• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

80ኛው ዓመት የየካቲት 12 የሰማእታት ቀን ዝክረ-በዓል

March 24, 2017 05:20 am by Editor Leave a Comment

ጋዜጣዊ መግለጫ   

በ1929 ዓ/ም ፋሺሽት ኢጣልያ 30000 ኢትዮጵያውያንን በአዲስ አበባ ከተማ በሶስት ቀኖች ውስጥ የጨፈጨፈችበት 80ኛ የየካቲት 12 ቀን ዝክረ-በዓል በዓለም-አቀፍ ደረጃ ተከብሯል። እስካሁን ለድርጅታችን በደረሰው ዜና መሠረት፤ በዓሉ በአዲስ አበባ፤ በዳላስ፤ በአትላንታ፤ በማያሚ፤ በኒውዮርክ፤ በዋሺንግተን ዲ.ሲ.፤ በሮም፤ በኮሎኝ፤ በአውሮራ፤ በቫንኩቨር፤ በቶሮንቶ፤ በሲያትል፤ በፕሪቶሪያና በስቶክሆልም ተከብሯል። የአከባበሩም ዘዴ በአብዛኛው በጸሎት ሲሆን፤ እንደ ዳላስ፤ ኒውዮርክ፤ ፕሪቶሪያና ሮም ባሉ ከተሞች በጉባኤ፤ እንዲሁም በዋሺንግተን ዲ.ሲ. በሰላማዊ ሰልፍ ተከናውኗል።

ካጋጠሙት እጅግ የሚያበረታቱ ክስተቶች ውስጥ፤ ከፍ ያለ ምሥጋና የሚገባቸው የመገናኛ ብዙኃን ስለ ሰማእታቱ ቀን ሰፊ ግንዛቤ እንዲገኝ ያበረከቱት አስተዋጽኦ ነው። እነዚህም ቪ.ኦ.ኤ. ሬዲዮ፤ የጀርመን ሬዲዮ፤ ኢሳት፤ ሕበር ሬዲዮ፤ ኢ.ቢ.ኤስ (ርእዮት)፤ የዳላስ ኢትዮጵያ መረዳጃ ማሕበር ሬዲዮ፤ ማሕደረ ሬዲዮ፤ ጣና ሪዲዮ፤ እና ኤስ.ቢ.ኤስ (አውስትሬሊያ) ሬዲዮ ናቸው።

ከተገኙው መልካም ውጤቶች ውስጥ፤

(ሀ) ቫቲካን፤ ፋሺሽት ኢጣልያን ደግፋ ስለ ነበር፤ የኢትዮጵያን ሕዝብ ይቅርታ እንድትጠይቅ ከታች በተመለከተው ድረ-ገጻችን የሚገኘው አቤቱታ በ700 ተጨማሪ ሰዎች በላይ ተፈርሟል። ባሁኑ ጊዜ የፈራሚዎች ቁጥር 5600 ቢደርስም የሚፈለገው 100000 ስለሆነ ተጨማሪ ጥረት እንደሚያስፈልግ ግልጽ ነው።

ፎቶ: ከግራ ወደቀኝ አቶ ጣሰው መልዓከህይወት፣ አቶ ከባዱ በላቸው እና ጠበቃ ፍጹም አቻምየለህ አለሙ

(ለ) በኢጣልያ፤ ሮም ከተማ በተከናወነው፤ በአብዛኛው ኢጣልያኖችና ጥቂት ኢትዮጵያውያን በተገኙበት ጉባኤ፤ ውይይቱ ያተኮረው በኢትዮጵያ ላይ ተፈጽሞ ለነበረው የጦር ወንጀል ተጠያቂ የነበሩ ፋሺሽቶች የጀርመን ተጠያቂዎች ነረምበርግ  (Nuremburg) በተሰኘው የፍትሕ ሥርዓት እንደ ተከሰሱ ወንጀል ፈጻሚ የነበሩ ኢጣልያኖችም ለፍትሕ መቅረብ እንደነበረባቸው ሐሳቦች በመለዋወጥ ነበር።

(ሐ) ሮም በተከናወነው ጉባኤ የተነሳው ሌላው አርእስት “የኢትዮጵያ ጨፍጫፊ” በመባል ለሚታወቀው ለሮዶልፎ ግራዚያኒ፤ የቫቲካን ተወካይ በተገኙበት፤ እ.አ.አ. በነሐሴ 2012 ስለ ተመረቀለት መታሰቢያና መናፈሻ ነበር። አፊሌ በምትባል የኢጣልያ ከተማ የሚገኘው መታሰቢያ እንዲወገድና ለጉዳዩም ተጠያቂ የሆኑት የከተማው ከንቲባ እና ምክትል ከንቲባ የእስር ፍርድ ተበይኖባቸው ጉዳዩ በይግባኝ በመታየት ላይ ቢሆንም ሮም የሚገኙ የኢትዮጵያ ወዳጆች በቅርብ እየተከታተሉት ነው።

ፋሺሽት ኢጣልያ በኢትዮጵያ ላይ ለፈጸመችው እጅግ ከባድ የጦር ወንጀል፤ አንድ ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን በመጨፍጨፋቸው፤ 2000 ቤተ ክርስቲያኖች፤ 525000 ቤቶችና 14 ሚሊዮን እንስሶች በመውደማቸውና ብዙ ንብረት በመዘረፉ እንዲሁም ቫቲካን ለፋሺሽቶቹ ስለ ፈጸመችው ድጋፍ፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ ይቅርታ እንዲጠየቅና ተገቢው ካሣ እንዲከፈለው፤ ድርጅታችን ጥረቱን እየቀጠለ ነው፡፡

ቸሩ የኢትዮጵያ አምላክ ለውድ ሐገራችን የሚገባውን ፍትሕ እንድናስገኝ ይርዳን።

ዓለምአቀፍሕብረትለፍትሕ – የኢትዮጵያጉዳይ

4002 Blacksmith Drive, Garland, TX 75044; Tel: (214)703 9022

www.globalallianceforethiopia.org; E-mail: info@globalallianceforethiopia.com

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule