• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በአማራና ትግራይ ህዝብ መካካል አብሮነቱ እንዲጠናከር የሁለቱ ክልሎች ፖለቲከኞች ተቀራርበው ሊሰሩ እንደሚገባ ተገለጸ

November 17, 2019 07:53 pm by Editor Leave a Comment

በአማራና በትግራይ ክልል ህዝቦች መካካል ለዘመናት የዘለቀው የአብሮነት እሴት ተጠናክሮ እንዲቀጥል የሁለቱ ክልሎች መንግሥታትና ፖለቲከኞች ልብ ለልብ ተቀራርበው ሊሰሩ ይገባል ሲሉ በጎንደር ከተማ የሚገኙ የትግራይ ተወላጆች ተናገሩ።

የጎንደር ከተማ አስተዳደር በከተማው ከሚኖሩ የትግራይ ተወላጆች ጋር በወቅታዊ፣ ክልላዊና ሀገራዊ ሁኔታ ላይ ያዘጋጀው የምክክር መድረክ ዛሬ ተካሂዷል።

በምክክር መድረኩ ላይ ተሳታፊ የሆኑ የትግራይ ተወላጆች እንደተናገሩት መንግስትና የፖለቲካ ስርአት አላፊ ሲሆኑ፤ ህዝብና አገር ግን የሚቀጥሉና የታሪክ ባለቤት ናቸው።

“ጎንደር ያደኩባት፣ የሸመገልኩባት፣ ልጅ ወልጄና አሳድጌ ለወግ ማዕረግ የበቃሁባት ህዝቡም በፍቅር ያኖረኝ ከተማ ነች” ያሉት አቶ ወልደገብርኤል ተክኤ የተባሉ ነዋሪ ናቸው።

“በኖርኩባቸው 40 ዓመታት በከተማው አማራ እና ትግሬ ተባብለን አናውቅም፤ የብሔርም ጠብና ግጭትም አልነበረም” ያሉት አቶ ወልደገብርኤል አሁን በታሪካቸው የማያውቁት ነገር እየተከሰተ በመሆኑ ማዘናቸውን ተናግረዋል።

መንግስት ቢያልፍም ህዝብና ሀገር ቀጣይ መሆናቸውን ገልጸው የሁለቱ ክልሎች መንግስታትና ፖለቲከኞች ተቀራርበው በመስራት ከግጭት ይልቅ የሁለቱን ህዝቦች አንድነትና አብሮነት በሚያስቀጥሉ ጉዳዮች ላይ እንዲያተኩሩ ጠይቀዋል።

ላለፉት 44 ዓመታት በጎንደር ከተማ ከህዝቡ ጋር በፍቅር መኖራቸውንና ጎንደር ከተማንም በምክትል ከንቲባነት ጭምር ማስተዳደራቸውን የተናገሩት ደግሞ አቶ አያሌው ተስፋይ ናቸው።

የብሔር ፖለቲካ ሁለቱን ህዝቦች ለመከፋፋልና ለማጋጨት በር መክፈቱን የተናገሩት አቶ አያሌው፥ አሁን ሁለቱን ህዝቦች ለማቀራረብ የተዘጋጀው መድረክ ቢዘገይም ጅምሩ ተጠናክሮ እንዲቀጥል አስገንዝበዋል።

በሁለቱ ክልል ህዝቦች መካከል ለዘመናት የቆየው አብሮነት እንዲጠናከር የክልሎቹ አመራሮችም ሆነ ፖለቲከኞች እርስ በርስ ከመገፋፋት ይልቅ ከልብ ተቀራርበው ሊሰሩ እንደሚገባ ተናግረዋል።

በህዝባዊ የምክክር መድረኩ ላይ የተገኙት የትግራይ ዴሞክራሲ ትብብር ፓርቲ ምክትል ሊቀ-መንበር ኢንጂነር ግደይ ዘርአጽዮን በበኩላቸው የአማራና የትግራ ህዝብ ዘመናት የዘለቀ አብሮነት ያለው ኩሩና አቃፊ ህዝብ መሆኑን ተናግረዋል።

አጼ ዮሐንስ መተማ ላይ መስዋዕት የሆኑት ለትግራይ ሳይሆን ለአንዲት ኢትዮጵያና ህዝቧ መሆኑን ገልጸዋል።

“የዛሬ ፖለቲከኞችና ስልጣን ፈላጊዎች ህዝብን ከህዝብ በማጋጨት የራሳቸውን ህልውና ለማስቀጠል የሚያደርጉትን የፖለቲካ ሴራ ሁለቱ ህዝቦች በጋራ ቆመው መታገል አላባቸው ብለዋል።

ኢንጂነር ግደይ እንዳሉት ፓርቲው በግጭት ምክንያት ከአማራ ክልል የተፈናቀሉ የትግራይ ተወላጆች ዳግም ወደአካባቢው እንደሚመለሱና እንዲቋቋሙ ለማድረግ ከአማራ ክልል መንግስት ጋር ጥረት እያደረገ ነው።

የአማራ ክልል መንግስት ይህን መሰል የህዝብ ለህዝብ የምክክር መድረክ እንዲዘጋጅ በመፍቀዱ አመስግነው በሌሎች መድረኮችም ተጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል፡፡
የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሙሉብርሃን ኃይሌ በበኩላቸው “የፖለቲካ ስርአቱ እንጂ የአማራ ህዝብ የትግራይን ህዝብ አላፈናቀለም” ብለዋል።

“የአማራ ህዝብ ሦስት ዓመት ሙሉ ተፈናቅለው የሄዱ የትግራይ ተወላጆችን ቤትና ንብረት ሳያስነካ እየጠበቀ ስለመሆኑ በቂ ማስረጃ አለኝ” ሲሉም ተናግረዋል።

“የምክክር መድረኩ የሁለቱን ህዝቦች ዘመናት የዘለቀውን አብሮነት በማስቀጠል የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቱን ዳግም ለማጠናከር ያለመ ነው” ያሉት ደግሞ የጎንደር ከተማ ምክትል ከንቲባ አቶ ተሸመ አግማስ ናቸው።

የተጀመረውን ሀገራዊ ለውጥ በማስቀጠል ረገድ ሁለቱ ህዝቦች የጎላ ሚና እንዳላቸው ተናግረው በአገሪቱ የገጠመውን የአንድነት ፈተና በጽናት በመቆም በጋራ መሻገር እንደሚገባ አመልክተዋል።

በምክክር መድረኩ ከከተማው የተለያዩ ክፍለ ከተሞች የተውጣጡ የትግራይ ተወላጆችን ጨምሮ ከፍተኛ አመራሮችና የከተማው የሰላምና የልማት ሸንጎ አባላት እንዲሁም የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ አመራሮች ተሳታፊ ሆነዋል።

ምንጭ ፦ኢዜአ

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
Copyright © 2026 · Goolgule