• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በአማራና ትግራይ ህዝብ መካካል አብሮነቱ እንዲጠናከር የሁለቱ ክልሎች ፖለቲከኞች ተቀራርበው ሊሰሩ እንደሚገባ ተገለጸ

November 17, 2019 07:53 pm by Editor Leave a Comment

በአማራና በትግራይ ክልል ህዝቦች መካካል ለዘመናት የዘለቀው የአብሮነት እሴት ተጠናክሮ እንዲቀጥል የሁለቱ ክልሎች መንግሥታትና ፖለቲከኞች ልብ ለልብ ተቀራርበው ሊሰሩ ይገባል ሲሉ በጎንደር ከተማ የሚገኙ የትግራይ ተወላጆች ተናገሩ።

የጎንደር ከተማ አስተዳደር በከተማው ከሚኖሩ የትግራይ ተወላጆች ጋር በወቅታዊ፣ ክልላዊና ሀገራዊ ሁኔታ ላይ ያዘጋጀው የምክክር መድረክ ዛሬ ተካሂዷል።

በምክክር መድረኩ ላይ ተሳታፊ የሆኑ የትግራይ ተወላጆች እንደተናገሩት መንግስትና የፖለቲካ ስርአት አላፊ ሲሆኑ፤ ህዝብና አገር ግን የሚቀጥሉና የታሪክ ባለቤት ናቸው።

“ጎንደር ያደኩባት፣ የሸመገልኩባት፣ ልጅ ወልጄና አሳድጌ ለወግ ማዕረግ የበቃሁባት ህዝቡም በፍቅር ያኖረኝ ከተማ ነች” ያሉት አቶ ወልደገብርኤል ተክኤ የተባሉ ነዋሪ ናቸው።

“በኖርኩባቸው 40 ዓመታት በከተማው አማራ እና ትግሬ ተባብለን አናውቅም፤ የብሔርም ጠብና ግጭትም አልነበረም” ያሉት አቶ ወልደገብርኤል አሁን በታሪካቸው የማያውቁት ነገር እየተከሰተ በመሆኑ ማዘናቸውን ተናግረዋል።

መንግስት ቢያልፍም ህዝብና ሀገር ቀጣይ መሆናቸውን ገልጸው የሁለቱ ክልሎች መንግስታትና ፖለቲከኞች ተቀራርበው በመስራት ከግጭት ይልቅ የሁለቱን ህዝቦች አንድነትና አብሮነት በሚያስቀጥሉ ጉዳዮች ላይ እንዲያተኩሩ ጠይቀዋል።

ላለፉት 44 ዓመታት በጎንደር ከተማ ከህዝቡ ጋር በፍቅር መኖራቸውንና ጎንደር ከተማንም በምክትል ከንቲባነት ጭምር ማስተዳደራቸውን የተናገሩት ደግሞ አቶ አያሌው ተስፋይ ናቸው።

የብሔር ፖለቲካ ሁለቱን ህዝቦች ለመከፋፋልና ለማጋጨት በር መክፈቱን የተናገሩት አቶ አያሌው፥ አሁን ሁለቱን ህዝቦች ለማቀራረብ የተዘጋጀው መድረክ ቢዘገይም ጅምሩ ተጠናክሮ እንዲቀጥል አስገንዝበዋል።

በሁለቱ ክልል ህዝቦች መካከል ለዘመናት የቆየው አብሮነት እንዲጠናከር የክልሎቹ አመራሮችም ሆነ ፖለቲከኞች እርስ በርስ ከመገፋፋት ይልቅ ከልብ ተቀራርበው ሊሰሩ እንደሚገባ ተናግረዋል።

በህዝባዊ የምክክር መድረኩ ላይ የተገኙት የትግራይ ዴሞክራሲ ትብብር ፓርቲ ምክትል ሊቀ-መንበር ኢንጂነር ግደይ ዘርአጽዮን በበኩላቸው የአማራና የትግራ ህዝብ ዘመናት የዘለቀ አብሮነት ያለው ኩሩና አቃፊ ህዝብ መሆኑን ተናግረዋል።

አጼ ዮሐንስ መተማ ላይ መስዋዕት የሆኑት ለትግራይ ሳይሆን ለአንዲት ኢትዮጵያና ህዝቧ መሆኑን ገልጸዋል።

“የዛሬ ፖለቲከኞችና ስልጣን ፈላጊዎች ህዝብን ከህዝብ በማጋጨት የራሳቸውን ህልውና ለማስቀጠል የሚያደርጉትን የፖለቲካ ሴራ ሁለቱ ህዝቦች በጋራ ቆመው መታገል አላባቸው ብለዋል።

ኢንጂነር ግደይ እንዳሉት ፓርቲው በግጭት ምክንያት ከአማራ ክልል የተፈናቀሉ የትግራይ ተወላጆች ዳግም ወደአካባቢው እንደሚመለሱና እንዲቋቋሙ ለማድረግ ከአማራ ክልል መንግስት ጋር ጥረት እያደረገ ነው።

የአማራ ክልል መንግስት ይህን መሰል የህዝብ ለህዝብ የምክክር መድረክ እንዲዘጋጅ በመፍቀዱ አመስግነው በሌሎች መድረኮችም ተጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል፡፡
የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሙሉብርሃን ኃይሌ በበኩላቸው “የፖለቲካ ስርአቱ እንጂ የአማራ ህዝብ የትግራይን ህዝብ አላፈናቀለም” ብለዋል።

“የአማራ ህዝብ ሦስት ዓመት ሙሉ ተፈናቅለው የሄዱ የትግራይ ተወላጆችን ቤትና ንብረት ሳያስነካ እየጠበቀ ስለመሆኑ በቂ ማስረጃ አለኝ” ሲሉም ተናግረዋል።

“የምክክር መድረኩ የሁለቱን ህዝቦች ዘመናት የዘለቀውን አብሮነት በማስቀጠል የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቱን ዳግም ለማጠናከር ያለመ ነው” ያሉት ደግሞ የጎንደር ከተማ ምክትል ከንቲባ አቶ ተሸመ አግማስ ናቸው።

የተጀመረውን ሀገራዊ ለውጥ በማስቀጠል ረገድ ሁለቱ ህዝቦች የጎላ ሚና እንዳላቸው ተናግረው በአገሪቱ የገጠመውን የአንድነት ፈተና በጽናት በመቆም በጋራ መሻገር እንደሚገባ አመልክተዋል።

በምክክር መድረኩ ከከተማው የተለያዩ ክፍለ ከተሞች የተውጣጡ የትግራይ ተወላጆችን ጨምሮ ከፍተኛ አመራሮችና የከተማው የሰላምና የልማት ሸንጎ አባላት እንዲሁም የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ አመራሮች ተሳታፊ ሆነዋል።

ምንጭ ፦ኢዜአ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule