• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ

January 11, 2023 03:47 pm by Editor Leave a Comment

“ፓርላማ” ተብሎ ሲጠራ በነበረው የኢህአዴግ ሸንጎ በቅንነትና በታማኝነት ሲያገለግሉ የነበሩት ተሾመ ቶጋ አሁን ደግሞ የቀድሞ ጌቶቻቸውን መልሶ የማቋቋም ኃላፊነት ተሰጥቷቸዋል።

በነበራቸው ቆራጥ የካድሬ ስብዕና ከአፈ ጉባዔነት ወደ አምባሳደርነት የተሸጋገሩት ተሾመ ቶጋ ላለፉት አራት ዓመታት በቻይና አምባሳደር ነበሩ። ከቻይና በፊትም እንደ ሌሎቹ የኢህአዴግ ካድሬዎች ባሳዩት ታማኝነት አምባሳደር ተብለው በተለያዩ አገራት ሲንከራተቱ ነበር።

በፓርላማው ቆይታቸው ከትህነግ ሰዎች እጅግ በበለጠ ለሥርዓቱ ታማኝ በመሆን የተቃዋሚ ፓርቲ የፓርላማ አባሎችን በማሰቃየት ደርሰው እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትዝታ ነው። የተቃዋሚ ፓርቲ የፓርላማ አባላት ሲናገሩ በማዋከብ ከዚያም አልፎ ከሚሰጣቸው ጊዜ ላይ በመቁረጥ እንዳይናገሩ፣ ሃሳባቸውን ሳይጨርሱ የመናገሪያውን ድምጽ በማጥፋት፣ እየተናገሩ እያለ ጣልቃ በመግባት ንግግራቸውን እንዲያስተካክሉ በመነታረክ፣ ንግግራቸው ከአጀንዳው ጋር የተያያዘ አይደለም በማለት አፍ በመካፈት፣ በበርካታ የመብት ገፈፋ ተግባር ላይ ተሠማርተው እንደነበር የብዙዎች ትዝታ ነው። 

ከዚህም የተነሳ የከተማ ፌዘኞች ቴሌ ይሸጠው የነበረውን የ፲ ብር ካርድ ተሾመ ቶጋ እያለ ይጠራው ነበር፤ የሞቀ ወሬ ላይ ምንም ማስጠንቀቂያ ሳይሰጥ ደቂቃው ሞላ በሚል ይቆርጠው ስለነበር። በተለይ ጅንጀና ላይ ያለ ወጣት እንዴት እንደሚሰማው በመገመት የተቃዋሚ ፓርቲ የፓርላማ አባላት በተሾመ የደረሰባቸውን መረዳት ይቻላል።

ቀድሞ “አምባሳደር” ሲባሉ የነበሩት ተሾመ “አቶ” ተብለው፤ እጅግ አሰልቺና አድካሚ ብዙ ጭቅጭቅ የበዛበትን የመልሶ ማቋቋም ሥራ ይሠራሉ። ይህንን በድል ሲጨርሱ አቶ ተብለው ጡረታ ይወጡና እሳቸውም በጡረተኛነት ይቋቋማሉ።

በዚህ አጋጣሚ ቀድሞ አምባሳደር የነበሩ ካድሬዎች ከሹመት ሥልጣናቸው ሲለቅቁ “አቶ” ወይም “ወይዘሮ” ወይም “ወይዘሪት” ተብለው ሊጠሩ ይገባል እላለሁ። በትምህርት ያገኙትና የራሳቸው ውጤት የሆነ ማዕረግ አይደለም። ለምሳሌ አቶ ተሾመ ቀድሞ ዛፍ ቆራጭ ወይም አሣ አጥማጅ ቢሆኑ አሁን ሲጠሩ የቀድሞው ዛፍ ቆራጭ ወይም አሣ አጥማጅ፣ የቀድሞ የተከበሩ አፈ ጉባዔ፣ አምባሳደር ተብለው አይጠሩም። ስለዚህ ለተሾመ ብቻ ሳይሆን ለሌሎችም ይህ አሠራር ተግባራዊ እንዲደረግ ሃሳብ እሰጣለሁ።

ስምን መልአክ ያወጣዋልና ለተሾመ መልካም ሹመት፤ መልካም አቶነት እመኛለሁ።

የተከበርኩ ነኝ ከፓርላማ ሠፈር


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣበ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Right Column Tagged With: china, teshome toga

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule