• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በአማራና ትግራይ ህዝብ መካካል አብሮነቱ እንዲጠናከር የሁለቱ ክልሎች ፖለቲከኞች ተቀራርበው ሊሰሩ እንደሚገባ ተገለጸ

November 17, 2019 07:53 pm by Editor Leave a Comment

በአማራና በትግራይ ክልል ህዝቦች መካካል ለዘመናት የዘለቀው የአብሮነት እሴት ተጠናክሮ እንዲቀጥል የሁለቱ ክልሎች መንግሥታትና ፖለቲከኞች ልብ ለልብ ተቀራርበው ሊሰሩ ይገባል ሲሉ በጎንደር ከተማ የሚገኙ የትግራይ ተወላጆች ተናገሩ።

የጎንደር ከተማ አስተዳደር በከተማው ከሚኖሩ የትግራይ ተወላጆች ጋር በወቅታዊ፣ ክልላዊና ሀገራዊ ሁኔታ ላይ ያዘጋጀው የምክክር መድረክ ዛሬ ተካሂዷል።

በምክክር መድረኩ ላይ ተሳታፊ የሆኑ የትግራይ ተወላጆች እንደተናገሩት መንግስትና የፖለቲካ ስርአት አላፊ ሲሆኑ፤ ህዝብና አገር ግን የሚቀጥሉና የታሪክ ባለቤት ናቸው።

“ጎንደር ያደኩባት፣ የሸመገልኩባት፣ ልጅ ወልጄና አሳድጌ ለወግ ማዕረግ የበቃሁባት ህዝቡም በፍቅር ያኖረኝ ከተማ ነች” ያሉት አቶ ወልደገብርኤል ተክኤ የተባሉ ነዋሪ ናቸው።

“በኖርኩባቸው 40 ዓመታት በከተማው አማራ እና ትግሬ ተባብለን አናውቅም፤ የብሔርም ጠብና ግጭትም አልነበረም” ያሉት አቶ ወልደገብርኤል አሁን በታሪካቸው የማያውቁት ነገር እየተከሰተ በመሆኑ ማዘናቸውን ተናግረዋል።

መንግስት ቢያልፍም ህዝብና ሀገር ቀጣይ መሆናቸውን ገልጸው የሁለቱ ክልሎች መንግስታትና ፖለቲከኞች ተቀራርበው በመስራት ከግጭት ይልቅ የሁለቱን ህዝቦች አንድነትና አብሮነት በሚያስቀጥሉ ጉዳዮች ላይ እንዲያተኩሩ ጠይቀዋል።

ላለፉት 44 ዓመታት በጎንደር ከተማ ከህዝቡ ጋር በፍቅር መኖራቸውንና ጎንደር ከተማንም በምክትል ከንቲባነት ጭምር ማስተዳደራቸውን የተናገሩት ደግሞ አቶ አያሌው ተስፋይ ናቸው።

የብሔር ፖለቲካ ሁለቱን ህዝቦች ለመከፋፋልና ለማጋጨት በር መክፈቱን የተናገሩት አቶ አያሌው፥ አሁን ሁለቱን ህዝቦች ለማቀራረብ የተዘጋጀው መድረክ ቢዘገይም ጅምሩ ተጠናክሮ እንዲቀጥል አስገንዝበዋል።

በሁለቱ ክልል ህዝቦች መካከል ለዘመናት የቆየው አብሮነት እንዲጠናከር የክልሎቹ አመራሮችም ሆነ ፖለቲከኞች እርስ በርስ ከመገፋፋት ይልቅ ከልብ ተቀራርበው ሊሰሩ እንደሚገባ ተናግረዋል።

በህዝባዊ የምክክር መድረኩ ላይ የተገኙት የትግራይ ዴሞክራሲ ትብብር ፓርቲ ምክትል ሊቀ-መንበር ኢንጂነር ግደይ ዘርአጽዮን በበኩላቸው የአማራና የትግራ ህዝብ ዘመናት የዘለቀ አብሮነት ያለው ኩሩና አቃፊ ህዝብ መሆኑን ተናግረዋል።

አጼ ዮሐንስ መተማ ላይ መስዋዕት የሆኑት ለትግራይ ሳይሆን ለአንዲት ኢትዮጵያና ህዝቧ መሆኑን ገልጸዋል።

“የዛሬ ፖለቲከኞችና ስልጣን ፈላጊዎች ህዝብን ከህዝብ በማጋጨት የራሳቸውን ህልውና ለማስቀጠል የሚያደርጉትን የፖለቲካ ሴራ ሁለቱ ህዝቦች በጋራ ቆመው መታገል አላባቸው ብለዋል።

ኢንጂነር ግደይ እንዳሉት ፓርቲው በግጭት ምክንያት ከአማራ ክልል የተፈናቀሉ የትግራይ ተወላጆች ዳግም ወደአካባቢው እንደሚመለሱና እንዲቋቋሙ ለማድረግ ከአማራ ክልል መንግስት ጋር ጥረት እያደረገ ነው።

የአማራ ክልል መንግስት ይህን መሰል የህዝብ ለህዝብ የምክክር መድረክ እንዲዘጋጅ በመፍቀዱ አመስግነው በሌሎች መድረኮችም ተጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል፡፡
የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሙሉብርሃን ኃይሌ በበኩላቸው “የፖለቲካ ስርአቱ እንጂ የአማራ ህዝብ የትግራይን ህዝብ አላፈናቀለም” ብለዋል።

“የአማራ ህዝብ ሦስት ዓመት ሙሉ ተፈናቅለው የሄዱ የትግራይ ተወላጆችን ቤትና ንብረት ሳያስነካ እየጠበቀ ስለመሆኑ በቂ ማስረጃ አለኝ” ሲሉም ተናግረዋል።

“የምክክር መድረኩ የሁለቱን ህዝቦች ዘመናት የዘለቀውን አብሮነት በማስቀጠል የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቱን ዳግም ለማጠናከር ያለመ ነው” ያሉት ደግሞ የጎንደር ከተማ ምክትል ከንቲባ አቶ ተሸመ አግማስ ናቸው።

የተጀመረውን ሀገራዊ ለውጥ በማስቀጠል ረገድ ሁለቱ ህዝቦች የጎላ ሚና እንዳላቸው ተናግረው በአገሪቱ የገጠመውን የአንድነት ፈተና በጽናት በመቆም በጋራ መሻገር እንደሚገባ አመልክተዋል።

በምክክር መድረኩ ከከተማው የተለያዩ ክፍለ ከተሞች የተውጣጡ የትግራይ ተወላጆችን ጨምሮ ከፍተኛ አመራሮችና የከተማው የሰላምና የልማት ሸንጎ አባላት እንዲሁም የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ አመራሮች ተሳታፊ ሆነዋል።

ምንጭ ፦ኢዜአ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule