• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

80ኛው ዓመት የየካቲት 12 የሰማእታት ቀን ዝክረ-በዓል

March 24, 2017 05:20 am by Editor Leave a Comment

ጋዜጣዊ መግለጫ   

በ1929 ዓ/ም ፋሺሽት ኢጣልያ 30000 ኢትዮጵያውያንን በአዲስ አበባ ከተማ በሶስት ቀኖች ውስጥ የጨፈጨፈችበት 80ኛ የየካቲት 12 ቀን ዝክረ-በዓል በዓለም-አቀፍ ደረጃ ተከብሯል። እስካሁን ለድርጅታችን በደረሰው ዜና መሠረት፤ በዓሉ በአዲስ አበባ፤ በዳላስ፤ በአትላንታ፤ በማያሚ፤ በኒውዮርክ፤ በዋሺንግተን ዲ.ሲ.፤ በሮም፤ በኮሎኝ፤ በአውሮራ፤ በቫንኩቨር፤ በቶሮንቶ፤ በሲያትል፤ በፕሪቶሪያና በስቶክሆልም ተከብሯል። የአከባበሩም ዘዴ በአብዛኛው በጸሎት ሲሆን፤ እንደ ዳላስ፤ ኒውዮርክ፤ ፕሪቶሪያና ሮም ባሉ ከተሞች በጉባኤ፤ እንዲሁም በዋሺንግተን ዲ.ሲ. በሰላማዊ ሰልፍ ተከናውኗል።

ካጋጠሙት እጅግ የሚያበረታቱ ክስተቶች ውስጥ፤ ከፍ ያለ ምሥጋና የሚገባቸው የመገናኛ ብዙኃን ስለ ሰማእታቱ ቀን ሰፊ ግንዛቤ እንዲገኝ ያበረከቱት አስተዋጽኦ ነው። እነዚህም ቪ.ኦ.ኤ. ሬዲዮ፤ የጀርመን ሬዲዮ፤ ኢሳት፤ ሕበር ሬዲዮ፤ ኢ.ቢ.ኤስ (ርእዮት)፤ የዳላስ ኢትዮጵያ መረዳጃ ማሕበር ሬዲዮ፤ ማሕደረ ሬዲዮ፤ ጣና ሪዲዮ፤ እና ኤስ.ቢ.ኤስ (አውስትሬሊያ) ሬዲዮ ናቸው።

ከተገኙው መልካም ውጤቶች ውስጥ፤

(ሀ) ቫቲካን፤ ፋሺሽት ኢጣልያን ደግፋ ስለ ነበር፤ የኢትዮጵያን ሕዝብ ይቅርታ እንድትጠይቅ ከታች በተመለከተው ድረ-ገጻችን የሚገኘው አቤቱታ በ700 ተጨማሪ ሰዎች በላይ ተፈርሟል። ባሁኑ ጊዜ የፈራሚዎች ቁጥር 5600 ቢደርስም የሚፈለገው 100000 ስለሆነ ተጨማሪ ጥረት እንደሚያስፈልግ ግልጽ ነው።

ፎቶ: ከግራ ወደቀኝ አቶ ጣሰው መልዓከህይወት፣ አቶ ከባዱ በላቸው እና ጠበቃ ፍጹም አቻምየለህ አለሙ

(ለ) በኢጣልያ፤ ሮም ከተማ በተከናወነው፤ በአብዛኛው ኢጣልያኖችና ጥቂት ኢትዮጵያውያን በተገኙበት ጉባኤ፤ ውይይቱ ያተኮረው በኢትዮጵያ ላይ ተፈጽሞ ለነበረው የጦር ወንጀል ተጠያቂ የነበሩ ፋሺሽቶች የጀርመን ተጠያቂዎች ነረምበርግ  (Nuremburg) በተሰኘው የፍትሕ ሥርዓት እንደ ተከሰሱ ወንጀል ፈጻሚ የነበሩ ኢጣልያኖችም ለፍትሕ መቅረብ እንደነበረባቸው ሐሳቦች በመለዋወጥ ነበር።

(ሐ) ሮም በተከናወነው ጉባኤ የተነሳው ሌላው አርእስት “የኢትዮጵያ ጨፍጫፊ” በመባል ለሚታወቀው ለሮዶልፎ ግራዚያኒ፤ የቫቲካን ተወካይ በተገኙበት፤ እ.አ.አ. በነሐሴ 2012 ስለ ተመረቀለት መታሰቢያና መናፈሻ ነበር። አፊሌ በምትባል የኢጣልያ ከተማ የሚገኘው መታሰቢያ እንዲወገድና ለጉዳዩም ተጠያቂ የሆኑት የከተማው ከንቲባ እና ምክትል ከንቲባ የእስር ፍርድ ተበይኖባቸው ጉዳዩ በይግባኝ በመታየት ላይ ቢሆንም ሮም የሚገኙ የኢትዮጵያ ወዳጆች በቅርብ እየተከታተሉት ነው።

ፋሺሽት ኢጣልያ በኢትዮጵያ ላይ ለፈጸመችው እጅግ ከባድ የጦር ወንጀል፤ አንድ ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን በመጨፍጨፋቸው፤ 2000 ቤተ ክርስቲያኖች፤ 525000 ቤቶችና 14 ሚሊዮን እንስሶች በመውደማቸውና ብዙ ንብረት በመዘረፉ እንዲሁም ቫቲካን ለፋሺሽቶቹ ስለ ፈጸመችው ድጋፍ፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ ይቅርታ እንዲጠየቅና ተገቢው ካሣ እንዲከፈለው፤ ድርጅታችን ጥረቱን እየቀጠለ ነው፡፡

ቸሩ የኢትዮጵያ አምላክ ለውድ ሐገራችን የሚገባውን ፍትሕ እንድናስገኝ ይርዳን።

ዓለምአቀፍሕብረትለፍትሕ – የኢትዮጵያጉዳይ

4002 Blacksmith Drive, Garland, TX 75044; Tel: (214)703 9022

www.globalallianceforethiopia.org; E-mail: info@globalallianceforethiopia.com

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am
  • የኦነግ ሸኔ አባላትን ዕድሜ ለማሳጠር የጂፒኤስ ቴክኖሎጂ ጥቅም ላይ እየዋለ ነው December 7, 2020 12:38 am
  • የቆሰሉ ወታደሮች በጠቅላይ ሚኒስትሩ ተጎበኙ December 6, 2020 11:41 pm
  • “ከዚህ በኋላ ይዘን እንታገላለን እንጂ ሠጥተን አንጠይቅም” ኮሎኔል ደመቀ December 2, 2020 12:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule