• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ጉደኛው መሪያችን

June 7, 2018 04:57 am by Editor 1 Comment

ዶ/ር አብይ አህመድን ምን እንላቸዋለን? ከአሁን በፊት መሪዎቻችንን ለመግለፅ የተጠቀምንባቸውን ቃላት ሁሉ የሚያልፉ ሆኑብኝ። ጉደኛ የሚለውን ቃል የመረጥኩት፥ ያልተለመደና ያልታየ ነገርን ስለሚገልፅ ነው። በሌሎች ስንቀና የኛም ተራ ደርሶ ይሆንን? ደቡብ አፍሪካ ማንዴላ ነበራት፤ ሕንድ ማህተመ ጋንዲ ነበራት፤ አሜሪካ ጆርጅ ዋሽንግተን ነበራት። ኢትዮጵያ ዶ/ር አብይ ደረሰውላት ይሆን?

ፋታ እንስጣቸው እያልን ስናወራ፤ እርሳቸው በድርጊታቸው አንዱን ሳናጣጥም ሌላ እየጨመሩ በመልካምነት ፋታ አሳጡን።

ቀድመው ያሞገሱትን ማማት ይቸግራል ብለን፤ ተስፋን በስጋት ሰንቀን ዳር ቆመን በጥርጣሬ የምናይ ሁሉ ጉድ ፈላብን። ዛሬ ዛሬ ተስፋ ስጋትን እያሸነፈ ከአጥናፍ እስከ አጥናፍ ለዶ/ር አብይ ድጋፍ እየጎረፈ ነው። ትላንት እንዳንጨራረስ እየፈራን ከዚህ አጣብቂኝ ማን ያወጣናል ስንል ነበር። የማይታለፍ የለም ያ ታለፈና፤ አሁን ዶ/ር አብይ በፍቅርና በይቅርታ ሁሉንም እየማረኩና እያስደመሙ፤ በደስታም እያሰከሩ በሚገርም አዲስ አካሄድ ኢትዮጵያን እያሻገሩ ይገኛሉ። ግን ቆም ብሎ ለሚያስተውል፤ ይህ ትዕይንት ከስጋና ደም ስራ በላይ ነው። የኢትዮጵያ አምላክ በምህረት እርሱ ራሱ ምድራችንን በፈውሱ እየጎበኘ እንደሆነ ለአስተዋይ ሰው ምንም ጥርጥር የለውም። አምላክ ደግሞ በስራ ላይ ሲሆን፤ ጠላት ለማሰናከል ሙከራ ያደርጋል እንጂ ፈጣሪን ያደናቅፈዋል ብሎ ማሰብ ሞኝነት ነው።

ያልተጠበቀው የኢትዮጵያዊነት ውበት ነገ እጅግ ደምቆ ሲበራ ልናይ ከሆነ፤ የማይጨበጥ ሕልም የሆነብን ዲሞክራሲ ነገ እንደ እለት እንጀራችን የምንመገበው ዕውነታ ሊሆን ከሆነ፤ ዛሬ የሚገፋፉትና የሚጠላለፉት ፖለቲከኞች ሁሉ በጠረጴዛ ዙሪያ ሆነው በወንድማማችነት መንፈስ የአስተሳሰብ ፍጭትና ፍትጊያ ሲያደርጉ አይተን ለመሆኑ እንዲህ ያሉ ድንቅየዎች ከየት መጡ እስክንል ድረስ የሚያስገርሙን ከሆነ፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሜዳውም ይሄው ፈረሱም ይሄው በሐቅ መሪህን ምረጥ ተብሎ ጉድ የሚባልበት ጊዜ ሊመጣ ከሆነ፤ እኛስ የየራሳችንን የኑሮ ብልሃታችንን እንደለመድነው ከዚህ በሁዋላ ማስኬድ እንዴት ይቻለናል?

ዛሬ አይደርስ መስሎን ራሳችንን ለኢትዮጵያ የተዘጋጀን እንደሆነ ለመጠየቅ ሀሳቡም የለንም። ዛሬ ዓይናችንን ዶ/ር አብይ ላይ አተኩረን ራሳችንን ከሃላፊነት አሰናብተናል። ቁምነገሩ ኢትዮጵያ ልትነሳና ልትደምቅ፤ ይህንንም መቀልበስ በማይቻል ጎዳና ላይ ዶ/ር አብይ በብልሃት የተሞላ የጥድፊያ ጉዞ ላይ ያሉ ይመስላል። ታዲያ ለዚህ የመታደስ ዘመን ራሳችንን በመስዋዕትነት ለመስጠት እያሰብን ነን ወይ? ኢትዮጵያ የሚሞትላት ሳይሆን በመስዋዕትነት በመኖር ለችግሯ ሊደርስላት የሚችል ዜጋ የምትፈልግበት ጊዜ እየመጣ ነው። ለመልካም ኑሮ ሀገራችንንና ምድራችንን ትተን የተሰደድን ሁሉ፤ ለምድራችን ፈውስ ለመሆን ምቾትን ንቀን፥ ከሕዝባችን ጋር መከራ በመቀበል የደስታው ተካፋይ ለመሆን ለኢትዮጵያ ዝግጅት ማድረግ የምጀምርበት ወቅት ነው። በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉትም ቢሆኑ በፅድቅና በእውነት ለሕዝብ አገልጋይ በመሆን ራስን ከምቾት አፋተው ራሳቸውን አሳልፈው በመስጠት የደስታው ተካፋይ ለመሆን ለኢትዮጵያ ዝግጅት የሚያደርጉበት ጊዜ ነው።

ዶ/ር አብይ ለኢትዮጵያ እየሰሩ ያሉትን እየወደድንና እያወደስን ባለበት በዚህ ወቅት፤ ለዶ/ር አብይ ኢትዮጵያ ራሳችንን በማዘጋጀት እንዲሆን ፈጣሪ ይርዳን። በመስዋዕትነት በምድረ ኢትዮጵያ በስራ ተጠምደን፤ የሀገራችንን ታሪክ በራሳችን ትውልድ ዘመነ ጊዜ ለውጠን በማየት ከዚህ ዓለም አልፈን፤ ዶ/ር አብይ እንዳሉት ያኔ እኛም በክብር ኢትዮጵያ እንሆናለን።

ዶ/ር አብይ “ፈጣሪ ኢትዮጵያን ይባርክ” ብለው ሲያውጁ፤ ያኔ የኢትዮጵያን ዕጣ ፈንታ ለሰማይ አደራ ሰጥተው ራሳችንን ለተዐምሩ እንድናዘጋጅ ልባችንን ማነሳሳታቸው ነበር። እንደተባለውም ፈጣሪ ኢትዮጵያን ሊባርክና ያሳለፍነውን የመከራ ዘመን ሊያስረሳን የተስፋ ጭላንጭል ከጊዜ ወደ ጊዜ ቦግ እያለ እየተጨመረ በመብራት ላይ ይገኛል። ለዚህ አስደናቂ የታሪክ ዕድል ራሳችንን ለኢትዮጵያ ለማዘጋጀት መዘርጋት የሚገባን ይመስለኛል። ዶ/ር አብይ የአምላክን በረከት ከመጥራት አኳያ በንፅፅር የንግግራቸው ማሳረጊያ አድርገው የሚጠቀሙበት ሌላ ሀሳብ አላቸው። ያም፦ “ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራ ተከብራና በልፅጋ ለዘላለም ትኑር”  የሚለው ቁምነገር ነው። ፈጣሪም ልመናችንን ሰምቶ እየጎበኘን ባለበት ሁኔታ፤ ዶ/ር አብይም ታማኝ ሆነው ራሳቸውን ለተባረከች ኢትዮጵያ ራሳቸውን እየሰጡ ባለበት ሁኔታ፤ እኛስ ለኢትዮጵያ ትንሳዔ ጥረት ለማድረግ ተዘጋጅተናል ወይ?

እግዚአብሔር ኢትዮጵያን አሰበ። ይጎበኛታልም።

ዶ/ር ዘላለም እሸቴ

ኢሜል፦ ethioStudy@gmail.com


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. samuel says

    June 14, 2018 06:05 pm at 6:05 pm

    ቀድሞ ማመስገን ኀላ ለማማት ይቸግራል እስኪ 1ዐመት ሳይታይ ይሄንን ያህል ለምን እሄን እንዳደረገ እናረጋግጥ እስኪ

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule