• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ

January 11, 2023 03:47 pm by Editor Leave a Comment

“ፓርላማ” ተብሎ ሲጠራ በነበረው የኢህአዴግ ሸንጎ በቅንነትና በታማኝነት ሲያገለግሉ የነበሩት ተሾመ ቶጋ አሁን ደግሞ የቀድሞ ጌቶቻቸውን መልሶ የማቋቋም ኃላፊነት ተሰጥቷቸዋል።

በነበራቸው ቆራጥ የካድሬ ስብዕና ከአፈ ጉባዔነት ወደ አምባሳደርነት የተሸጋገሩት ተሾመ ቶጋ ላለፉት አራት ዓመታት በቻይና አምባሳደር ነበሩ። ከቻይና በፊትም እንደ ሌሎቹ የኢህአዴግ ካድሬዎች ባሳዩት ታማኝነት አምባሳደር ተብለው በተለያዩ አገራት ሲንከራተቱ ነበር።

በፓርላማው ቆይታቸው ከትህነግ ሰዎች እጅግ በበለጠ ለሥርዓቱ ታማኝ በመሆን የተቃዋሚ ፓርቲ የፓርላማ አባሎችን በማሰቃየት ደርሰው እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትዝታ ነው። የተቃዋሚ ፓርቲ የፓርላማ አባላት ሲናገሩ በማዋከብ ከዚያም አልፎ ከሚሰጣቸው ጊዜ ላይ በመቁረጥ እንዳይናገሩ፣ ሃሳባቸውን ሳይጨርሱ የመናገሪያውን ድምጽ በማጥፋት፣ እየተናገሩ እያለ ጣልቃ በመግባት ንግግራቸውን እንዲያስተካክሉ በመነታረክ፣ ንግግራቸው ከአጀንዳው ጋር የተያያዘ አይደለም በማለት አፍ በመካፈት፣ በበርካታ የመብት ገፈፋ ተግባር ላይ ተሠማርተው እንደነበር የብዙዎች ትዝታ ነው። 

ከዚህም የተነሳ የከተማ ፌዘኞች ቴሌ ይሸጠው የነበረውን የ፲ ብር ካርድ ተሾመ ቶጋ እያለ ይጠራው ነበር፤ የሞቀ ወሬ ላይ ምንም ማስጠንቀቂያ ሳይሰጥ ደቂቃው ሞላ በሚል ይቆርጠው ስለነበር። በተለይ ጅንጀና ላይ ያለ ወጣት እንዴት እንደሚሰማው በመገመት የተቃዋሚ ፓርቲ የፓርላማ አባላት በተሾመ የደረሰባቸውን መረዳት ይቻላል።

ቀድሞ “አምባሳደር” ሲባሉ የነበሩት ተሾመ “አቶ” ተብለው፤ እጅግ አሰልቺና አድካሚ ብዙ ጭቅጭቅ የበዛበትን የመልሶ ማቋቋም ሥራ ይሠራሉ። ይህንን በድል ሲጨርሱ አቶ ተብለው ጡረታ ይወጡና እሳቸውም በጡረተኛነት ይቋቋማሉ።

በዚህ አጋጣሚ ቀድሞ አምባሳደር የነበሩ ካድሬዎች ከሹመት ሥልጣናቸው ሲለቅቁ “አቶ” ወይም “ወይዘሮ” ወይም “ወይዘሪት” ተብለው ሊጠሩ ይገባል እላለሁ። በትምህርት ያገኙትና የራሳቸው ውጤት የሆነ ማዕረግ አይደለም። ለምሳሌ አቶ ተሾመ ቀድሞ ዛፍ ቆራጭ ወይም አሣ አጥማጅ ቢሆኑ አሁን ሲጠሩ የቀድሞው ዛፍ ቆራጭ ወይም አሣ አጥማጅ፣ የቀድሞ የተከበሩ አፈ ጉባዔ፣ አምባሳደር ተብለው አይጠሩም። ስለዚህ ለተሾመ ብቻ ሳይሆን ለሌሎችም ይህ አሠራር ተግባራዊ እንዲደረግ ሃሳብ እሰጣለሁ።

ስምን መልአክ ያወጣዋልና ለተሾመ መልካም ሹመት፤ መልካም አቶነት እመኛለሁ።

የተከበርኩ ነኝ ከፓርላማ ሠፈር


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣበ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Right Column Tagged With: china, teshome toga

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule