• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ

January 11, 2023 03:47 pm by Editor Leave a Comment

“ፓርላማ” ተብሎ ሲጠራ በነበረው የኢህአዴግ ሸንጎ በቅንነትና በታማኝነት ሲያገለግሉ የነበሩት ተሾመ ቶጋ አሁን ደግሞ የቀድሞ ጌቶቻቸውን መልሶ የማቋቋም ኃላፊነት ተሰጥቷቸዋል።

በነበራቸው ቆራጥ የካድሬ ስብዕና ከአፈ ጉባዔነት ወደ አምባሳደርነት የተሸጋገሩት ተሾመ ቶጋ ላለፉት አራት ዓመታት በቻይና አምባሳደር ነበሩ። ከቻይና በፊትም እንደ ሌሎቹ የኢህአዴግ ካድሬዎች ባሳዩት ታማኝነት አምባሳደር ተብለው በተለያዩ አገራት ሲንከራተቱ ነበር።

በፓርላማው ቆይታቸው ከትህነግ ሰዎች እጅግ በበለጠ ለሥርዓቱ ታማኝ በመሆን የተቃዋሚ ፓርቲ የፓርላማ አባሎችን በማሰቃየት ደርሰው እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትዝታ ነው። የተቃዋሚ ፓርቲ የፓርላማ አባላት ሲናገሩ በማዋከብ ከዚያም አልፎ ከሚሰጣቸው ጊዜ ላይ በመቁረጥ እንዳይናገሩ፣ ሃሳባቸውን ሳይጨርሱ የመናገሪያውን ድምጽ በማጥፋት፣ እየተናገሩ እያለ ጣልቃ በመግባት ንግግራቸውን እንዲያስተካክሉ በመነታረክ፣ ንግግራቸው ከአጀንዳው ጋር የተያያዘ አይደለም በማለት አፍ በመካፈት፣ በበርካታ የመብት ገፈፋ ተግባር ላይ ተሠማርተው እንደነበር የብዙዎች ትዝታ ነው። 

ከዚህም የተነሳ የከተማ ፌዘኞች ቴሌ ይሸጠው የነበረውን የ፲ ብር ካርድ ተሾመ ቶጋ እያለ ይጠራው ነበር፤ የሞቀ ወሬ ላይ ምንም ማስጠንቀቂያ ሳይሰጥ ደቂቃው ሞላ በሚል ይቆርጠው ስለነበር። በተለይ ጅንጀና ላይ ያለ ወጣት እንዴት እንደሚሰማው በመገመት የተቃዋሚ ፓርቲ የፓርላማ አባላት በተሾመ የደረሰባቸውን መረዳት ይቻላል።

ቀድሞ “አምባሳደር” ሲባሉ የነበሩት ተሾመ “አቶ” ተብለው፤ እጅግ አሰልቺና አድካሚ ብዙ ጭቅጭቅ የበዛበትን የመልሶ ማቋቋም ሥራ ይሠራሉ። ይህንን በድል ሲጨርሱ አቶ ተብለው ጡረታ ይወጡና እሳቸውም በጡረተኛነት ይቋቋማሉ።

በዚህ አጋጣሚ ቀድሞ አምባሳደር የነበሩ ካድሬዎች ከሹመት ሥልጣናቸው ሲለቅቁ “አቶ” ወይም “ወይዘሮ” ወይም “ወይዘሪት” ተብለው ሊጠሩ ይገባል እላለሁ። በትምህርት ያገኙትና የራሳቸው ውጤት የሆነ ማዕረግ አይደለም። ለምሳሌ አቶ ተሾመ ቀድሞ ዛፍ ቆራጭ ወይም አሣ አጥማጅ ቢሆኑ አሁን ሲጠሩ የቀድሞው ዛፍ ቆራጭ ወይም አሣ አጥማጅ፣ የቀድሞ የተከበሩ አፈ ጉባዔ፣ አምባሳደር ተብለው አይጠሩም። ስለዚህ ለተሾመ ብቻ ሳይሆን ለሌሎችም ይህ አሠራር ተግባራዊ እንዲደረግ ሃሳብ እሰጣለሁ።

ስምን መልአክ ያወጣዋልና ለተሾመ መልካም ሹመት፤ መልካም አቶነት እመኛለሁ።

የተከበርኩ ነኝ ከፓርላማ ሠፈር


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣበ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Right Column Tagged With: china, teshome toga

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሤራ አክሻፊው ጎንደር ለሦስተኛ ጊዜ ታሪክ ሠራ May 10, 2023 09:25 am
  • ማር በከፍተኛ ደረጃ የኮንትሮባንድ ሰለባ ሆኗል May 9, 2023 09:24 am
  • ኦነግ በኦሮሚያ ሪፈረንደም እንዲካሄድ መጠየቁ ለሰላም ንግግሩ ዕንቅፋት ሆነ May 4, 2023 01:12 am
  • መረጃ ቲቪ ያጋራው አሳሳች መረጃ May 2, 2023 12:37 pm
  • “ከፈጣሪ በታች መከላከያ የሁላችን ዋስ ጠበቃ ነው፤ ትልቅ ይቅርታ እንጠይቃለን” April 13, 2023 10:19 am
  • በትግራይ የ”ልጆቻችን የት ናቸው?” ጥያቄ እየተሰማ ነው April 13, 2023 08:56 am
  • በትህነግ የፈረሰው የአክሱም ኤርፖርት ያስከተለው ዘርፈብዙ ኪሣራ April 13, 2023 03:21 am
  • “የከተማው ነዋሪ በመሰላቸቱ ተፈናቃዮች ከፍተኛ የምግብ ችግር” ገጥሟቸዋል April 12, 2023 09:23 am
  • ከዕድሜ ልክ እስከ 20 ዓመት ቅጣት ተበይኖባቸዋል April 11, 2023 02:58 pm
  • የኡጋንዳ የክልሎች ሚኒስትር በቆርቆሮ ሌብነት ተጠርጥረው ታሰሩ April 10, 2023 03:59 pm
  • ታከለ ከተነሳ በኋላ የመዐድን ሌቦች እየተያዙ ነው April 6, 2023 02:53 pm
  • አገር ለማተራመስ ያለመ የምሁራን፣ የሚዲያ ባለቤቶችና አክቲቪስቶች ህቡዕ ቡድን ተያዘ April 4, 2023 10:07 am
  • በ10 ዓመት ውስጥ ከ44 ቢሊየን ዶላር በላይ ሸሽቷል April 4, 2023 09:26 am
  • አየር ጨብጦ አሁን ያለውን መንግሥት ከሥልጣን ልቀቁ አይሆንም March 29, 2023 09:47 am
  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule