• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“በአንድ ቀን ትምህርት ፎቶ አንሺ ሆኜ ቁጭ አልኩ” የ69 ዓመቷ አረጋዊ ወ/ሮ ባዩሽ

October 27, 2013 09:11 am by Editor Leave a Comment

ካዛንቺስ አካባቢ በልመና የሚተዳደሩ አንድ አይነሥውር ሽማግሌ አሉ፡፡ የሚለምኑት ከካዛንቺስ ስድስት ኪሎና ፒያሳ ለመሄድ ታክሲ ከሚጠብቁ ተሳፋሪዎች ነው፡፡ አንድ ቀን በእለቱ የለመኑትን ገንዘብ ታክሲ እየጠበቅሁ ባለሁበት ቁጠርልኝ አሉኝ፡፡ እስከ ቀኑ 11 ሰዓት አርባ ብር ለምነዋል፡፡ በሌላ ቀን ተመልሼ ጠየቅኋቸው። በልመና ከሚያገኙት ገንዘብ ልጃቸውን ኮሌጅ አስተምረዋል፡፡ ልጃቸው ሥራ ከያዘ ከዓመታት በኋላም ግን ልመና አላቆሙም፡፡ አሁንም እዚያው ካዛንቺስ እየለመኑ ነው፡፡

“ለምን ልመና አያቆሙም?” አልኳቸው፡፡

“ምን ላድርግ ቁጭ ልበል እንዴ?” በማለት እኔኑ መልሰው ጠየቁኝ፡፡ እዚያው ካዛንቺስ የሚለምኑ ሌላ አረጋዊ ከፍተኛ የእይታ ችግር አለባቸው፡፡ በምፅዋት የሚያገኙትን ሳንቲም ይዳብሱና አምስት ሳንቲም ከሆነ መልሰው ይወረውሩታል፡፡
በአንፃሩ የእይታም የአቅምም ችግር ያለባቸው የማይመስሉ አንዲት አሮጊት፤ ኡራኤል ቤተክርስትያን አካባቢ ከጥቂት ወራት በፊት አገኘሁ፡፡ የእሳቸው የአለማመን ዘይቤ ከተለመደው የተለየ ነው፡፡

“ቤቴ ልደታ ነው፤ መሳፈርያ አልያዝኩም” አሉኝ፡፡
“ኑ፤ እኔ እከፍልሎታለሁ፤ በዚያ አቅጣጫ ነው የምሄድው” አልኳቸው፡፡
“ባትሰጥ አትተወውም” ብለው እየተቆጡ ትተውኝ ሄዱ፡፡

ከቀኑ 11 ሰዓት ግድም ብሔራዊ ትያትር አካባቢ ሲለምኑ ያገኘኋቸው መስራት የሚችሉ ሴት ለልመናው ምክንያት የሰጡት “ልጄ ታሞብኝ ማሳከሚያ አጣሁ” የሚል ነው፡፡ እኒህኑ ሴት ከምሽቱ አንድ ሰዓት አካባቢ ኡራኤል ቤተክርስትያን አካባቢ ሲለምኑ አገኘኋቸው፡፡

አሁን ደግሞ “ገንዘቤን ዘረፉኝ” ሲሉ ሰማኋቸው፡፡

በየቦታው መሥራት እየቻሉ ልመና የወጡ አረጋውያን አያሌ ናቸው፡፡ አንዳንዶቹ አመል ሆኖባቸው ነው እንጂ ሠርተው በገቢ ራሳቸውን መደጐም ይችላሉ፡፡ ለዚህም ይመስላል “ኸልፕ ኤጅ ኢንተርናሽናል”፣ የኢትዮጵያ አረጋውያን ማህበር እና ሌሎች አጋሮቻቸው ባለፈው ሳምንት አረጋውያን ሰርተው መጠቀም የሚችሉ መሆኑን የሚያሳይ የአራት ቀናት አውደርእይ ቦሌ አካባቢ በትሮፒካል ጋርደን ያዘጋጁት፡፡ ሰርተው ራሳቸውን በመደጐማቸው ደስተኞች መሆናቸውን ያነጋገርኳቸው አረጋውያን ይገልፃሉ፡፡

በ1993 ዓ.ም የተመሰረተው የኢትዮጵያ አረጋውያን ማህበር፤ 38 አባል ማህበራት ያሉት ሲሆን “ጤነኛ አረጋውያን ሰርተው መኖር ይችላሉ” በሚል መርህ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል፡፡ ማህበሩ፤ በአረጋውያን ሊተገበሩ የሚችሉ ፕሮጀክቶችን የሚቀርፅ ሲሆን አረጋውያንን በስልጠናና በልምድ ልውውጥ ያግዛል፡፡

የልምድ ልውውጡ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት ይከናወናል፡፡ ባለፈው ዓመት ለምሳሌ በእንግሊዝ የፖትስማውዝ ከተማ አረጋውያን ማህበር የአዲስ አበባ አቻውን ለልምድ ልውውጥ ጠርቶ ነበር፡፡ ነገር ግን ለማህበሩ ፕሮጀክት ኦፊሰር ብቻ ሲፈቀድ የአረጋውያን ማህበር ፕሬዚደንቱ፤ “የከተማ ቦታ የለዎትም፤ ጡረታዎም ሃያ ፓውንድ አይሞላም፤ ሄደው ሊቀሩ ይችላሉ” በሚል የእንግሊዝ ኤምባሲ ቪዛ መከልከሉ ቅሬታ አሳድሯል፡፡ እናም የፖትስማውዙ ማህበር ለእንግሊዝ ፓርላማ ክስ አቅርቧል፤ ምላሹ ባይታወቅም፡፡ ቪዛ የተሰጠው ፕሮጀክት ኦፊሰር ግን እንግሊዝ ቀርቷል፡፡

የአረጋውያን ማህበር አባላት፤ ህብረተሰቡ ለአረጋውያን ያለው አመለካከት የተዛባ መሆኑ ችግራቸውን የከፋ እንዳደረገባቸው ይናገራሉ፡፡ ይሄን አመለካከት ለማስወገድም ትግል ላይ ናቸው፡፡ የህብረተሰቡ የተዛባ አመለካከት እንዲወገድ እየሰራን ነው የምትለው የ”ኼልፕ ኤጅ ኢንተርናሽናል” የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ኤርና ምንተስኖት ሃንዝ፤ በአረጋውያን ላይ የሚደርስባቸው መብት ረገጣ እንዲቆም ፊርማ እያሰባሰቡ መሆኑንና ቅሬታቸውን ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እንደሚያቀርቡ ተናግራለች፤ ሕግ እንዲበጅለት፡፡በሰሞኑ አውደርእይ ብዙ መንቀሳቀስ የማይችሉ አረጋውያን አትክልት ውሃ ሲያጠጡ፣ ለራሳቸው ምግብ ለማሰናዳት ሽንኩርትና ድንች ሲልጡ የሚያሳዩ ፎቶግራፎች ቀርበዋል፡፡ ሥራዎቻቸው ከቀረቡላቸው ማህበራት አንዱ “እንረዳዳ” የአረጋውያን ማህበር ሲሆን አረጋውያን የተረጅነት ስሜት እንዳይሰማቸው እያደረግሁ ነው የሚለው ማህበሩ፤ የተወሰነ ሥራ እንደየአቅማቸው እየሰሩ መሆኑን ገልጿል፡፡ የማህበሩ አባላት የሰሯቸው የሽመና ውጤቶችም በአውደርእዩ ላይ ቀርበዋል። አረጋውያኑ እንደየስራቸው መጠንም ገንዘብ ያገኛሉ፡፡ ጋቢ የሰራ የጋቢ ዋጋ፣ ፎጣ የሰራ የፎጣ ዋጋ ያገኛል፡፡ አባላቱ ዱቄት፣ ዘይት፣ ሳሙናና የመሳሰሉትም ይሰጣቸዋል፡፡ ተቀጥረው የመስራት አቅም ያላቸው ደግሞ በወጥ ቤትነት፣ በጥበቃ፣ በአትክልተኝነትና በፅዳት ሥራዎች እንደሚቀጠሩ ለማወቅ ተችሏል፡፡የአረጋውያኑ ምርቶች ወደ ገበያው ገብተው የሚሸጡበት ሁኔታ የጠየቅኋት የአውደርዕዩ አስጐበኚ፤ “በባዛር እና በዕቁብ ይሸጣል፡፡ ለምሳሌ ብርጭቆ ፋብሪካ በወር ስምንት ጋቢ ይገዛል” ብላለች፡፡

የ75 ዓመቱ አረጋዊ አቶ መኩርያ፤ የጉለሌ አካባቢ ነዋሪ ሲሆኑ በፊት ገበሬ ነበሩ፡፡ አሁን ግን ሸማኔ ሆነዋል፡፡ በቀን ሦስት ክንድ እና ከዚያ በላይ እየሸመኑ በሳምንት አንድ ጋቢ እንደሚያደርሱ የተናገሩት አረጋዊው፤ “እኔ ተሯሩጬ መሸጥ ስለማልችል ማህበሬ ነው የሚሸጥልኝ” ብለዋል፡፡

ሌላው የ70 ዓመት አረጋዊ አቶ ኃይሌ ሀብተማርያም፤ ከበቾ አካባቢ ያርሱ ነበር፡፡ አቅም እያነሳቸው ሲሄዱ እየተረዱም ቢሆን አምራች አረጋዊ በመሆን አንዳንድ ወጪዎቻቸውን ራሳቸው እንደሚችሉ ገልፀውልኛል፡፡

“ውድ የአረጋውያን በጐ አድራጐት ድርጅት” በየወሩ ለእያንዳንዱ አረጋዊ 100 ብር የሚሰጥ ሲሆን አረጋውያኑ አትክልትና ፍራፍሬ በመነገድ ተጨማሪ ገቢ ያገኛሉ፡፡

የ69 ዓመቷ ወይዘሮ ባዩሽ ወልደአረጋይ፤ እድሜያቸው ሳያግዳቸው ፎቶ አንሺ ሆነዋል፡፡
“ፎቶ ማንሳት መቼ ጀመሩ?” ብዬ ጠየቅኋቸው፤ ወይዘሮ ባዩሽን፡፡ “እዚህ አረጋውያን ድርጅት ውስጥ እየሰራሁ “ኼልፕኤጅ ኢንተርናሽናል” ለልምድ ልውውጥ የውጭ ሰዎች አመጣ፡፡ በማግስቱ ካሜራ ሰጡን፤ ለማስተማር፡፡ እዚያው አስተማሩን። ሦስት አረጋውያን ነን በእለቱ ስልጠና የተሰጠን። አሰልጣኛችን እንዴት እንደምናነሳ አሳይቶን “ነገ ታሳዩኛላችሁ” ብሎ ሄደ፡፡ ራሳችን ያሳነውን የታጠበ ፎቶም ለኛ አሳይቶን ካሜራው ለእያንዳንዳችን ቀረ። ይኸውልህ ልጄ፤ በአንድ ቀን ትምህርት ፎቶ አንሺ ሆኜ ቁጭ አልኩ፡፡ ከዚያን ወዲህ ሠርግ ላይ ‘እቴቴ እስቲ ፎቶ አንሺን’ ተብያለሁ”

“እና ለወደፊት ምን አሰቡ ታዲያ?”
“ጥሩ ነው፤ ደግሞም ፎቶ እያነሳሁ ገንዘብ ማግኘቱም ይጠቅማል፡፡ እግዚአብሔር ካለ በዚህ ካሜራዬ ተአምር እሰራበታለሁ፡፡ ትልቅ ሥራ እሰራበታለሁ፤ ራሴንም እደጉምበታለሁ” ብለዋል፤ ወ/ሮ ባዩሽ፡፡

ከ86 ሚ. የኢትዮጵያ ሕዝብ ውስጥ አምስት ሚሊዮን ያህሉ አረጋውያን እንደሆኑ የ”ኼልፕ ኤጅ” መረጃ ይጠቁማል፡፡ (መልካሙ ተክሌ: አዲስ አድማስ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Social Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule