• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሳህለወርቅ ዘውዴ – የኢትዮጵያ የመጀመሪያዋ ሴት ፕሬዚዳንት

October 26, 2018 11:39 am by Editor 2 Comments

ተወልደው ያደጉት አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ሲሆን የመጀመሪያና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን የተከታተሉት በሊሴ ገብረማርያም ትምህርት ቤት ነው። አራት ሴት ልጆች ለነበሯቸው ወላጆቻቸው የመጀመሪያ ልጅ የሆኑት ሳህለወርቅ ዘውዴ ገና በ17 ዓመታቸው ነጻ የትምህርት ዕደል አግኝተው ወደ ፈረንሳይ በማቅናት ሞንትፔልየር (Montpellier) በምትባለው የፈረንሳይ ከተማ በሚገኘው ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ሞንትፔልየር (University of Montpellier) የተፈጥሮ ሳይንስን አጥንተዋል።

በሀገረ ፈረንሳይ ለዘጠኝ ዓመታት ከቆዩ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ በመመለስ በትምህርት ሚኒስቴር ውስጥ የሕዝብ ግንኙነት ክፍልን ማገልገል ጀመሩ። ቆይተውም የሕዝብ ግንኙነት ክፍሉን በበላይነት መርተዋል። ከዚያም ወደ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በመዘዋወር በተለያዩ የሥራ ኃላፊነቶች አገልግለዋል።

ወ/ሮ ሳህለወርቅ ዘውዴ በአምባሳደርነት ለመሾም ከአምባሳደር ዮዲት እምሩ ቀጥሎ ሁለተኛዋ እንስት ናቸው። በመጀመሪያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሆነው የተሾሙትም ሴኔጋል ሲሆን የአምባሳደርነት ስልጣናቸውም ሴኔጋልን ጨምሮ ማሊን፣ ኬፕ ቨርዴን፣ ጊኒ ቢሳውን፣ ጋምቢያን እና ጊኒን (እ.ኤ.አ 1989–1993) ያጠቃልል ነበር።

ቀጥሎም እ.ኤ.አ 1983–2002 በጅቡቲ የኢትዮጵያ አምባሳደርና በኢጋድ (IGAD) የኢትዮጵያ ተጠሪ ሆነው አገልግለዋል። እ.ኤ.አ ከ2002 ጀምሮ እስከ 2006 ድረሰ በፈረንሳይ (ሞሮኮን ጨምሮ) የኢትዮጵያ አምባሳደርና በዩኔስኮ (UNESCO) የኢትዮጵያ ተጠሪ ሆነው አገልግለዋል። እ.ኤ.አ. ከ2006 ጀምሮ እስከ 2009 ድረስ በአፍሪካ ህብረት (AU) እና በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (UNECA) የኢትዮጵያ ተጠሪ ሆነው ሀገራቸውን አገልግለዋል።

ከሀያ ዓመታት በላይ በተለያዩ ሀገራትና ዓለምአቀፋዊ ድርጅቶች የኢትዮጵያ አምባሳደርና ተጠሪ በመሆን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤትን ያገለገሉት አምባሳደር ሳህለወርቅ ዘውዴ እ.ኤ.አ በ2009 የተበባሩት መንግስታት ድርጅትን (ተመድ) በመቀላቀል የድርጅቱ በመካከለኛው አፍሪካ ሪፑብሊክ የተቀናጀ ሰላም ግንባታ መሪ (Head BINUCA) በመሆን ማገልገል ጀመሩ።

ይህ አገልግሎታቸውም ወደ ሚቀጥለው ኃላፊነት አሸጋግሯቸው እ.ኤ.አ በ2011 ዓም የዚያን ጊዜ የተመድ ጠቅላይ-ጸሀፊ ባን ኪ-ሙን አዲስ ለተቋቃመው በናይሮቢ የተመድ ጽህፈት ቤት (UNON) የመጀመሪያዋ ጠቅላይ-መሪ አድርገው ሾማቸው። በዚያም ለሰባት ዓመታት ካገለገሉ በኋላ እ.ኤ.አ በሰኔ ወር 2010 የአሁኑ የተመድ ጠቅላይ-ጸሀፊ አንቶንዮ ጉቴሬስ አምባሳደር ሳህለወርቅ ዘውዴን በተመድ ጠቅላይ-መሪ ስር (Under-Secretary-General) የአፍሪካ ህብረት ልዩ ተጠሪ (UN’s Special Representative to the AU) እና በአፍሪካ ህብረት ውስጥ የተመድ ጽህፈት ቤት ዋና ኃላፊ (Head of UNOAU) አድርገው ሾሟቸው፤ ፕሬዚዳንት እስከሆኑበት ቀን ድረስ በዚሁ ሹመታቸው እያገለገሉ ነበር።

አምባሳደር ሳህለወርቅ ዘውዴ፣ ባለትዳርና የሁለት ወንድ ልጆች እናት ናቸው።

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. gi Haile says

    October 27, 2018 06:38 pm at 6:38 pm

    የአንድ ታላቀሰ መሪ መለኪያዎች በየትኛውም የሥልጣን እርከን ይሁን ታመኝና ታታሪ ሰራተኛ ሆኖ መገኘትና የተሰጠውን ኃለፊነት በብቃት የሚወጣ ማለት ነው ። የአዲሱ ፕሬዝዳንት የመሪነት ልምድ ያካበቱት የተሰጣቸውን ኃለፊነት በብቃት መወጣት ነው። ኢትዮጵያ ብዙ ታማኝ መራዎች በዘመናት መካከል ነበሩኣት። እነዚህን መሪዎች ልናመሰግን እንወዳለን። በለፉት 27 አመት ውስጥ ደግሞ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ታይቶ የማይታወቅ ብልሹ መሪዎች የተፈጠሩበት ጊዜም ነው። ስለነዚህ ብልሹ መሪዎች ደገሰሞ በጣም እናዝናለን እናፈራለን። እንደ ፕሬዘዳንት ሳዕለወርቅ ዘውዴ ያሉ መሪዎች አገራችን በጣም ያስፈልጓታል። ኢትዮጵያ በመልካም ሕዝቦቿና መሪዎቿ ጋር ለዘለዓለም ትኑር ።

    Reply
  2. በለው ! says

    November 5, 2018 07:05 am at 7:05 am

    ጋዜጠኛ ለታሪክ ጀርባውን ሲሰጥ አስፈሪም አሳፋሪም ይሆናል!!!
    አቻምየለህ ታምሩ
    * አገራችን ከወይዘሮ ሣሕለ ወርቅ ዘውዴ በፊት ንግስተ-ነገስታት ዘውዲቱ ምኒልክ፣ ሕንደኬ፣ ማክዳና ዮዲት የሚባሉ ሴት ርዕሳነ ብሔራት ነበሯት!
    የኢትዮጵያን እድሜ ከወያኔ የአገዛዝ ዘመን ጀምረው የሚቆጥሩ እንደ BBC News Amharic አይነት ጋዜጠኞች ወይዘሮ ሣሕለ ወርቅ ዘውዴን የመጀመሪያዋ ሴት የኢትዮጵያ ርዕሰ ብሔር እያደረጓቸው ይገኛሉ። ከዛሬ 98 ዓመታት በፊት ወይዘሮ ሣሕለ ወርቅ ዘውዴ ዛሬ በገቡበት የኢትዮጵያ ቤተ መንግሥት ውስጥ የኢትዮጵያ መሪ ሆነው የገቡ ሌላ ሴት ርዕሰ ብሔር ነበሩ። ስማቸው ወይዘሮ ዘውዲቱ ምኒልክ ይባላል!

    * ወይዘሮ ሣሕለ ወርቅ ዘውዴን ርዕሰ ብሔር አድርጎ የሾመው ኦሮሞው ዐቢይ አሕመድ ነው።
    * ወይዘሮ ዘውዲቱ ምኒልክንም ርዕሰ ብሔር አድርገው የሾሟቸው የዘመኑ አንጋሽና የጦር መሪ የነበሩት ኦሮሞው ፊታውራሪ ኃብተ ጊዮርጊስ ዲኔግዴ (አባ መላ) ናቸው።
    ከወይዘሮ ዘውዲቱ ምኒልክ በፊት ሕንደኬ፣ ማክዳና ዮዲት የሚባሉ ሴት የኢትዮጵያ ርዕሳነ ብሔራት ነበሩ። ወይዘሮ ዘውዲቱ ምኒልክን ጨምሮ ከወይዘሮ ሣሕለ ወርቅ ዘውዴ በፊት የነበሩት የኢትዮጵያ ሴት ርዕሳነ ብሔራት ሁሉ በሥልጣን ረገድ ከዛሬዋ ርዕሰ ብሔር እጅግ የገዘፈ የሙሉ ሥልጣን ባለቤቶች ነበሩ።
    የዛሬዋ ርዕሰ ብሔር የፖለቲካ ሥልጣናቸው የይስሙላ ወይንም cermonial ነው። ከወይዘሮ ሣሕለ ወርቅ ዘውዴ በፊት የነበሩት የኢትዮጵያ ሴት ርዕሳነ ብሔራት ግን ዘውድ እየጫኑ የሚያነሱ፣ ሹም ሽር የሚያደርጉ፣ ጦር የሚያዝዙ፣ ብቸኛ የአገር መሪዎችና አባወራዎች ነበሩ! የዛሬዋ ርዕሰ ብሔር ወይዘሮ ሣሕለ ወርቅ ዘውዴ ግን ሌላው ቢቀር ከተሰጣቸው ሥልጣን መካከል ዋና የሆነው ሕግ የማጽደቅ ሥልጣን እንኳ ረቂቁ ቀርቦላቸው በ15 ቀናት ውስጥ ካልፈረሙት የርሳቸውን ይሁንታ ሳያገኝ ሕግ መሆን የሚችልበት ትርጉም የሌለው ሥልጣን ነው ያላቸው!
    F

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
Copyright © 2026 · Goolgule