• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በስዊድን የኤርትራ ኤምባሲ አጣብቂኝ ውስጥ ገባ

September 8, 2014 01:24 am by Editor 1 Comment

በስዊድን የኤርትራ ኤምባሲ በስደት አገራቸውን ጥለው የወጡ የኤርትራ ስደተኞችን እንደሚሰልል ተረጋገጠ። የስዊድን መንግሥት በደረሰው ጥቆማና ማስረጃ መሰረት ባደረገው ማጣራት ኤምባሲው በስለላ ስራ ተሰማርቶ ስዊድን ከለላ የሰጠቻቸውን የኤርትራ ተወላጆች አንደሚከታተልና እንደሚሰልል ማስረጃ ተይዞበታል።

ተቀማጭነታቸው ስዊድን የሆነ የጎልጉል ተባባሪዎች ጉዳዩ ከሚመለከታቸው ክፍሎች ጋር በመነጋገር እንዳመለከቱት፣ የስዊድን ዜግነት ያላቸውንና ሻዕቢያን ለማስወገድ የሚንቀሳቀሱ ድርጅቶችን የሚደግፉ፣ አክቲቪስት የሆኑትን የኤርትራ አገዛዝ በኤምባሲው አማካይነት እንደሚስልላቸው የታወቀው በጥቆማ ነው።

ውስን ቁጥር ያላቸው በስዊድን የሚኖሩ የኤርትራ ተወላጆች ባቀረቡት ጥቆማ መሰረት የስዊድን መንግሥት ባካሄደው ማጣራት የኤርትራ ኤምባሲ የተከሰሰበትን ተግባር እንደሚፈጽም ተረጋግጧል። የመረጃው ባለቤቶች እንዳሉት ስደተን ሸሽተው የሚኖሩበት አገር ድረስ እየተከታተሉ መሰለል በህግ የተከለከለ በመሆኑ የኤርትራ ኤምባሲ ሊዘጋ እንደሚችል ፍንጭ ማግኘታቸውን አመልክተዋል።

ዳዊት ይስሃቅ
ዳዊት ይስሃቅ

ይህንኑ የተረዳው የሻዕቢያ አገዛዝ ከውሳኔው በፊት የምርመራውን ውጤት ለማስገልበጥ የበኩሉን እየሰራ መሆኑንን ከመረጃው አጠናካሪዎች ለመረዳት ተችሏል። የስዊድን መንግሥት በኤርትራ እስር ቤት ታስሮ ይሙት ይዳን በይፋ በማይታቀወቀው ጋዜጠኛ ዳዊት ይስሃቅ ጉዳይ ከፕሬዚዳንት ኢሳያስ ጋር ሲወዛገብ እንደነበርና ጉዳዩ እስካሁን እልባት እንዳላገኘ የመረጃው አቀባዮች አመልክተዋል።

በተለያዩ አገራት በትውልድ አገራቸው ያለውን አገዛዝ ኮንነው የጥገኛነት ማመልከቻ የሚያስገቡ፣ ከለላ ከተሰጣቸው በኋላ “በደለን” ለሚሉት አገዛዝ ሲላላኩና ሲሰሩ ባደባባይ እንደሚታይ በመጠቆም አስተያየት የሰጡ፣ ይህ የኤርትራ ተወላጆች መረጃ ላይ ያተኮረ ክስ ለኢትዮጵያዊያን ታላቅ ትምህርት እንደሚሆን ተናግረዋል።

በአሜሪካና በተለያዩ የአውሮጳ አገሮች ኢህአዴግ ዜጎችን እየተከታተለ እንደሚሰልል፣ በአፍሪካ ድንበር አቋርጦ የፈለገውን ከመሰለል አልፎ እንደሚያስርና እንደሚገድል ያስታወሱት አስተያያት ሰጪ “ተቃዋሚዎች የኢህአዴግ ኤምባሲዎች የስለላ ስራ እንደሚሰሩ ማስረጃ በመሰብሰብ ክስ ሊመሰርቱ ይገባል” ብለዋል።ali and isayas

ጋዜጠኛ ዳዊት የስዊድን ዜግነት ያለው ሲሆን 2001 ላይ ነበር የታሰረው። በኤርትራ የመጀመሪያዋ “ሴቲት” ጋዜጣ ሪፖርተርና ሸሪክ ባለቤት የነበረው ዳዊት በመስከረም 2001 ከመኖሪያ ቤቱ ታፍኖ ሲወሰድ በተመሳሳይ 10 የሚሆኑ ጋዜጠኞችም መታሰራቸው በወቅቱ ዓለምአቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተከላካይ ድርጅት (ሲፒጄ) ዘግቦ ነበር። ከነሱም በተጨማሪ ተለምዶ G15 የሚባሉት የለውጥ አራማጅ ባለስልጣኖች አብረው ታስረዋል። ዳዊት የት እንደታሰረ ባለስልጣናት እንኳን እንደማያውቁ አቶ አሊ አብዶ የቀድሞው የማስታወቂያ ሚኒስትር ኢሳያስን ከድተው ከኮበለሉ በኋላ መግለጻቸውን በስዊድን የሚገኙ መገናኛዎች ወንድማቸውን ጠቅሰው መዘገባቸው ይታወሳል።

“የፕሬዚዳንት ኢሳያስ ልጅ” የሚባሉት አቶ አሊ፣ ዳዊት በህይወት እንደሌለ ፍንጭ በመስጠት ቀዳሚው ባለስልጣን ሆነዋል። የሆነ ሆኖ ሻዕቢያ በጋዜጠኛ ዳዊት ጉዳይ በግልጽ እምነት ክህደት አላካሄደም። ጋዜጣ ከኤርትራ ምድር እንዲታገድ መደረጉን በወቅቱ የወጡ መረጃዎች ያመለክታሉ። (ፎቶ: የኤምባሲው ድረገጽ)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. aradaw says

    September 11, 2014 01:52 am at 1:52 am

    የእኛን ጉድ ማን ይናገር ማን ያውራ
    የእኛዎቹ ከመሰለል ኣልፎ ያፍናሉ ይገድላሉ

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule