• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ነጠላ ተባራይ ንፍቅ ስነ-ስሌት [ካልኩለስ በአማርኛ]

March 16, 2017 04:36 am by Editor Leave a Comment

ይህ መፅሀፍ ለፊዚክስ ሂሳባዊ ዝግጅት በሚል በኣዲስ ኣበባ ዩኒቨርስቲ ፕረስ የታተመው የጥራዝ ፩ ተከታይ በመሆን፣ ለሳይንስ እና ምህንድስና ትምህርት ኣገልግሎት ተጨማሪ ሂሳባዊ ፅንስ-ሃሳቦችን ይሰጣል። ስለሆነም፣ በቅድሚያ ኣጭር ኣልጀብራዊ (Algebraic) እና ስነ-ዘዌያዊ (Trigonometric) ክለሳ ከሰጠ በሁዋላ፣ ስለ”ተግባር” (Function) በሰፊው ያብራራል። ቀጥሎም፣ ዋና የስነ-ስሌት መሰረት በሆነው ለከት (Limit)፣ ስነ-ቅርፅ (Geometry) እና የቀጥተኛ መስመር ዝንባሌ (Slope) በመጠቀም የ”ለውጥ ቅልጥፍና” (Rate of Change) እና ለማንኛውም የተግባር ዝብ (Curve) ዝንባሌ የሚያገለግለውን በስነ-ስሌት ድናን (Derivative) በመባል የሚታወቀውን ያብራራል። የድናን ኣጠቃቀም እና ፋይዳን በተለያዩ የትምህርት ቅርንጫፎች ያሳያል። ለዚህም፣ ከሁለት መቶ ሃምሳ በላይ የሆኑ ምሳሌዎች ከጥቅል ፍቺዎቻችው ጋር በፅሁፉ ተካተዋል።

መፅሃፉን ለመፃፍ ብዙ ቃላትን መተርጎም ኣስፈልጓል። በተቻለን መጠን ከቋንቋው በሚገኙ ቃላት ተጠቅመናል። እርግጥ ከተፀውኦ ስም የተገኙ (ለምሳሌ ኣልጀብራ) ወይም በኣማርኛ ስር የሰደዱ (ለምሳሌ ዜሮ) የመሳሰሉትን ቃላት ኣልተረጎምንም። የፅሁፉ ኣላማዎች (፩) ትምህርትን እና ተደራሽነቱን ለማስፋፋት፣ (፪) ባህልን እና ቋንቋውን ለማዳበር (፫) በሃገሪቱ የነበሩ ሳይንሳዊ እና ምህንድስና ክህለቶች እንዳይጠፉ ለማድረግ፣ (፬) ኣማርኛ ሂሳባዊም ሆነ ሳይንሳዊ ክህሎት የለውም የሚለውን የተሳሳተ ከፈን ለመግፈፍ እና (፭) ሌሎች ሂሳባዊም ሆነ ሳይንሳዊ ደራሲያንን በኣማርኛ እንዲፅፉ ለማበራታት ነው። ይህ ፅሁፍ በሚዘጋጅበት ጊዜ ብዙ ሂሳባዊ እና ሳይንሳዊ ቃላት ከጥንት ጀምሮ በኢትዮጵያ ከነበሩ ጥበቦች፣ ለምሳሌ፣ ከሸክላ፣ ከቀንድ፣ ከብር እና ወርቅ ኣንጥሮሽ፣ ከጦር (መከላከያ) ስልት፣ ከሃይማኖት ፅሁፍ፣ ከግብይይት፣ ከህፃናት ጨዋታ፣ ከኮከብ ቆጠራ፣ ከጥንቆላ እና ከስድብም ሳይቀር ተገኝተዋል። ለትርጉምም ኣገልግለዋል። “ከኣንጀት ካለቀሱ እንባ እይገድም” እንደሚባለው፣ ከተፈለገ ሳይንሳዊ ፅሁፍ በኣማርኛ መፃፍ ይቻላል። የሚያግደን የራሳችን ስንፈት ብቻ ነው!

As a follow up, this book builds upon the mathematical-conceptual foundations for science and engineering laid down by “Mathematical Preparations for Physics”, published by Addis Ababa University Press. To this end, after brief reviews of Algebra and Trigonometry, it expands on the concept of functions. It then introduces the limit, the foundation of differential calculus. It introduces the concept of rate of change with the aid of limits, the slope of a straight line and simple geometry, from which it transitions to the slope of a generalized curve and introduces and expounds the major concept of the derivative. It demonstrates the application of the derivative in various disciplines by providing over two-hundred and fifty fully solved examples.

Writing this book required the translation of several words. The authors have tried, to extent possible, to draw from the Amharic language.  They have, however, preserved words derived from proper noun (such as Algebra) or words like “zero” that are already assimilated in Amharic.  Some of the objectives of the book are: (1) to expand education and its accessibility, (2) to nurture cultural and linguistic growth, (3) to preserve Ethiopia’s long existing scientific and engineering skills, (4) to dispel the erroneous belief that Amharic lacks both mathematical and scientific capabilities, and (5) to encourage other authors to write Amharic textbooks.  In the preparation of this textbook, the authors have drawn from the rich and ancient technologies in existence since time immemorial. They have drawn from ancient Ethiopian crafts such as ceramics, horn lathing, silver and gold smith works, weaving, defense strategies, religious texts, business, children’s games, astrology and numerology, magic art, and even insults for possible source of technical and mathematical terms. As the Amharic saying goes “if genuinely sad, tears flow naturally”; if so desired, one can write mathematical and scientific books in Amharic. The only thing stopping us is our own weakness!

ዶክተር ባሕሩ ካሣሁን

ዶክተር ባሕሩ ካሣሁን የቀዳማዊ ኃይለሥላሴ (ኣዲስ ኣበባ) ዩኒቨርሲቲ፣ ስቴት ዩኒቨርስቲ ኦፍ ኒው ዮርክ እና የኣሪዞና ስቴት ዩኒቨርሲቲ ምሩቅ ነው። በሐረር ራስ መኮንን ትምህርት ቤት፣ በኣዳማ (ናዝሬት) ኣፄ ገላውዲዮስ ትምህርት ቤት፣ በኣሜሪካ ኣሪዞና ስቴት ዩኒቨርሲቲ፣ ኬን ዩኒቨርሲቲ እና በቻይና ኬን ዌንጆ ዩኒቭርሲቲ ሂሳብ፣ ፊዚክስ እና የ”ምህንድስና ጥይቦ” (Engineering Mechanics) ኣስተምሯል። ከሃያ ኣመት በላይ “ቁጥራዊ ትንተና እና ስሌት ዘዴ” (Numerical Analysis and Computational Methods) በፍብረካ (Manufacturing) ስለሚሰጠው ፋይዳ እና ኣገልግሎት በተመራማሪነት በቤል ላቦራቶሪ ሰርቷል። ከምርመራውም ውጤት የሁለት “መብተ-ፈጠራ” (Patent) ባለቤት ሆኗል። በተጨማሪም፣ የ”መገናኛ ጭፍራ ግለታዊ ብገራ እና ቁጥጥር” (Communication Satellite Thermal Design and Control) ተቆጣጣሪ በመሆን ለኣራት ኣመት ኣገልግሏል። ከኣስራሶስት ኣመት በላይ በመምህርነት እና ከሃያ ኣመት በላይ በምህንድስና ተመራማሪነት ያካበተውን ክህሎት እና እውቀት በኣማርኛ ሊፅፍ እየተጋ ነው። ከትጋቱ ውጤቶች ኣንዱ በኣዲስ ኣበባ ዩኒቨርሲቲ (፪ሺህ፬) የታተመው ለፊዚክስ ሂሳባዊ ዝግጅት ሲሆን፣ ይህ መፅሀፍ ደግሞ ሁለተኛው (ተከታዩ) ነው።

ዶክተር ወልደአረጋይ ውብነህ

ዶክተር ወልደአረጋይ ውብነህ በኬን ዩኒቨርሲቲ የሂሳብ ፕሮፌሰር በመሆን ከ፲፱፻፹፭ ጀምሮ እስከ አሁን ሂሳብ በማስተማር፣ የሂሳብ ምርመራ በማድረግ፣ እና የኮሌጅ ተማሪዎችን ምርመራ ማስተማር እና በመምራት ላይ ይገኛሉ። በ፲፱፻፷፱ የመጀመሪያ ዲግሬ በሂሳብ የቀድሞው ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ (ኣሁን አዲስ አባባ ዩኒቨርሲቲ)፣ በ፲፱፻፸፪ ኤም ኤስ ዲግሪ ኤመሪ ዩኒቨርሲቲ በስታቲስቲክስ አና (ባዮሜትሪ)፣ ዶክተር ኦፍ ኤዱኬሽን ፲፱፻፺ ረትገርስ ዩኒቨርሲቲ በትምሀርት ስታቲስቲክስ እና ልክና አግኝተዋል። ከ፲፱፻፸፰ እስከ ፲፱፻፹፭ ቨርጂኒያ ቴክ ኢንስቲቲዩት እና ስቴት ዩኒቨርሲቲ ሂሳብ በማስተማር አገልግለዋል። ከ፲፱፻፸፪ እስከ ፲፱፻፸፬ ቨርጂኒያ ስቴት ዩኒቨርሲቲ በፒትስበርግ የሂሳብ ፕሮፌሰር ነበሩ። ወደ ኣሜሪካ ኣገር ከመምጣታቸው በፊት (፲፱፻፸) ለኣንድ ኣመት ዓፄ ገላውዲዎስ ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት (ናዝሬት ከተማ) ሂሳብ ኣስተምረዋል።

መጽሕፉን ለመግዛት እዚህ ላይ ይጫኑ

The Red Sea Press, 2017

Mathematics/AMHARIC

Trim size: 8.5 X 11 inches

Page count: 602

ISBN: 978-1-56902-527-7

Publisher: The Red Sea Press.

ፕሮፌሰር ባሕሩ ካሣሁን እና ፕሮፌሰር ወልደ-አረጋይ ውብነህ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Social Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “የገቡበት ገብተን አንድ ሰው አናስቀርም – በተለይ አመራሩን” ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ February 15, 2021 11:46 pm
  • የትግራይ ገበሬና የከተማ ነዋሪ በሠራዊታችን ላይ አንድ ጥይት አልተኮሰም – ሪር አድሚራል ክንዱ February 4, 2021 01:51 pm
  • ኢንተርፖል፤ የህወሃት ሳምሪዎች የማይካድራ ጭፍጭፋ ከቦኮሃራም የከፋ ነው February 4, 2021 11:10 am
  • ጄኔራሎች “ተገድለዋል” በሚል የሀሰት መረጃ ሲያሰራጭ የነበረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ February 4, 2021 08:48 am
  • በትግራይ ክልል በሴቶች ላይ ተፈጸመ የተባለውን ጥቃት የሚያጣራ ግብረ ኃይል መቀሌ ገባ February 3, 2021 12:06 pm
  • ፓርቲዎች የምርጫ መወዳደሪያ ምልክቶቻቸውን ወሰዱ February 3, 2021 10:29 am
  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule