• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሮመዳን ዋዜማ እና ሮመዳን በሳውዲ

July 9, 2013 02:19 am by Editor Leave a Comment

እንኳንስ ለኔ ቢጤ አፍላ የጎልማሳነት እድሜውን በሳውዲ እየገፋ ላለ ላንድ ሰሞን ጉብኝት ሳውዲን የመጎብኘት እድልን ላገኘ የሮመዳን ወር የጾምና የጸሎት ወር ልዩና የማይረሳ ትዝታ ይቋጠርበታል፡፡ በሮመዳን ዋዜማ የገበያ ጥድፊያramadan 1 የተለመደ ነው፡፡ ጾሙን ለመያዝ የሚያስችሉ የምግብ ፍጆታና ቁሳቁሶችን ዋዜማ መገለጫ ሆኖ ከአመት አመት የሚስተናገድ ቀልብን ሳቢ ትዕይንት ነውና በዛሬው የማለዳ ወጋወጌ ስለ ሮመዳን ዋዜማ ከማውቀው ጥቂቱን ላካፍላችሁ ወድጃለሁ ! የፈቀዳችሁ ተከተሉኝ. . .

. . . ጾም ሲፈታ ለሚቀርበው የጾም መፍቻ ተምርና ጣፋጭ መጠጦች ጨምሮ የምግብ ማዕዱን ramadan 3ለማድመቅ ታላቅ ቅናሽን በሚያደርጉት ትላልቅ የገበያ አዳራሾች የሚደረገው ግብይት ደምቆ የሚስተዋለው በሮመዳን ዋዜማ ባሉት ጥቂት ቀናት ውስጥ ነው፡፡ ለአረቦች ነዳጅ ለሰጠ ፈጣሪ ምስጋና ይግባውና የዘመኑ ቴክኖሎጂ የወለዳቸው የተለያዩ የባውዛ መብራቶችና የሌዘርramadan 2 አንጸባራቂ ብርሃኖች አውራ መንገዶችንና የህዝብ መዝናኛ ቦታወችን የማድመቁ ሃላፊነት የሳውዲ መንግስት ሃላፊነቱን ሲወጣ የሚታየው የሮመዳንን በአል ለመቀበል ሽር ጉድ የሚባልበት አጋጣሚም ይህ የዋዜማ ወቅት ነው ! በሮመዳን ጂዳ እጹብ ድንቅ የሚታይባት ሙሽራ ናት ቢባል ማጋነን አይሆንም !

በሮመዳን ሰውም ቸር ነው ! . . . በየመንገዱ ሲያልፍ ሲያገድም ሰላም ሳይባባል አይተላለፍም፡፡ በተለይ በጾሙ ወቅት ለአንድየ ሰላምታ ” አውቀዋለሁ ፣ አላውቀውም” የሚባል ነገር አይሰራም፡፡ ፈገግ ብሎ በሰላምታ ከመጨባበጥ ባለፈ አብሮ እንዳደገ ትከሻ ለትከሻ ሰላምታ መለዋወጥ የተለመደ የሮመዳን ወር ልዩ ህበረ ቀለማዊ ውበት ነው፡፡ ቀን ላይ ሁሉም ምግብ ቤቶችና ሻሂ ቤቶች ዝግ ናቸው፡፡ ከረፋዱ ጀምሮ ቢሮዋቸውን የሚከፍቱት በአብዛኛው ከውጭ ኩባንያዎች ጋር ትሥሥር ያላቸው ጽህፈት ቤቶች ፤ ለሮመዳን ፍጆታ ምግብ መጠጥ ምኑ ምናምኑን የሚያቀርቡት ፋብሪካዎችና ከዚሁ ጋር ተዛማጅ እንቅስቃሴ የሚያደርጉ ሱቆች ብቻ ናቸው፡፡ ቀኑ ወደ ማታ የተቀየረ ይመስላል፡፡  ጾሙ ከተፈታ በኋላ ምሽት ላይ ምግብ ሲበላ እንደ ሃገራችን ሰው በቅርቡ ያለውን ይጋብዛል “ፈደል” ይሉታል ! “እባክህ እንብላ !” እንደ ማለት ነው፡፡ እንብላ ብሎ አንዱ አንዱን ሲሸማግል ማየት የተለመደ ነው !

ጅዳ በምትደምቅበት ወቅት በሮመዳን ሁሉም ነገር የሚሆነው ማታ ነው፡፡ ታዲያ ማታ ይህ ሁሉ ሲሆን ቀን ላይ ጥድፊያ አይታይም፡፡ አውላላውን ጥርጊያ መንገድ ሞልተው የሚርመሰመሱት ሚጢጢዎችም ሆኑ ትላልቅ የቅንጦት መኪኖችም አልፎ አልፎ ውር ውር ከማለት ባለፈ ብዙ አይታዩም፡፡ ከተማዋ የተወረረች ትመስላለች፡፡ ቀን ላይ ሃይማኖቱ ምንም ይሁን ምን እንደ ሲጋራውና እንደ ምግቡ ሁሉ ውሃ መጠጣት እንኳ አይፈቀድለትም፡፡ “መምኑእ” ነው ክልክል ! በሳውዲ ! በሮመዳን ጾም ዋዜማ የሚፈልገውን ሁሉ እቤቱ ከዋውኖ መውጣት ግድ ይላል ! የስሞኑ ናላን ሰብሮ የሚገባው የጅዳን ሃሩር ጸሃይና የቀይ ባህር ወበቅ አይጣል ነው! . . .ዛሬ በዋዜማው ያለሁት ከመካ 80 ኪሌ ሜትር የቅርብ ርቀት በምትገኘው በወደብ ከተማዋ በጅዳ ነው! አምና ይህን ሰአት ድግሞ ከልጆቸ ጋር የሮመዳንን ዋዜማ የመጨረሻ ቀን የተቀበልኳት ኮረብታማ እናramadan kareem ረባዳ በሆነችው ከተማ ጣይፍ ላይ ሆኘ መካን ቁልቁል እያየኋት ነው ! . . . በቀጣይ አመታት የት እንደምሆንም ብቻ ሳይሆነ እኖር አልኑር፣ የሚያውቀው አንድየ ብቻ ነው!

በዘንድሮው ሮመዳን ቅዱሳኑ መካና መዲና እንደለመዱት ከመላ አለም ለጸሎት የሚመጡ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ምእመናን ሙሉ በሙሉ አይስተናገድባቸውም ። ምክንያት አለው ፣ታላቁ የካእባ እና የመዲና ቅዱሳን ቦታዎችን ለማስፋፋት ፣ ከአመት እስከ አመት ተንቦርቅቆ ውሎ የሚያድረውን የበርሃ ሃሩር ወደ ኤሌትሪክ ሃይል ለመቀየር ፣ ትላልቅ ማረፊያ ሆቴሎች ለመገንባት እና ቅዱሳኑን ቦታዎች በፈጣን ዘመናዊ ባቡር ለማገናኘት በቢሊዮኖች የሚቆጠር መዋዕለ ንዋይ ተመድቧል። ከግንባታው ጋር መጨናነቅ እንዳይፈጠር የጸሎተኞች ቁጥር እንዲቀንስ መደረጉን የሳውዲ መንግስት አስታውቋል። በዚህ መሰረት ከሃገር ውስጥ የጸሎተኞች ኮታ በ50 እጅ የቀነሰ ሲሆን የውጭ ምዕመናን ኮታ በ20 እጅ እንዲቀንስ ተደርጓል ! ግንባታው ሲጠናቀቅም የመካና መዲና የቅዱስ ቦታዎች የማስተናገድ አቅም በእጥፍ ድርብ እንደሚጨምር በዋዜማው ያሰባሰብኳቸው መረጃዎች ለሮመዳኑ ዋዜማ የማለዳ ወጌ ግብአት ሆነውኛል!

እንኳን ለሮመዳን የጾምና የጸሎት ወር በሰላም አደረሳችሁ !

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule