• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ማዕረግ እንስጣቸው!

April 27, 2016 06:52 am by Editor 4 Comments

ሰው በሕይወት ሳለ መቼም ማድነቅ አንወድ

ማሻሻል አለብን ይሄን ነገር የግድ

እኚህ ጠንካራ ሰው ፕሮፌሠር መስፍን

ለራሳቸው ቢሆን የለፉት እስካሁን

ሀብት ከሥልጣን ጋር በእጃቸው ጨብጠው

በታዩ ነበረ ከሁሉ ሰው በልጠው

ነገር ግን እኚህ ሰው ለሀገር ሲለፉ

ምንም ሳይኖራቸው ዕድሜአቸውን ገፉmesfin-woldemariam

ሆኖም እንደሳቸው ከህሊናው አድሮ

መኖር ክብር አለው እየበሉ ሽሮ

ጥንትም ሆነ አሁን በተሳሳተ ሀገር

መቼም ድኖ አያውቅም አዋቂ ከችግር

ገዢን የማይፈሩት በዕድሜ ዘመናቸው

እኮ ለምንድነው ብለውም ቢሏችሁ

ህሊናው የጸዳ ያልፈጸመ በደል

እስከዛሬ ድረስ መቼ ፈርቶ ያውቃል

ብላችሁ መልሱ ይሄን ተናገሩ

ሌላ ምንም አይደል አትጠራጠሩ

እኚህን ታላቅ ሰው እንያዛቸው በወግ

በዕድሜ ዘመናቸው ክብርን አንንፈግ

የሳቸው ብቸኛ ህዝብ ነው ሿሚያቸው

ማዕረጋቸው ላይ ማዕረግ እንስጣቸው

******

ለፕሮፌሠር መስፍን ወልደማርያም 86ኛ የልደት በዓል መታሰቢያ የተጻፈ

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. eunetu says

    April 30, 2016 02:07 pm at 2:07 pm

    ወለላዬ እኔም ተስማምቻለሁ፤
    በጎ ሃሳብሽን እጋራለሁ፤
    ለእኒህ ሰው ጤናን እመኛለሁ፤
    የማያልፍ ሥራ ላገር ሲሠሩ አይቻለሁ፤
    አጨራረሳቸው እንዲያምር አጥብቄ እጸልያለሁ፤
    መሀሪው ጌታም ይሰማኛል ብዬ አምናለሁ፤
    በእውነት አሜን በይ እኔ ከልብ ብያለሁ።

    በዘመናቸው ለራሳቸው ያልኖሩ፤
    ላገር ለወገን ብቻ ሲጮሁ የኖሩ፤
    እንደ እኔ እንኳን ጎጆ ለመቀለስ ያልሞከሩ፤
    አቅቷቸው ሳይሆን ቅድሚያ በመስጠት ላገር ለምድሩ፤
    የከበረ ሰው ነኝ በል/ሉ በማለት ሁሉም ሲሮጥ ወደ ዘር ማንዘሩ፤
    ነው!ናቸው እንበል ዛሬ፣ ነገን ጠብቀን ከማለት ነበሩ፤
    ስለዚ ዛሬውኑ ተስማምተን መልካም ስም እናውጣላቸውና ይክበሩ፤
    ሰው የዘራውን ያጭዳል እንደሚል ቃሉ፤
    እኔ ግን ቀድሜ ብያቸዋለሁ፣
    ያለመጽሀፍ ቅዱስ ወንጌል ሰባኪ!!!

    እውነቱ ነኝ

    Reply
  2. koster says

    May 2, 2016 10:58 am at 10:58 am

    We should respect and appreciate all those who are voice for the voiceless Ethiopians when they are alive.

    Reply
  3. eunetu says

    May 2, 2016 05:35 pm at 5:35 pm

    Golgule?????

    I can not understand why you are waiting for my comment to post????

    Eunetu

    Reply
  4. ሸመልስይማም says

    May 17, 2016 02:07 pm at 2:07 pm

    ኢትዮጵያሀገሬምኝነሽተላላየምተልሽቀርቶየገደለሸበላ
    ተብላል::
    ሸመልስከደሴ

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
Copyright © 2026 · Goolgule