• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ፈትለወርቅን ማንገስ ያቃተው የስብሃት ቡድን የአዜብ ዕገዳ እንዲነሳ ሊቀበል ነው

November 29, 2017 03:02 pm by Editor 3 Comments

መቀሌ ላይ ሲሰዳደቡ የቆዩት የበረሃ ወንበዴዎች ደብረጽዮንን መሪያቸው አድርገው በመምረጥ የፈትለወርቅን ዋና መሪነት ውድቅ አድርገዋል። ይህ ለስብሃት ነጋ ሽንፈት የሆነው ክስተት በአዜብ ላይ የተጣለው ዕገዳ እንዲነሳ ወደመቀበል ሊገደድ ይችላል እየተባለ ነው። የኤፈርት ጉዳይ አሁንም አከራካሪ ሆኗል።

ከልክ ባለፈ ሁኔታ መቀሌ ላይ ሲወነጃጀሉና ሲሰዳደቡ የቆዩት የህወሓት የበረሃና የድህረ በረሃ ወንበዴዎች በመጨረሻ ላይ የስለላውን ማሽን ደብረጽዮን ገብረሚካኤልን ዋና መሪያቸው አድርገው መርጠዋል። “ሞንጆሪኖ” በማለት ሳሞራ ዩኑስ ጣሊያናዊ ስም የሰጣት ፈትለወርቅ በነስብሃት ቡድን የዋናውን ቦታ እንድትይዝ ከፍተኛ ጥረት ቢደረግላትም “የመለስ ራዕይ” አስጠባቂ የሆነው ቡድን አልረታም በማለት ውድቅ አድርጓታል። በውጤቱም በዓለምአቀፍ የመረጃ ቋት በአሸባሪነት የተመዘገበው የህወሓት ቡድን ምክትል ሆና ተመርጣለች።

የዛሬ 12ዓመት አካባቢ “ሎንዶን ለትምህርት በነበርኩበት ጊዜ በኮምፒውተር መጻፍ አልችልም ነበር፤ የሚቀርቡ ወረቀቶችን በእጄ ጽፌ ነበር የማቀርበው” በማለት በርግጥ የመማሯን ሁኔታ አጠራጣሪ አድርጋ የተናገረችው ፈትለወርቅ፤ የስብሃት ቡድን የህወሓት መሪ ሊያደርጋት ከፍተኛ ሙከራ ቢያደርግም በ“ራዕይ አስጠባቂዎቹ” ቡድን ውድቅ ተደርጎበታል። ውጤቱን መቀበል ግን የሆነበት የስብሃት ቡድን በምክትልነት የመመረጧን ጉዳይ እንደ ድል ወስዶ ስልታዊ ማፈግፈግ አድርጓል።

“የመለስ ራዕይ” አስጠባቂ ቡድን “የግል ራዕይ የለም፤ ራዕይ ድርጅት ነው” በሚለው የስብሃት ቡድን ከፍተኛ ጥቃት በደረሰበት ጊዜ ሒሷን መዋጥ ያቃታት አዜብ ስብሰባውን ረግጣ መውጣቷ ይታወቃል። በአምቦ ዩኒቨርሲቲ መምህር የሆነው ስዩም ተሾመ “ውስጥ አዋቂውን” ጠቅሶ በፌስቡክ ገጹ ላይ እንደተናገረው “የመለስ አጥንት ይወጋናል” የሚለው የራዕይ አስጠባቂ ቡድን የዳያስፖራ (ትግሬዎችን) ድጋፍ በከፍተኛ ሁኔታ አግኝቷል። እነዚሁ የመለስ ራዕይ ደጋፊ ዳያስፖራዎች “እናከብራችኋለን እንጂ አንፈራችሁም!” የሚል መልዕክት በስልክና ኢሜል አድራሻዎች በገፍ ሲልኩ” መቆየታቸውን አስታውቋል። እንቅስቃሴውን ማሸነፍ የተሳነው የስብሃት ነጋ ቡድን ፈትለወርቅን በምክትልነት አስመርጦ እጅ መስጠት ግድ ሆኖበታል።

ይህ እጅ መስጠት በአዜብ ላይ የተጣለውን ዕገዳ እንዲነሳ እስከመቀበል ሊያደርስ ይችላል የሚል ግምት እየተሰጠው ይገኛል። በህወሓት የወንበዴዎች ቡድን አሠራር መሠረት ስብሰባ ረግጦ መውጣት ዋጋ የሚያስከፍል መሆኑ የነስዬ ታሪክ ምስክር ነው። ከዚህ አንጻር የአዜብ ዕገዳ እስከምን እንደሚደርስ በቅርቡ የሚታይ ይሆናል።

ከህወሓት ኅልውና ጋር በተያያዘ የኤፈርት ጉዳይ ትልቁ አጀንዳ በመሆኑ የስብሃት ቡድን ድርጅቱን ወደራሱ ቤተሰብ ለመጠቅለል የሚያደርገው ሙከራ ደንቃራ ገጥሞታል። በመቀሌው የወንበዴዎቹ ስብሰባ ላይ “ከኤፈርት ያለ አግባብ የወሰድከውን 30 ሚሊዮን ዶላር መልስ” የተባለው ስብሃት “ባለቤት የሌለው መስሎኝ ነው የወሰድኩት” በማለት ምላሽ መስጠቱን ስዩም ውስጥ አዋቂ ምንጮቹን ጠቅሶ ዘግቧል። ከዚህ አንጻር የወንድሙ ልጅ የሆነችውን ፈትለወርቅን በማንገስ ኤፈርትንም ለመቆጣጠር ያለመው የስብሃት ጸረ-መለስ ራዕይ ቡድን ኤፈርትንም ለመለስ ራዕይ አስጠባቂ ቡድን ያስረክባል የሚለው ግምት እያየለ መጥቷል።

የበረሃ ወንበዴዎቹ ከዚህ ሁሉ ስድድብና መረን የለቀቀ መናናቅ በኋላ የአሸባሪ ቡድኑን ኃላፊ አድርጎ የቀድሞ ወንበዴዎችን እና ከበረሃ መልስ ወደ ድርጅቱ የገቡትን በመቀላቀል “ሥራ (አሸባሪ) አስፈጻሚ” አድርጎ የሚከተሉትን መርጧል፤

ደብረጽዮን ገብረሚካኤል
ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሔር
ዓለም ገብረዋህድ
አስመላሽ ወልደሥላሴ
ጌታቸው ረዳ
አዲስዓለም ባሌማ
ኬርያ ኢብራሂም
አብርሃም ተከስተ
ጌታቸው አሰፋ

ከዚህ ቀጥሎ የሚጠበቀው ከላይ የተጠቀሱትን ጨምሮ ከትምህርትና መልካም አስተሳሰብ የጸዱ በርካታ ወንበዴዎችና ዘራፊዎች በሚሰበሰቡበት “ድርጅታዊ ጉባዔ” ላይ የአዜብ “ጎላ” መስፍንን ዕድል ፈንታ መወሰን ይሆናል። ከተሳካላት በ“መለስ ራዕይ” መቀመጫዋን ታስተካክል ይሆናል፤ ካልሆነም “ታጋይ አይሞትም” የሚል “ጉሊት” ከፍታ ከዚህ በፊት የተናገረችውን “ሃፍታም” የመሆን “ራዕይዋን” ለማሳካት ደፋ ቀና የምትልበት “ብሩህ” መጪ ጊዜ ይሆንላታል በማለት አስተያየት ሰጪዎች ተሳልቀዋል።

ለዜናው ቅንብር የተጠቀምናቸው ምንጮች፤ ሪፖርተር እና Ethio think tank ናቸው።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Mulugeta Andargie says

    November 30, 2017 03:49 am at 3:49 am

    ዶ/ር ደብረ ጽዮን!! የትግራይ ክልል ካንተ ብዙ ይጠብቃል!! በተለይም!በተለይም! የክልሉ መንግስት ከፌደራሉ መንግስት ጋር ተባብሮ የመስራት ድክመት ስለሚታይ: ክልሎች የተገቢውን ቦታ እንዲይዙ ያላሰለሰ ጥረት: በእኩልነት መተያየት(ታክስ:የገበያ ትንንቅ:የፌደራሉን ስራ ማወቅ:ግብር አሰባሰብ:የፌደራሉን ድጎማ:ወዘተ) የትግራይ ህዝብ ማሳወቅና ግንዛቤ እንዲኖረው ማድረግ:ከስራ አስፈጻሚው ብዙይጠበቃል::ተገቢውን ሰው በተገቢው ቦታ ማስቀመጥም ከትችት ያድናል! ገና ለገና ታግሏል በማለት ስህተትን መንቀስ ነውር እንዳይደለ መማርና ማስተማር ለእድገት ወሳኝ ነው::

    Reply
  2. aradw says

    December 1, 2017 01:36 am at 1:36 am

    I do not see this overrated news, from radio TV,and FB in the diaspora. These are people who are grown under the TPLF propaganda, idea and when it comes to Ethiopian politics one is not different from the other. The drunken and hashis addict Gecho to Mongerino and others that can be said a lot but not here. These are bunch of murderers, assassins and giving them this much importance saddens me very much. What happened is happened. What are we doing now and what role are we playing to bring their demise. I will continue supporting what is going home specially what the Oromo Kerro are doing. I CONTINUE TO DO IN MY CAPACITY USING EVERY SITUATION TO EXPOSE THE EVILS OF TPLF. i am sorry to see my country are led by these thugs.

    Reply
  3. Ayu says

    December 1, 2017 06:54 am at 6:54 am

    thank you we (Ethiopian) need more info about the current situation including independent sources on the ground. Information is a power and peace full tool better than a GUN to change the situation on the ground.

    Thank you again

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule