaye says

    May 19, 2014 11:54 am at 11:54 am

    የላይኛው ወደ ስድ ንባብነት ስለተቀየረ ነው የደገምኩት በለው ግሩም ቅኔ አዘል ግጥም ጽፈዋል በተለይ የመጨረሻው ማሰሪያዎ ሁላችንንም የሚአጣቅስ በመሆኑ ወስጥ አወቅ ሳይሆኑ አይቀሩም ብዬ ገመትኩ ከአክብሮት ምስጋና ጋር

    Reply
  5. በለው ! says

    May 21, 2014 04:38 am at 4:38 am

    ******************
    ኢትዮጵያዊነት ፅድቅ ክብር ድንቅ ነው
    ሐመርን ያላየ ሀመር ነዳሁ ያለው እንደ አበራ ለማ ነክቶ ይሞክረው !
    ውስጥ አወቅ ባልሆንም ዓይን ምሥክር ነው
    ወለላ የመሰለች የሚያበራ እያየሁ እንደምን ልለፈው? ከንፈሮቿን ገጥማ አንቴና ብትወጥር
    ምንይልክ ተደንቆ በለው! ቢል ቦንብ አድፍጦ ቢወረውር
    ወለላዋ ለማ አበራም ስንገጥም እየው ሲያምር!!
    ******************
    ከሰላምታ ጋር!! በቸር ይግጠመን በለው!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
Copyright © 2026 · Goolgule