• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የጎልጉል ቅምሻ

December 31, 2012 01:14 pm by Editor 1 Comment

ፍቅር ቁመት አይወስነውም

የዓለማችን ረጅም ወጣት የከንፈር ወዳጅ የሆነው የ22ዓመቱ ብራዚላዊ ከፍቅረኛው ጋር ያለው ግንኙነት እጅግ አስደሳች እንደሆነ ገለጸ፡፡ ዕድሜዋ 17ዓመትና ቁመትዋ 6ጫማ ከ8ኢንች (2.1ሜትር) የምትረዝመው ኤሊሳኒ ሲልቫ ዕድገቷን የሚቆጣጠረው ዕጢ ላይ ባጋጠማት ችግር ምክንያት እንደዚህ ቁመቷ ሊረዝም እንደቻለና በሽታዋ ከታወቀ በኋላ ሐኪሞች ዕብጠቱን እንዳስወገዱት ተገልጾዋል፡፡

ወደፊት ሞዴሊስት ለመሆን የምታስበው የከንፈው ወዳጅዋ መልካም ስብዕና ያለውና ለእርሷም ድንቅ አመለካከት እንዳለው ገልጻለች፡፡ ሆኖም ችግሯን ከመግለጽ አልተቆጠበችም፤ “ያለኝ ዋና ችግር እጅ ለእጅ ተያይዘን ስንሄድ ትንሹን ወንድሜን ወይም ልጄን ይዤ የምሄድ ይመስለኛል” ብላለች፡፡

የዓመቱ ሰው

ቀዳማዊ ኃይለሥላሴን ታህሳስ 4፤ 1928ዓም (ጃኑዋሪ 6፤1936 አውሮጳውያኑ ቆጣጠር) ዕትሙ የዓመቱ ሰው በማለት የሰየማቸውና በየዓመቱ ይህንኑ ሲያደርግ የቆየው ታይም መጽሔት ባራክ ኦባማን የ2012 የዓመቱ ሰው በማለት ሰይሟቸዋል፡፡ ለስያሜው ምክንያት አድርጎ የጠቀሰውም ባራክ ኦባማ የአሜሪካንን ኅብረት ወደ ተሻለ ደረጃ በማድረስና በዚህ አስቸጋሪ ዘመን ደካማነትን ወደ ዕድል (ብርታት) በመቀየር ቀዳሚውን ቦታ በመያዛቸው የዓመቱ ሰው ለመባል መቻላቸውን ይጠቅሳል፡፡

 

በተቃራኒው የፕሬዚዳንቱን መመረጥ የሚቃወሙ ድርጊቱን አጥብቀው የኮነኑ ሲሆን ባራክ ኦባማ ለዚህ የዓመቱ ሰው ክብር መብቃት የቻሉት “ደደቦች ስለሚወዷቸው እና የመረጃ እጦት ያላቸው ስለሚደግፏቸው” መሆኑን በመጥቀስ ምርጫውን ያጥላሉም አሉ፡፡

የግብረሰዶማውያን መጽሐፍ ቅዱስ

ራሱን “የግብረሰዶማውያን መጽሐፍቅዱስ” በማለት የሚጠራ መጽሐፍ መታተሙን ሰሞኑን ተሰምቷል፡፡ ከቀደምት መጽሃፍቅዱስ ትርጉሞች መካከል በዋንኛነት የሚጠቀሰው የንጉሥ ጀምስ ዕትምን በመተካት የንግሥት ጀምስ ዕትም በማለት የወጣው ይኸው መጽሐፍ በመጽሐፍቅዱስ ላይ ስለ ግብረሰዶማውያን የተጠቀሰውን የፍርሃቻና የተዛባ አጻጻፍ በተከላከለ መልኩ የተጻፈ መሆኑን ያስረዳል፡፡

ደራሲው፡ እግዚአብሔር ተባባሪው ደግሞ ክርስቶስ በማለት በውስጥ ገጹ ላይ ያሰፈረውን ይህንን መጽሐፍ ማን እንዳዘጋጀው የተሰጠ ምንም ዓይነት መረጃ የለም፡፡ በአሁኑ ጊዜ በሽያጭ ላይ የሚገኝ ሲሆን በርካታ አስተያየት ሰጪዎችም የተለያዩ የሃይማኖት መጽሐፎች በተለይም ቁርዓን እንደዚህ ባለ መልኩ ለግብረሰዶማውያን እንዲታተም ጥያቄ አቅርበዋል፡፡

“ስታሊንን እወደዋለሁ” 

ሰሞኑን የቀድሞዋ ሶቪየት ኅብረት መሪ የነበሩት ጆሴፍ ስታሊን 133ኛ የልደት በዓል በተከበረ ጊዜ በጆርጂያና በሩሲያ የሚገኙ ደጋፊዎቻቸው በዓሉን በሃዘን – መሪያቸውን በማጣታቸው – በኩራት – እንደ ስታሊን ዓይነት ወደዚህ ምድር በመወለዱ – አክብረውታል፡፡

“ስታሊንን እወደዋለሁ” የሚሉት በበዓሉ ላይ የተገኙት ደጋፊ ሲናገሩ “የ12 ዓመት ልጅ ሆኜ ሳለሁ አያቴ ስታሊን ሞቶ እንዴት አምርራ ስታለቅስ እንደነበረ አስታውሳለሁ” ብለዋል፡፡ በሩሲያ በተከበረው በዓል ላይ በኮሙኒስት ፓርቲው መሪ ጌናዲ ዡጋኖቭ የሚመሩ በመቶዎች የሚቆጠሩ ደጋፊዎች የስታሊን መቃብር በሚገኝበት ቀዩ አደባባይ አበባ አኑረዋል፡፡ የስታሊን ተቃዋሚ የሆኑ በተለይም በዩክሬይን የሚኖሩም በዓሉን ተቃውሞ በማሰማት አሳልፈዋል፡፡

“በወንድሙ ጦስ ተገደለ”

የአሳድን አገዛዝ ለመጣል እየተዋጉ ያሉትና የምዕራባውያን ቀጥተኛ ድጋፍ ያላቸው የሶሪያ አማጺያን ሰሞኑን የፈጸሙት ግድያ በአሰቃቂነቱ ተጠቃሽ ሆኗል፡፡ የክርስትና እምነት ተከታይ የሆነውን ግለሰብ ታፍኖ ከተወሰደ በኋላ አማጺያኑ አንገቱን ቆርጠው የቀረውን አካሉን ለውሾች መስጠታቸውን ታውቋል፡፡

በታክሲ ሥራ የሚተዳደረው የ38 ዓመቱ ግለሰብ ወንድም አማጺያኑን በመንቀፍ የውንብድና ሥራ እየሰሩ መሆናቸውን ከተናገረ በኋላ በወንድሙ ጦስ ታፍኖ መወሰዱን ጉዳዩን በቅርብ የሚያውቁት መነኩሴይት ተናግረዋል፡፡ የቅዱስ ያዕቆብ ገዳም መነኩሴ የሆኑት እናት በድርጊቱ እስላማዊ አክራሪዎችን የኮነኑ ሲሆን ምዕራባውያን እንዲህ ያለው አሰቃቂ ድርጊት በአገራቸው እንዲፈጸም ለአማጺያኑ መሣሪያ በማቀበል መደገፋቸውን አጥብቀው ኮንነዋል፡፡ በቶሎ ካልተቋጨ ወደፊት ወደ ሃይማኖታዊ ጦርነት ሊሸጋገር እንደሚችል የከረረ ሃሳብ እየተሰጠበት ያለውና ሁለት ዓመት ሊሞላው ጥቂት ወራት የቀሩት የሶሪያ ጦርነት እስካሁን ከ44ሺህ በላይ ዜጎችን ህይወት ቀጥፏል፡፡

ጥይት መከላከያ ለልጆች

በቅርቡ በአሜሪካ በት/ቤት ተኩስ ተከፍቶ 20ሕጻናት ተማሪዎች ከተገደሉ በኋላ በኮሎምቢያ የሚገኝ የጥይት መከላከያ ጃኬት አምራች ድርጅት ለልጆች የሚሆን ልብስ ማዘጋጀቱን ገለጸ፡፡

ከማንኛውም ዓይነት የሽጉጥና አውቶማቲክ ጠብመንጃ ጥይት የሚከላከለውና ቀለል ያለ ክብደት ያለው ጃኬት የልጆችን ቀልብ እንዲስብ በተለያዩ ቀለማት እንደሚሠራ ኩባንያው አስታውቋል፡፡ ዋጋው 500ዶላር ከሆነው ከዚህ ጃኬት በተጨማሪ ኩባንያው ጥይት የሚከላከል የልጆች ደብተር መያዣ ቦርሳም እንዳዘጋጀ ገልጾዋል፡፡

ኤሌክትሮኒክ ሲጋራ አያዋጣም

የሲጋራ ሱስን ለመተው ይረዳል እየተባለ በስፋት የሚሸጠው የኤሌክትሮኒክ ሲጋራ ማጨስ ለማቆም እንደማይረዳ ተሰማ፡፡ የጣሊያን ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ባወጣው በዚሁ መግለጫ መሠረት ኒኮቲን ያለው በመሆኑ ጉዳቱ እንደመደበኛው ሲጋራ ሲሆን አጫሾችን ሲጋራ ለማቆም የሚያደርገው አስተዋጽዖ እንደሌለ አስታውቋል፡፡

በሲጋራ ማጨስ ማቆምን አስመልክቶ ምክር የሚሰጡ እንደሚሉት ኒኮቲንን ከሰውነት በማስወገድ በአጠቃላይ ሲጋራ ማጨስ ማቆም አማራጭ የሌለው ጉዳይ እንደሆን ይናገራሉ፡፡ ሰዎች ይህንን ውሳኔ ሲያደርጉ የተለያዩ ስሜቶች የሚፈራረቁባቸው ቢሆንም አስቸጋሪ የሆኑት ስሜቶች ከ24 እስከ 72ሰዓታት ባሉት ጊዜያት ውስጥ እንደሚጠፉ እንዲሁም በአካል ላይ የሚከሰቱት ችግሮች ደግሞ ከአራት ሳምንታት ባልበለጠ ጊዜ ፈጽሞ እንደሚወገዱ ሳይንሳዊ መረጃዎችን በመጥቀስ አስተያየት ይሰጣሉ፡፡

የሳምንቱ ምርጥ ፎቶ

ምስሉን ያገኘነው ከፌስቡክ ነው፡፡ “ልማቱ እንዴት ነው?” ብሎ ለሚጠይቅ ብዙ ከማለት ይህንን “ልማታዊ ፎቶ” “ከሶማሊያውያን የሚበልጡ ኢትዮጵያዊያን ተሰደዋል” በሚል ርዕስ የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ኮሚሽን ያወጣውን ዘገባ አጣቅሰን ከጻፍነው “ደጋፊ ዜና” ጋር ማቅረብ ጥሩ መልስ ሊሆን ይችላል፡፡

ዘገባውን ለማጠናቀር በየጽሁፉ ከጠቀስናቸው ምንጮች በተጨማሪ ሌሎችንም የሚዲያ ውጤቶች መጠቀማችንን ለመግለፅ እንወዳለን፡፡ ከዜናዎቹ ማነስ አኳያ በየጸሁፉ ለመግለጽ ባለመቻላችን ይቅርታ እንጠይቃለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Feleke Gethaun says

    December 31, 2012 01:45 pm at 1:45 pm

    Best

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule