• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በስዊድን የኤርትራ ኤምባሲ አጣብቂኝ ውስጥ ገባ

September 8, 2014 01:24 am by Editor 1 Comment

በስዊድን የኤርትራ ኤምባሲ በስደት አገራቸውን ጥለው የወጡ የኤርትራ ስደተኞችን እንደሚሰልል ተረጋገጠ። የስዊድን መንግሥት በደረሰው ጥቆማና ማስረጃ መሰረት ባደረገው ማጣራት ኤምባሲው በስለላ ስራ ተሰማርቶ ስዊድን ከለላ የሰጠቻቸውን የኤርትራ ተወላጆች አንደሚከታተልና እንደሚሰልል ማስረጃ ተይዞበታል።

ተቀማጭነታቸው ስዊድን የሆነ የጎልጉል ተባባሪዎች ጉዳዩ ከሚመለከታቸው ክፍሎች ጋር በመነጋገር እንዳመለከቱት፣ የስዊድን ዜግነት ያላቸውንና ሻዕቢያን ለማስወገድ የሚንቀሳቀሱ ድርጅቶችን የሚደግፉ፣ አክቲቪስት የሆኑትን የኤርትራ አገዛዝ በኤምባሲው አማካይነት እንደሚስልላቸው የታወቀው በጥቆማ ነው።

ውስን ቁጥር ያላቸው በስዊድን የሚኖሩ የኤርትራ ተወላጆች ባቀረቡት ጥቆማ መሰረት የስዊድን መንግሥት ባካሄደው ማጣራት የኤርትራ ኤምባሲ የተከሰሰበትን ተግባር እንደሚፈጽም ተረጋግጧል። የመረጃው ባለቤቶች እንዳሉት ስደተን ሸሽተው የሚኖሩበት አገር ድረስ እየተከታተሉ መሰለል በህግ የተከለከለ በመሆኑ የኤርትራ ኤምባሲ ሊዘጋ እንደሚችል ፍንጭ ማግኘታቸውን አመልክተዋል።

ዳዊት ይስሃቅ
ዳዊት ይስሃቅ

ይህንኑ የተረዳው የሻዕቢያ አገዛዝ ከውሳኔው በፊት የምርመራውን ውጤት ለማስገልበጥ የበኩሉን እየሰራ መሆኑንን ከመረጃው አጠናካሪዎች ለመረዳት ተችሏል። የስዊድን መንግሥት በኤርትራ እስር ቤት ታስሮ ይሙት ይዳን በይፋ በማይታቀወቀው ጋዜጠኛ ዳዊት ይስሃቅ ጉዳይ ከፕሬዚዳንት ኢሳያስ ጋር ሲወዛገብ እንደነበርና ጉዳዩ እስካሁን እልባት እንዳላገኘ የመረጃው አቀባዮች አመልክተዋል።

በተለያዩ አገራት በትውልድ አገራቸው ያለውን አገዛዝ ኮንነው የጥገኛነት ማመልከቻ የሚያስገቡ፣ ከለላ ከተሰጣቸው በኋላ “በደለን” ለሚሉት አገዛዝ ሲላላኩና ሲሰሩ ባደባባይ እንደሚታይ በመጠቆም አስተያየት የሰጡ፣ ይህ የኤርትራ ተወላጆች መረጃ ላይ ያተኮረ ክስ ለኢትዮጵያዊያን ታላቅ ትምህርት እንደሚሆን ተናግረዋል።

በአሜሪካና በተለያዩ የአውሮጳ አገሮች ኢህአዴግ ዜጎችን እየተከታተለ እንደሚሰልል፣ በአፍሪካ ድንበር አቋርጦ የፈለገውን ከመሰለል አልፎ እንደሚያስርና እንደሚገድል ያስታወሱት አስተያያት ሰጪ “ተቃዋሚዎች የኢህአዴግ ኤምባሲዎች የስለላ ስራ እንደሚሰሩ ማስረጃ በመሰብሰብ ክስ ሊመሰርቱ ይገባል” ብለዋል።ali and isayas

ጋዜጠኛ ዳዊት የስዊድን ዜግነት ያለው ሲሆን 2001 ላይ ነበር የታሰረው። በኤርትራ የመጀመሪያዋ “ሴቲት” ጋዜጣ ሪፖርተርና ሸሪክ ባለቤት የነበረው ዳዊት በመስከረም 2001 ከመኖሪያ ቤቱ ታፍኖ ሲወሰድ በተመሳሳይ 10 የሚሆኑ ጋዜጠኞችም መታሰራቸው በወቅቱ ዓለምአቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተከላካይ ድርጅት (ሲፒጄ) ዘግቦ ነበር። ከነሱም በተጨማሪ ተለምዶ G15 የሚባሉት የለውጥ አራማጅ ባለስልጣኖች አብረው ታስረዋል። ዳዊት የት እንደታሰረ ባለስልጣናት እንኳን እንደማያውቁ አቶ አሊ አብዶ የቀድሞው የማስታወቂያ ሚኒስትር ኢሳያስን ከድተው ከኮበለሉ በኋላ መግለጻቸውን በስዊድን የሚገኙ መገናኛዎች ወንድማቸውን ጠቅሰው መዘገባቸው ይታወሳል።

“የፕሬዚዳንት ኢሳያስ ልጅ” የሚባሉት አቶ አሊ፣ ዳዊት በህይወት እንደሌለ ፍንጭ በመስጠት ቀዳሚው ባለስልጣን ሆነዋል። የሆነ ሆኖ ሻዕቢያ በጋዜጠኛ ዳዊት ጉዳይ በግልጽ እምነት ክህደት አላካሄደም። ጋዜጣ ከኤርትራ ምድር እንዲታገድ መደረጉን በወቅቱ የወጡ መረጃዎች ያመለክታሉ። (ፎቶ: የኤምባሲው ድረገጽ)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. aradaw says

    September 11, 2014 01:52 am at 1:52 am

    የእኛን ጉድ ማን ይናገር ማን ያውራ
    የእኛዎቹ ከመሰለል ኣልፎ ያፍናሉ ይገድላሉ

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule