• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ፈትለወርቅን ማንገስ ያቃተው የስብሃት ቡድን የአዜብ ዕገዳ እንዲነሳ ሊቀበል ነው

November 29, 2017 03:02 pm by Editor 3 Comments

መቀሌ ላይ ሲሰዳደቡ የቆዩት የበረሃ ወንበዴዎች ደብረጽዮንን መሪያቸው አድርገው በመምረጥ የፈትለወርቅን ዋና መሪነት ውድቅ አድርገዋል። ይህ ለስብሃት ነጋ ሽንፈት የሆነው ክስተት በአዜብ ላይ የተጣለው ዕገዳ እንዲነሳ ወደመቀበል ሊገደድ ይችላል እየተባለ ነው። የኤፈርት ጉዳይ አሁንም አከራካሪ ሆኗል።

ከልክ ባለፈ ሁኔታ መቀሌ ላይ ሲወነጃጀሉና ሲሰዳደቡ የቆዩት የህወሓት የበረሃና የድህረ በረሃ ወንበዴዎች በመጨረሻ ላይ የስለላውን ማሽን ደብረጽዮን ገብረሚካኤልን ዋና መሪያቸው አድርገው መርጠዋል። “ሞንጆሪኖ” በማለት ሳሞራ ዩኑስ ጣሊያናዊ ስም የሰጣት ፈትለወርቅ በነስብሃት ቡድን የዋናውን ቦታ እንድትይዝ ከፍተኛ ጥረት ቢደረግላትም “የመለስ ራዕይ” አስጠባቂ የሆነው ቡድን አልረታም በማለት ውድቅ አድርጓታል። በውጤቱም በዓለምአቀፍ የመረጃ ቋት በአሸባሪነት የተመዘገበው የህወሓት ቡድን ምክትል ሆና ተመርጣለች።

የዛሬ 12ዓመት አካባቢ “ሎንዶን ለትምህርት በነበርኩበት ጊዜ በኮምፒውተር መጻፍ አልችልም ነበር፤ የሚቀርቡ ወረቀቶችን በእጄ ጽፌ ነበር የማቀርበው” በማለት በርግጥ የመማሯን ሁኔታ አጠራጣሪ አድርጋ የተናገረችው ፈትለወርቅ፤ የስብሃት ቡድን የህወሓት መሪ ሊያደርጋት ከፍተኛ ሙከራ ቢያደርግም በ“ራዕይ አስጠባቂዎቹ” ቡድን ውድቅ ተደርጎበታል። ውጤቱን መቀበል ግን የሆነበት የስብሃት ቡድን በምክትልነት የመመረጧን ጉዳይ እንደ ድል ወስዶ ስልታዊ ማፈግፈግ አድርጓል።

“የመለስ ራዕይ” አስጠባቂ ቡድን “የግል ራዕይ የለም፤ ራዕይ ድርጅት ነው” በሚለው የስብሃት ቡድን ከፍተኛ ጥቃት በደረሰበት ጊዜ ሒሷን መዋጥ ያቃታት አዜብ ስብሰባውን ረግጣ መውጣቷ ይታወቃል። በአምቦ ዩኒቨርሲቲ መምህር የሆነው ስዩም ተሾመ “ውስጥ አዋቂውን” ጠቅሶ በፌስቡክ ገጹ ላይ እንደተናገረው “የመለስ አጥንት ይወጋናል” የሚለው የራዕይ አስጠባቂ ቡድን የዳያስፖራ (ትግሬዎችን) ድጋፍ በከፍተኛ ሁኔታ አግኝቷል። እነዚሁ የመለስ ራዕይ ደጋፊ ዳያስፖራዎች “እናከብራችኋለን እንጂ አንፈራችሁም!” የሚል መልዕክት በስልክና ኢሜል አድራሻዎች በገፍ ሲልኩ” መቆየታቸውን አስታውቋል። እንቅስቃሴውን ማሸነፍ የተሳነው የስብሃት ነጋ ቡድን ፈትለወርቅን በምክትልነት አስመርጦ እጅ መስጠት ግድ ሆኖበታል።

ይህ እጅ መስጠት በአዜብ ላይ የተጣለውን ዕገዳ እንዲነሳ እስከመቀበል ሊያደርስ ይችላል የሚል ግምት እየተሰጠው ይገኛል። በህወሓት የወንበዴዎች ቡድን አሠራር መሠረት ስብሰባ ረግጦ መውጣት ዋጋ የሚያስከፍል መሆኑ የነስዬ ታሪክ ምስክር ነው። ከዚህ አንጻር የአዜብ ዕገዳ እስከምን እንደሚደርስ በቅርቡ የሚታይ ይሆናል።

ከህወሓት ኅልውና ጋር በተያያዘ የኤፈርት ጉዳይ ትልቁ አጀንዳ በመሆኑ የስብሃት ቡድን ድርጅቱን ወደራሱ ቤተሰብ ለመጠቅለል የሚያደርገው ሙከራ ደንቃራ ገጥሞታል። በመቀሌው የወንበዴዎቹ ስብሰባ ላይ “ከኤፈርት ያለ አግባብ የወሰድከውን 30 ሚሊዮን ዶላር መልስ” የተባለው ስብሃት “ባለቤት የሌለው መስሎኝ ነው የወሰድኩት” በማለት ምላሽ መስጠቱን ስዩም ውስጥ አዋቂ ምንጮቹን ጠቅሶ ዘግቧል። ከዚህ አንጻር የወንድሙ ልጅ የሆነችውን ፈትለወርቅን በማንገስ ኤፈርትንም ለመቆጣጠር ያለመው የስብሃት ጸረ-መለስ ራዕይ ቡድን ኤፈርትንም ለመለስ ራዕይ አስጠባቂ ቡድን ያስረክባል የሚለው ግምት እያየለ መጥቷል።

የበረሃ ወንበዴዎቹ ከዚህ ሁሉ ስድድብና መረን የለቀቀ መናናቅ በኋላ የአሸባሪ ቡድኑን ኃላፊ አድርጎ የቀድሞ ወንበዴዎችን እና ከበረሃ መልስ ወደ ድርጅቱ የገቡትን በመቀላቀል “ሥራ (አሸባሪ) አስፈጻሚ” አድርጎ የሚከተሉትን መርጧል፤

ደብረጽዮን ገብረሚካኤል
ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሔር
ዓለም ገብረዋህድ
አስመላሽ ወልደሥላሴ
ጌታቸው ረዳ
አዲስዓለም ባሌማ
ኬርያ ኢብራሂም
አብርሃም ተከስተ
ጌታቸው አሰፋ

ከዚህ ቀጥሎ የሚጠበቀው ከላይ የተጠቀሱትን ጨምሮ ከትምህርትና መልካም አስተሳሰብ የጸዱ በርካታ ወንበዴዎችና ዘራፊዎች በሚሰበሰቡበት “ድርጅታዊ ጉባዔ” ላይ የአዜብ “ጎላ” መስፍንን ዕድል ፈንታ መወሰን ይሆናል። ከተሳካላት በ“መለስ ራዕይ” መቀመጫዋን ታስተካክል ይሆናል፤ ካልሆነም “ታጋይ አይሞትም” የሚል “ጉሊት” ከፍታ ከዚህ በፊት የተናገረችውን “ሃፍታም” የመሆን “ራዕይዋን” ለማሳካት ደፋ ቀና የምትልበት “ብሩህ” መጪ ጊዜ ይሆንላታል በማለት አስተያየት ሰጪዎች ተሳልቀዋል።

ለዜናው ቅንብር የተጠቀምናቸው ምንጮች፤ ሪፖርተር እና Ethio think tank ናቸው።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Mulugeta Andargie says

    November 30, 2017 03:49 am at 3:49 am

    ዶ/ር ደብረ ጽዮን!! የትግራይ ክልል ካንተ ብዙ ይጠብቃል!! በተለይም!በተለይም! የክልሉ መንግስት ከፌደራሉ መንግስት ጋር ተባብሮ የመስራት ድክመት ስለሚታይ: ክልሎች የተገቢውን ቦታ እንዲይዙ ያላሰለሰ ጥረት: በእኩልነት መተያየት(ታክስ:የገበያ ትንንቅ:የፌደራሉን ስራ ማወቅ:ግብር አሰባሰብ:የፌደራሉን ድጎማ:ወዘተ) የትግራይ ህዝብ ማሳወቅና ግንዛቤ እንዲኖረው ማድረግ:ከስራ አስፈጻሚው ብዙይጠበቃል::ተገቢውን ሰው በተገቢው ቦታ ማስቀመጥም ከትችት ያድናል! ገና ለገና ታግሏል በማለት ስህተትን መንቀስ ነውር እንዳይደለ መማርና ማስተማር ለእድገት ወሳኝ ነው::

    Reply
  2. aradw says

    December 1, 2017 01:36 am at 1:36 am

    I do not see this overrated news, from radio TV,and FB in the diaspora. These are people who are grown under the TPLF propaganda, idea and when it comes to Ethiopian politics one is not different from the other. The drunken and hashis addict Gecho to Mongerino and others that can be said a lot but not here. These are bunch of murderers, assassins and giving them this much importance saddens me very much. What happened is happened. What are we doing now and what role are we playing to bring their demise. I will continue supporting what is going home specially what the Oromo Kerro are doing. I CONTINUE TO DO IN MY CAPACITY USING EVERY SITUATION TO EXPOSE THE EVILS OF TPLF. i am sorry to see my country are led by these thugs.

    Reply
  3. Ayu says

    December 1, 2017 06:54 am at 6:54 am

    thank you we (Ethiopian) need more info about the current situation including independent sources on the ground. Information is a power and peace full tool better than a GUN to change the situation on the ground.

    Thank you again

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule