• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሮመዳን ዋዜማ እና ሮመዳን በሳውዲ

July 9, 2013 02:19 am by Editor Leave a Comment

እንኳንስ ለኔ ቢጤ አፍላ የጎልማሳነት እድሜውን በሳውዲ እየገፋ ላለ ላንድ ሰሞን ጉብኝት ሳውዲን የመጎብኘት እድልን ላገኘ የሮመዳን ወር የጾምና የጸሎት ወር ልዩና የማይረሳ ትዝታ ይቋጠርበታል፡፡ በሮመዳን ዋዜማ የገበያ ጥድፊያramadan 1 የተለመደ ነው፡፡ ጾሙን ለመያዝ የሚያስችሉ የምግብ ፍጆታና ቁሳቁሶችን ዋዜማ መገለጫ ሆኖ ከአመት አመት የሚስተናገድ ቀልብን ሳቢ ትዕይንት ነውና በዛሬው የማለዳ ወጋወጌ ስለ ሮመዳን ዋዜማ ከማውቀው ጥቂቱን ላካፍላችሁ ወድጃለሁ ! የፈቀዳችሁ ተከተሉኝ. . .

. . . ጾም ሲፈታ ለሚቀርበው የጾም መፍቻ ተምርና ጣፋጭ መጠጦች ጨምሮ የምግብ ማዕዱን ramadan 3ለማድመቅ ታላቅ ቅናሽን በሚያደርጉት ትላልቅ የገበያ አዳራሾች የሚደረገው ግብይት ደምቆ የሚስተዋለው በሮመዳን ዋዜማ ባሉት ጥቂት ቀናት ውስጥ ነው፡፡ ለአረቦች ነዳጅ ለሰጠ ፈጣሪ ምስጋና ይግባውና የዘመኑ ቴክኖሎጂ የወለዳቸው የተለያዩ የባውዛ መብራቶችና የሌዘርramadan 2 አንጸባራቂ ብርሃኖች አውራ መንገዶችንና የህዝብ መዝናኛ ቦታወችን የማድመቁ ሃላፊነት የሳውዲ መንግስት ሃላፊነቱን ሲወጣ የሚታየው የሮመዳንን በአል ለመቀበል ሽር ጉድ የሚባልበት አጋጣሚም ይህ የዋዜማ ወቅት ነው ! በሮመዳን ጂዳ እጹብ ድንቅ የሚታይባት ሙሽራ ናት ቢባል ማጋነን አይሆንም !

በሮመዳን ሰውም ቸር ነው ! . . . በየመንገዱ ሲያልፍ ሲያገድም ሰላም ሳይባባል አይተላለፍም፡፡ በተለይ በጾሙ ወቅት ለአንድየ ሰላምታ ” አውቀዋለሁ ፣ አላውቀውም” የሚባል ነገር አይሰራም፡፡ ፈገግ ብሎ በሰላምታ ከመጨባበጥ ባለፈ አብሮ እንዳደገ ትከሻ ለትከሻ ሰላምታ መለዋወጥ የተለመደ የሮመዳን ወር ልዩ ህበረ ቀለማዊ ውበት ነው፡፡ ቀን ላይ ሁሉም ምግብ ቤቶችና ሻሂ ቤቶች ዝግ ናቸው፡፡ ከረፋዱ ጀምሮ ቢሮዋቸውን የሚከፍቱት በአብዛኛው ከውጭ ኩባንያዎች ጋር ትሥሥር ያላቸው ጽህፈት ቤቶች ፤ ለሮመዳን ፍጆታ ምግብ መጠጥ ምኑ ምናምኑን የሚያቀርቡት ፋብሪካዎችና ከዚሁ ጋር ተዛማጅ እንቅስቃሴ የሚያደርጉ ሱቆች ብቻ ናቸው፡፡ ቀኑ ወደ ማታ የተቀየረ ይመስላል፡፡  ጾሙ ከተፈታ በኋላ ምሽት ላይ ምግብ ሲበላ እንደ ሃገራችን ሰው በቅርቡ ያለውን ይጋብዛል “ፈደል” ይሉታል ! “እባክህ እንብላ !” እንደ ማለት ነው፡፡ እንብላ ብሎ አንዱ አንዱን ሲሸማግል ማየት የተለመደ ነው !

ጅዳ በምትደምቅበት ወቅት በሮመዳን ሁሉም ነገር የሚሆነው ማታ ነው፡፡ ታዲያ ማታ ይህ ሁሉ ሲሆን ቀን ላይ ጥድፊያ አይታይም፡፡ አውላላውን ጥርጊያ መንገድ ሞልተው የሚርመሰመሱት ሚጢጢዎችም ሆኑ ትላልቅ የቅንጦት መኪኖችም አልፎ አልፎ ውር ውር ከማለት ባለፈ ብዙ አይታዩም፡፡ ከተማዋ የተወረረች ትመስላለች፡፡ ቀን ላይ ሃይማኖቱ ምንም ይሁን ምን እንደ ሲጋራውና እንደ ምግቡ ሁሉ ውሃ መጠጣት እንኳ አይፈቀድለትም፡፡ “መምኑእ” ነው ክልክል ! በሳውዲ ! በሮመዳን ጾም ዋዜማ የሚፈልገውን ሁሉ እቤቱ ከዋውኖ መውጣት ግድ ይላል ! የስሞኑ ናላን ሰብሮ የሚገባው የጅዳን ሃሩር ጸሃይና የቀይ ባህር ወበቅ አይጣል ነው! . . .ዛሬ በዋዜማው ያለሁት ከመካ 80 ኪሌ ሜትር የቅርብ ርቀት በምትገኘው በወደብ ከተማዋ በጅዳ ነው! አምና ይህን ሰአት ድግሞ ከልጆቸ ጋር የሮመዳንን ዋዜማ የመጨረሻ ቀን የተቀበልኳት ኮረብታማ እናramadan kareem ረባዳ በሆነችው ከተማ ጣይፍ ላይ ሆኘ መካን ቁልቁል እያየኋት ነው ! . . . በቀጣይ አመታት የት እንደምሆንም ብቻ ሳይሆነ እኖር አልኑር፣ የሚያውቀው አንድየ ብቻ ነው!

በዘንድሮው ሮመዳን ቅዱሳኑ መካና መዲና እንደለመዱት ከመላ አለም ለጸሎት የሚመጡ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ምእመናን ሙሉ በሙሉ አይስተናገድባቸውም ። ምክንያት አለው ፣ታላቁ የካእባ እና የመዲና ቅዱሳን ቦታዎችን ለማስፋፋት ፣ ከአመት እስከ አመት ተንቦርቅቆ ውሎ የሚያድረውን የበርሃ ሃሩር ወደ ኤሌትሪክ ሃይል ለመቀየር ፣ ትላልቅ ማረፊያ ሆቴሎች ለመገንባት እና ቅዱሳኑን ቦታዎች በፈጣን ዘመናዊ ባቡር ለማገናኘት በቢሊዮኖች የሚቆጠር መዋዕለ ንዋይ ተመድቧል። ከግንባታው ጋር መጨናነቅ እንዳይፈጠር የጸሎተኞች ቁጥር እንዲቀንስ መደረጉን የሳውዲ መንግስት አስታውቋል። በዚህ መሰረት ከሃገር ውስጥ የጸሎተኞች ኮታ በ50 እጅ የቀነሰ ሲሆን የውጭ ምዕመናን ኮታ በ20 እጅ እንዲቀንስ ተደርጓል ! ግንባታው ሲጠናቀቅም የመካና መዲና የቅዱስ ቦታዎች የማስተናገድ አቅም በእጥፍ ድርብ እንደሚጨምር በዋዜማው ያሰባሰብኳቸው መረጃዎች ለሮመዳኑ ዋዜማ የማለዳ ወጌ ግብአት ሆነውኛል!

እንኳን ለሮመዳን የጾምና የጸሎት ወር በሰላም አደረሳችሁ !

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule