• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ነጠላ ተባራይ ንፍቅ ስነ-ስሌት [ካልኩለስ በአማርኛ]

March 16, 2017 04:36 am by Editor Leave a Comment

ይህ መፅሀፍ ለፊዚክስ ሂሳባዊ ዝግጅት በሚል በኣዲስ ኣበባ ዩኒቨርስቲ ፕረስ የታተመው የጥራዝ ፩ ተከታይ በመሆን፣ ለሳይንስ እና ምህንድስና ትምህርት ኣገልግሎት ተጨማሪ ሂሳባዊ ፅንስ-ሃሳቦችን ይሰጣል። ስለሆነም፣ በቅድሚያ ኣጭር ኣልጀብራዊ (Algebraic) እና ስነ-ዘዌያዊ (Trigonometric) ክለሳ ከሰጠ በሁዋላ፣ ስለ”ተግባር” (Function) በሰፊው ያብራራል። ቀጥሎም፣ ዋና የስነ-ስሌት መሰረት በሆነው ለከት (Limit)፣ ስነ-ቅርፅ (Geometry) እና የቀጥተኛ መስመር ዝንባሌ (Slope) በመጠቀም የ”ለውጥ ቅልጥፍና” (Rate of Change) እና ለማንኛውም የተግባር ዝብ (Curve) ዝንባሌ የሚያገለግለውን በስነ-ስሌት ድናን (Derivative) በመባል የሚታወቀውን ያብራራል። የድናን ኣጠቃቀም እና ፋይዳን በተለያዩ የትምህርት ቅርንጫፎች ያሳያል። ለዚህም፣ ከሁለት መቶ ሃምሳ በላይ የሆኑ ምሳሌዎች ከጥቅል ፍቺዎቻችው ጋር በፅሁፉ ተካተዋል።

መፅሃፉን ለመፃፍ ብዙ ቃላትን መተርጎም ኣስፈልጓል። በተቻለን መጠን ከቋንቋው በሚገኙ ቃላት ተጠቅመናል። እርግጥ ከተፀውኦ ስም የተገኙ (ለምሳሌ ኣልጀብራ) ወይም በኣማርኛ ስር የሰደዱ (ለምሳሌ ዜሮ) የመሳሰሉትን ቃላት ኣልተረጎምንም። የፅሁፉ ኣላማዎች (፩) ትምህርትን እና ተደራሽነቱን ለማስፋፋት፣ (፪) ባህልን እና ቋንቋውን ለማዳበር (፫) በሃገሪቱ የነበሩ ሳይንሳዊ እና ምህንድስና ክህለቶች እንዳይጠፉ ለማድረግ፣ (፬) ኣማርኛ ሂሳባዊም ሆነ ሳይንሳዊ ክህሎት የለውም የሚለውን የተሳሳተ ከፈን ለመግፈፍ እና (፭) ሌሎች ሂሳባዊም ሆነ ሳይንሳዊ ደራሲያንን በኣማርኛ እንዲፅፉ ለማበራታት ነው። ይህ ፅሁፍ በሚዘጋጅበት ጊዜ ብዙ ሂሳባዊ እና ሳይንሳዊ ቃላት ከጥንት ጀምሮ በኢትዮጵያ ከነበሩ ጥበቦች፣ ለምሳሌ፣ ከሸክላ፣ ከቀንድ፣ ከብር እና ወርቅ ኣንጥሮሽ፣ ከጦር (መከላከያ) ስልት፣ ከሃይማኖት ፅሁፍ፣ ከግብይይት፣ ከህፃናት ጨዋታ፣ ከኮከብ ቆጠራ፣ ከጥንቆላ እና ከስድብም ሳይቀር ተገኝተዋል። ለትርጉምም ኣገልግለዋል። “ከኣንጀት ካለቀሱ እንባ እይገድም” እንደሚባለው፣ ከተፈለገ ሳይንሳዊ ፅሁፍ በኣማርኛ መፃፍ ይቻላል። የሚያግደን የራሳችን ስንፈት ብቻ ነው!

As a follow up, this book builds upon the mathematical-conceptual foundations for science and engineering laid down by “Mathematical Preparations for Physics”, published by Addis Ababa University Press. To this end, after brief reviews of Algebra and Trigonometry, it expands on the concept of functions. It then introduces the limit, the foundation of differential calculus. It introduces the concept of rate of change with the aid of limits, the slope of a straight line and simple geometry, from which it transitions to the slope of a generalized curve and introduces and expounds the major concept of the derivative. It demonstrates the application of the derivative in various disciplines by providing over two-hundred and fifty fully solved examples.

Writing this book required the translation of several words. The authors have tried, to extent possible, to draw from the Amharic language.  They have, however, preserved words derived from proper noun (such as Algebra) or words like “zero” that are already assimilated in Amharic.  Some of the objectives of the book are: (1) to expand education and its accessibility, (2) to nurture cultural and linguistic growth, (3) to preserve Ethiopia’s long existing scientific and engineering skills, (4) to dispel the erroneous belief that Amharic lacks both mathematical and scientific capabilities, and (5) to encourage other authors to write Amharic textbooks.  In the preparation of this textbook, the authors have drawn from the rich and ancient technologies in existence since time immemorial. They have drawn from ancient Ethiopian crafts such as ceramics, horn lathing, silver and gold smith works, weaving, defense strategies, religious texts, business, children’s games, astrology and numerology, magic art, and even insults for possible source of technical and mathematical terms. As the Amharic saying goes “if genuinely sad, tears flow naturally”; if so desired, one can write mathematical and scientific books in Amharic. The only thing stopping us is our own weakness!

ዶክተር ባሕሩ ካሣሁን

ዶክተር ባሕሩ ካሣሁን የቀዳማዊ ኃይለሥላሴ (ኣዲስ ኣበባ) ዩኒቨርሲቲ፣ ስቴት ዩኒቨርስቲ ኦፍ ኒው ዮርክ እና የኣሪዞና ስቴት ዩኒቨርሲቲ ምሩቅ ነው። በሐረር ራስ መኮንን ትምህርት ቤት፣ በኣዳማ (ናዝሬት) ኣፄ ገላውዲዮስ ትምህርት ቤት፣ በኣሜሪካ ኣሪዞና ስቴት ዩኒቨርሲቲ፣ ኬን ዩኒቨርሲቲ እና በቻይና ኬን ዌንጆ ዩኒቭርሲቲ ሂሳብ፣ ፊዚክስ እና የ”ምህንድስና ጥይቦ” (Engineering Mechanics) ኣስተምሯል። ከሃያ ኣመት በላይ “ቁጥራዊ ትንተና እና ስሌት ዘዴ” (Numerical Analysis and Computational Methods) በፍብረካ (Manufacturing) ስለሚሰጠው ፋይዳ እና ኣገልግሎት በተመራማሪነት በቤል ላቦራቶሪ ሰርቷል። ከምርመራውም ውጤት የሁለት “መብተ-ፈጠራ” (Patent) ባለቤት ሆኗል። በተጨማሪም፣ የ”መገናኛ ጭፍራ ግለታዊ ብገራ እና ቁጥጥር” (Communication Satellite Thermal Design and Control) ተቆጣጣሪ በመሆን ለኣራት ኣመት ኣገልግሏል። ከኣስራሶስት ኣመት በላይ በመምህርነት እና ከሃያ ኣመት በላይ በምህንድስና ተመራማሪነት ያካበተውን ክህሎት እና እውቀት በኣማርኛ ሊፅፍ እየተጋ ነው። ከትጋቱ ውጤቶች ኣንዱ በኣዲስ ኣበባ ዩኒቨርሲቲ (፪ሺህ፬) የታተመው ለፊዚክስ ሂሳባዊ ዝግጅት ሲሆን፣ ይህ መፅሀፍ ደግሞ ሁለተኛው (ተከታዩ) ነው።

ዶክተር ወልደአረጋይ ውብነህ

ዶክተር ወልደአረጋይ ውብነህ በኬን ዩኒቨርሲቲ የሂሳብ ፕሮፌሰር በመሆን ከ፲፱፻፹፭ ጀምሮ እስከ አሁን ሂሳብ በማስተማር፣ የሂሳብ ምርመራ በማድረግ፣ እና የኮሌጅ ተማሪዎችን ምርመራ ማስተማር እና በመምራት ላይ ይገኛሉ። በ፲፱፻፷፱ የመጀመሪያ ዲግሬ በሂሳብ የቀድሞው ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ (ኣሁን አዲስ አባባ ዩኒቨርሲቲ)፣ በ፲፱፻፸፪ ኤም ኤስ ዲግሪ ኤመሪ ዩኒቨርሲቲ በስታቲስቲክስ አና (ባዮሜትሪ)፣ ዶክተር ኦፍ ኤዱኬሽን ፲፱፻፺ ረትገርስ ዩኒቨርሲቲ በትምሀርት ስታቲስቲክስ እና ልክና አግኝተዋል። ከ፲፱፻፸፰ እስከ ፲፱፻፹፭ ቨርጂኒያ ቴክ ኢንስቲቲዩት እና ስቴት ዩኒቨርሲቲ ሂሳብ በማስተማር አገልግለዋል። ከ፲፱፻፸፪ እስከ ፲፱፻፸፬ ቨርጂኒያ ስቴት ዩኒቨርሲቲ በፒትስበርግ የሂሳብ ፕሮፌሰር ነበሩ። ወደ ኣሜሪካ ኣገር ከመምጣታቸው በፊት (፲፱፻፸) ለኣንድ ኣመት ዓፄ ገላውዲዎስ ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት (ናዝሬት ከተማ) ሂሳብ ኣስተምረዋል።

መጽሕፉን ለመግዛት እዚህ ላይ ይጫኑ

The Red Sea Press, 2017

Mathematics/AMHARIC

Trim size: 8.5 X 11 inches

Page count: 602

ISBN: 978-1-56902-527-7

Publisher: The Red Sea Press.

ፕሮፌሰር ባሕሩ ካሣሁን እና ፕሮፌሰር ወልደ-አረጋይ ውብነህ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Social Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule