• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ነጠላ ተባራይ ንፍቅ ስነ-ስሌት [ካልኩለስ በአማርኛ]

March 16, 2017 04:36 am by Editor Leave a Comment

ይህ መፅሀፍ ለፊዚክስ ሂሳባዊ ዝግጅት በሚል በኣዲስ ኣበባ ዩኒቨርስቲ ፕረስ የታተመው የጥራዝ ፩ ተከታይ በመሆን፣ ለሳይንስ እና ምህንድስና ትምህርት ኣገልግሎት ተጨማሪ ሂሳባዊ ፅንስ-ሃሳቦችን ይሰጣል። ስለሆነም፣ በቅድሚያ ኣጭር ኣልጀብራዊ (Algebraic) እና ስነ-ዘዌያዊ (Trigonometric) ክለሳ ከሰጠ በሁዋላ፣ ስለ”ተግባር” (Function) በሰፊው ያብራራል። ቀጥሎም፣ ዋና የስነ-ስሌት መሰረት በሆነው ለከት (Limit)፣ ስነ-ቅርፅ (Geometry) እና የቀጥተኛ መስመር ዝንባሌ (Slope) በመጠቀም የ”ለውጥ ቅልጥፍና” (Rate of Change) እና ለማንኛውም የተግባር ዝብ (Curve) ዝንባሌ የሚያገለግለውን በስነ-ስሌት ድናን (Derivative) በመባል የሚታወቀውን ያብራራል። የድናን ኣጠቃቀም እና ፋይዳን በተለያዩ የትምህርት ቅርንጫፎች ያሳያል። ለዚህም፣ ከሁለት መቶ ሃምሳ በላይ የሆኑ ምሳሌዎች ከጥቅል ፍቺዎቻችው ጋር በፅሁፉ ተካተዋል።

መፅሃፉን ለመፃፍ ብዙ ቃላትን መተርጎም ኣስፈልጓል። በተቻለን መጠን ከቋንቋው በሚገኙ ቃላት ተጠቅመናል። እርግጥ ከተፀውኦ ስም የተገኙ (ለምሳሌ ኣልጀብራ) ወይም በኣማርኛ ስር የሰደዱ (ለምሳሌ ዜሮ) የመሳሰሉትን ቃላት ኣልተረጎምንም። የፅሁፉ ኣላማዎች (፩) ትምህርትን እና ተደራሽነቱን ለማስፋፋት፣ (፪) ባህልን እና ቋንቋውን ለማዳበር (፫) በሃገሪቱ የነበሩ ሳይንሳዊ እና ምህንድስና ክህለቶች እንዳይጠፉ ለማድረግ፣ (፬) ኣማርኛ ሂሳባዊም ሆነ ሳይንሳዊ ክህሎት የለውም የሚለውን የተሳሳተ ከፈን ለመግፈፍ እና (፭) ሌሎች ሂሳባዊም ሆነ ሳይንሳዊ ደራሲያንን በኣማርኛ እንዲፅፉ ለማበራታት ነው። ይህ ፅሁፍ በሚዘጋጅበት ጊዜ ብዙ ሂሳባዊ እና ሳይንሳዊ ቃላት ከጥንት ጀምሮ በኢትዮጵያ ከነበሩ ጥበቦች፣ ለምሳሌ፣ ከሸክላ፣ ከቀንድ፣ ከብር እና ወርቅ ኣንጥሮሽ፣ ከጦር (መከላከያ) ስልት፣ ከሃይማኖት ፅሁፍ፣ ከግብይይት፣ ከህፃናት ጨዋታ፣ ከኮከብ ቆጠራ፣ ከጥንቆላ እና ከስድብም ሳይቀር ተገኝተዋል። ለትርጉምም ኣገልግለዋል። “ከኣንጀት ካለቀሱ እንባ እይገድም” እንደሚባለው፣ ከተፈለገ ሳይንሳዊ ፅሁፍ በኣማርኛ መፃፍ ይቻላል። የሚያግደን የራሳችን ስንፈት ብቻ ነው!

As a follow up, this book builds upon the mathematical-conceptual foundations for science and engineering laid down by “Mathematical Preparations for Physics”, published by Addis Ababa University Press. To this end, after brief reviews of Algebra and Trigonometry, it expands on the concept of functions. It then introduces the limit, the foundation of differential calculus. It introduces the concept of rate of change with the aid of limits, the slope of a straight line and simple geometry, from which it transitions to the slope of a generalized curve and introduces and expounds the major concept of the derivative. It demonstrates the application of the derivative in various disciplines by providing over two-hundred and fifty fully solved examples.

Writing this book required the translation of several words. The authors have tried, to extent possible, to draw from the Amharic language.  They have, however, preserved words derived from proper noun (such as Algebra) or words like “zero” that are already assimilated in Amharic.  Some of the objectives of the book are: (1) to expand education and its accessibility, (2) to nurture cultural and linguistic growth, (3) to preserve Ethiopia’s long existing scientific and engineering skills, (4) to dispel the erroneous belief that Amharic lacks both mathematical and scientific capabilities, and (5) to encourage other authors to write Amharic textbooks.  In the preparation of this textbook, the authors have drawn from the rich and ancient technologies in existence since time immemorial. They have drawn from ancient Ethiopian crafts such as ceramics, horn lathing, silver and gold smith works, weaving, defense strategies, religious texts, business, children’s games, astrology and numerology, magic art, and even insults for possible source of technical and mathematical terms. As the Amharic saying goes “if genuinely sad, tears flow naturally”; if so desired, one can write mathematical and scientific books in Amharic. The only thing stopping us is our own weakness!

ዶክተር ባሕሩ ካሣሁን

ዶክተር ባሕሩ ካሣሁን የቀዳማዊ ኃይለሥላሴ (ኣዲስ ኣበባ) ዩኒቨርሲቲ፣ ስቴት ዩኒቨርስቲ ኦፍ ኒው ዮርክ እና የኣሪዞና ስቴት ዩኒቨርሲቲ ምሩቅ ነው። በሐረር ራስ መኮንን ትምህርት ቤት፣ በኣዳማ (ናዝሬት) ኣፄ ገላውዲዮስ ትምህርት ቤት፣ በኣሜሪካ ኣሪዞና ስቴት ዩኒቨርሲቲ፣ ኬን ዩኒቨርሲቲ እና በቻይና ኬን ዌንጆ ዩኒቭርሲቲ ሂሳብ፣ ፊዚክስ እና የ”ምህንድስና ጥይቦ” (Engineering Mechanics) ኣስተምሯል። ከሃያ ኣመት በላይ “ቁጥራዊ ትንተና እና ስሌት ዘዴ” (Numerical Analysis and Computational Methods) በፍብረካ (Manufacturing) ስለሚሰጠው ፋይዳ እና ኣገልግሎት በተመራማሪነት በቤል ላቦራቶሪ ሰርቷል። ከምርመራውም ውጤት የሁለት “መብተ-ፈጠራ” (Patent) ባለቤት ሆኗል። በተጨማሪም፣ የ”መገናኛ ጭፍራ ግለታዊ ብገራ እና ቁጥጥር” (Communication Satellite Thermal Design and Control) ተቆጣጣሪ በመሆን ለኣራት ኣመት ኣገልግሏል። ከኣስራሶስት ኣመት በላይ በመምህርነት እና ከሃያ ኣመት በላይ በምህንድስና ተመራማሪነት ያካበተውን ክህሎት እና እውቀት በኣማርኛ ሊፅፍ እየተጋ ነው። ከትጋቱ ውጤቶች ኣንዱ በኣዲስ ኣበባ ዩኒቨርሲቲ (፪ሺህ፬) የታተመው ለፊዚክስ ሂሳባዊ ዝግጅት ሲሆን፣ ይህ መፅሀፍ ደግሞ ሁለተኛው (ተከታዩ) ነው።

ዶክተር ወልደአረጋይ ውብነህ

ዶክተር ወልደአረጋይ ውብነህ በኬን ዩኒቨርሲቲ የሂሳብ ፕሮፌሰር በመሆን ከ፲፱፻፹፭ ጀምሮ እስከ አሁን ሂሳብ በማስተማር፣ የሂሳብ ምርመራ በማድረግ፣ እና የኮሌጅ ተማሪዎችን ምርመራ ማስተማር እና በመምራት ላይ ይገኛሉ። በ፲፱፻፷፱ የመጀመሪያ ዲግሬ በሂሳብ የቀድሞው ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ (ኣሁን አዲስ አባባ ዩኒቨርሲቲ)፣ በ፲፱፻፸፪ ኤም ኤስ ዲግሪ ኤመሪ ዩኒቨርሲቲ በስታቲስቲክስ አና (ባዮሜትሪ)፣ ዶክተር ኦፍ ኤዱኬሽን ፲፱፻፺ ረትገርስ ዩኒቨርሲቲ በትምሀርት ስታቲስቲክስ እና ልክና አግኝተዋል። ከ፲፱፻፸፰ እስከ ፲፱፻፹፭ ቨርጂኒያ ቴክ ኢንስቲቲዩት እና ስቴት ዩኒቨርሲቲ ሂሳብ በማስተማር አገልግለዋል። ከ፲፱፻፸፪ እስከ ፲፱፻፸፬ ቨርጂኒያ ስቴት ዩኒቨርሲቲ በፒትስበርግ የሂሳብ ፕሮፌሰር ነበሩ። ወደ ኣሜሪካ ኣገር ከመምጣታቸው በፊት (፲፱፻፸) ለኣንድ ኣመት ዓፄ ገላውዲዎስ ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት (ናዝሬት ከተማ) ሂሳብ ኣስተምረዋል።

መጽሕፉን ለመግዛት እዚህ ላይ ይጫኑ

The Red Sea Press, 2017

Mathematics/AMHARIC

Trim size: 8.5 X 11 inches

Page count: 602

ISBN: 978-1-56902-527-7

Publisher: The Red Sea Press.

ፕሮፌሰር ባሕሩ ካሣሁን እና ፕሮፌሰር ወልደ-አረጋይ ውብነህ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Social Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule