• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በስዊድን የኤርትራ ኤምባሲ አጣብቂኝ ውስጥ ገባ

September 8, 2014 01:24 am by Editor 1 Comment

በስዊድን የኤርትራ ኤምባሲ በስደት አገራቸውን ጥለው የወጡ የኤርትራ ስደተኞችን እንደሚሰልል ተረጋገጠ። የስዊድን መንግሥት በደረሰው ጥቆማና ማስረጃ መሰረት ባደረገው ማጣራት ኤምባሲው በስለላ ስራ ተሰማርቶ ስዊድን ከለላ የሰጠቻቸውን የኤርትራ ተወላጆች አንደሚከታተልና እንደሚሰልል ማስረጃ ተይዞበታል።

ተቀማጭነታቸው ስዊድን የሆነ የጎልጉል ተባባሪዎች ጉዳዩ ከሚመለከታቸው ክፍሎች ጋር በመነጋገር እንዳመለከቱት፣ የስዊድን ዜግነት ያላቸውንና ሻዕቢያን ለማስወገድ የሚንቀሳቀሱ ድርጅቶችን የሚደግፉ፣ አክቲቪስት የሆኑትን የኤርትራ አገዛዝ በኤምባሲው አማካይነት እንደሚስልላቸው የታወቀው በጥቆማ ነው።

ውስን ቁጥር ያላቸው በስዊድን የሚኖሩ የኤርትራ ተወላጆች ባቀረቡት ጥቆማ መሰረት የስዊድን መንግሥት ባካሄደው ማጣራት የኤርትራ ኤምባሲ የተከሰሰበትን ተግባር እንደሚፈጽም ተረጋግጧል። የመረጃው ባለቤቶች እንዳሉት ስደተን ሸሽተው የሚኖሩበት አገር ድረስ እየተከታተሉ መሰለል በህግ የተከለከለ በመሆኑ የኤርትራ ኤምባሲ ሊዘጋ እንደሚችል ፍንጭ ማግኘታቸውን አመልክተዋል።

ዳዊት ይስሃቅ
ዳዊት ይስሃቅ

ይህንኑ የተረዳው የሻዕቢያ አገዛዝ ከውሳኔው በፊት የምርመራውን ውጤት ለማስገልበጥ የበኩሉን እየሰራ መሆኑንን ከመረጃው አጠናካሪዎች ለመረዳት ተችሏል። የስዊድን መንግሥት በኤርትራ እስር ቤት ታስሮ ይሙት ይዳን በይፋ በማይታቀወቀው ጋዜጠኛ ዳዊት ይስሃቅ ጉዳይ ከፕሬዚዳንት ኢሳያስ ጋር ሲወዛገብ እንደነበርና ጉዳዩ እስካሁን እልባት እንዳላገኘ የመረጃው አቀባዮች አመልክተዋል።

በተለያዩ አገራት በትውልድ አገራቸው ያለውን አገዛዝ ኮንነው የጥገኛነት ማመልከቻ የሚያስገቡ፣ ከለላ ከተሰጣቸው በኋላ “በደለን” ለሚሉት አገዛዝ ሲላላኩና ሲሰሩ ባደባባይ እንደሚታይ በመጠቆም አስተያየት የሰጡ፣ ይህ የኤርትራ ተወላጆች መረጃ ላይ ያተኮረ ክስ ለኢትዮጵያዊያን ታላቅ ትምህርት እንደሚሆን ተናግረዋል።

በአሜሪካና በተለያዩ የአውሮጳ አገሮች ኢህአዴግ ዜጎችን እየተከታተለ እንደሚሰልል፣ በአፍሪካ ድንበር አቋርጦ የፈለገውን ከመሰለል አልፎ እንደሚያስርና እንደሚገድል ያስታወሱት አስተያያት ሰጪ “ተቃዋሚዎች የኢህአዴግ ኤምባሲዎች የስለላ ስራ እንደሚሰሩ ማስረጃ በመሰብሰብ ክስ ሊመሰርቱ ይገባል” ብለዋል።ali and isayas

ጋዜጠኛ ዳዊት የስዊድን ዜግነት ያለው ሲሆን 2001 ላይ ነበር የታሰረው። በኤርትራ የመጀመሪያዋ “ሴቲት” ጋዜጣ ሪፖርተርና ሸሪክ ባለቤት የነበረው ዳዊት በመስከረም 2001 ከመኖሪያ ቤቱ ታፍኖ ሲወሰድ በተመሳሳይ 10 የሚሆኑ ጋዜጠኞችም መታሰራቸው በወቅቱ ዓለምአቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተከላካይ ድርጅት (ሲፒጄ) ዘግቦ ነበር። ከነሱም በተጨማሪ ተለምዶ G15 የሚባሉት የለውጥ አራማጅ ባለስልጣኖች አብረው ታስረዋል። ዳዊት የት እንደታሰረ ባለስልጣናት እንኳን እንደማያውቁ አቶ አሊ አብዶ የቀድሞው የማስታወቂያ ሚኒስትር ኢሳያስን ከድተው ከኮበለሉ በኋላ መግለጻቸውን በስዊድን የሚገኙ መገናኛዎች ወንድማቸውን ጠቅሰው መዘገባቸው ይታወሳል።

“የፕሬዚዳንት ኢሳያስ ልጅ” የሚባሉት አቶ አሊ፣ ዳዊት በህይወት እንደሌለ ፍንጭ በመስጠት ቀዳሚው ባለስልጣን ሆነዋል። የሆነ ሆኖ ሻዕቢያ በጋዜጠኛ ዳዊት ጉዳይ በግልጽ እምነት ክህደት አላካሄደም። ጋዜጣ ከኤርትራ ምድር እንዲታገድ መደረጉን በወቅቱ የወጡ መረጃዎች ያመለክታሉ። (ፎቶ: የኤምባሲው ድረገጽ)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. aradaw says

    September 11, 2014 01:52 am at 1:52 am

    የእኛን ጉድ ማን ይናገር ማን ያውራ
    የእኛዎቹ ከመሰለል ኣልፎ ያፍናሉ ይገድላሉ

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule