• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ

January 11, 2023 03:47 pm by Editor Leave a Comment

“ፓርላማ” ተብሎ ሲጠራ በነበረው የኢህአዴግ ሸንጎ በቅንነትና በታማኝነት ሲያገለግሉ የነበሩት ተሾመ ቶጋ አሁን ደግሞ የቀድሞ ጌቶቻቸውን መልሶ የማቋቋም ኃላፊነት ተሰጥቷቸዋል።

በነበራቸው ቆራጥ የካድሬ ስብዕና ከአፈ ጉባዔነት ወደ አምባሳደርነት የተሸጋገሩት ተሾመ ቶጋ ላለፉት አራት ዓመታት በቻይና አምባሳደር ነበሩ። ከቻይና በፊትም እንደ ሌሎቹ የኢህአዴግ ካድሬዎች ባሳዩት ታማኝነት አምባሳደር ተብለው በተለያዩ አገራት ሲንከራተቱ ነበር።

በፓርላማው ቆይታቸው ከትህነግ ሰዎች እጅግ በበለጠ ለሥርዓቱ ታማኝ በመሆን የተቃዋሚ ፓርቲ የፓርላማ አባሎችን በማሰቃየት ደርሰው እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትዝታ ነው። የተቃዋሚ ፓርቲ የፓርላማ አባላት ሲናገሩ በማዋከብ ከዚያም አልፎ ከሚሰጣቸው ጊዜ ላይ በመቁረጥ እንዳይናገሩ፣ ሃሳባቸውን ሳይጨርሱ የመናገሪያውን ድምጽ በማጥፋት፣ እየተናገሩ እያለ ጣልቃ በመግባት ንግግራቸውን እንዲያስተካክሉ በመነታረክ፣ ንግግራቸው ከአጀንዳው ጋር የተያያዘ አይደለም በማለት አፍ በመካፈት፣ በበርካታ የመብት ገፈፋ ተግባር ላይ ተሠማርተው እንደነበር የብዙዎች ትዝታ ነው። 

ከዚህም የተነሳ የከተማ ፌዘኞች ቴሌ ይሸጠው የነበረውን የ፲ ብር ካርድ ተሾመ ቶጋ እያለ ይጠራው ነበር፤ የሞቀ ወሬ ላይ ምንም ማስጠንቀቂያ ሳይሰጥ ደቂቃው ሞላ በሚል ይቆርጠው ስለነበር። በተለይ ጅንጀና ላይ ያለ ወጣት እንዴት እንደሚሰማው በመገመት የተቃዋሚ ፓርቲ የፓርላማ አባላት በተሾመ የደረሰባቸውን መረዳት ይቻላል።

ቀድሞ “አምባሳደር” ሲባሉ የነበሩት ተሾመ “አቶ” ተብለው፤ እጅግ አሰልቺና አድካሚ ብዙ ጭቅጭቅ የበዛበትን የመልሶ ማቋቋም ሥራ ይሠራሉ። ይህንን በድል ሲጨርሱ አቶ ተብለው ጡረታ ይወጡና እሳቸውም በጡረተኛነት ይቋቋማሉ።

በዚህ አጋጣሚ ቀድሞ አምባሳደር የነበሩ ካድሬዎች ከሹመት ሥልጣናቸው ሲለቅቁ “አቶ” ወይም “ወይዘሮ” ወይም “ወይዘሪት” ተብለው ሊጠሩ ይገባል እላለሁ። በትምህርት ያገኙትና የራሳቸው ውጤት የሆነ ማዕረግ አይደለም። ለምሳሌ አቶ ተሾመ ቀድሞ ዛፍ ቆራጭ ወይም አሣ አጥማጅ ቢሆኑ አሁን ሲጠሩ የቀድሞው ዛፍ ቆራጭ ወይም አሣ አጥማጅ፣ የቀድሞ የተከበሩ አፈ ጉባዔ፣ አምባሳደር ተብለው አይጠሩም። ስለዚህ ለተሾመ ብቻ ሳይሆን ለሌሎችም ይህ አሠራር ተግባራዊ እንዲደረግ ሃሳብ እሰጣለሁ።

ስምን መልአክ ያወጣዋልና ለተሾመ መልካም ሹመት፤ መልካም አቶነት እመኛለሁ።

የተከበርኩ ነኝ ከፓርላማ ሠፈር


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣበ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Right Column Tagged With: china, teshome toga

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule