• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኃይለማርያም ከየት ይለቃል? ያልነበረ “ፓርላማ” ወዴት ይበተናል?

December 27, 2017 04:23 pm by Editor 2 Comments

ከወራት በፊት የመልቀቂያ ደብዳቤ ያስገባውን አባዱላ ገመዳ የኢህአዴግ ሥራአስፈጻሚ ጥያቄውን አጽድቆለታል ተብሏል። ከዚህ ጋር ተከትሎ በቀጣይ ኃይለማርያም ከ“ሥልጣን” ይወርዳል የሚለው ጉዳይ በስፋት በሁሉም ዓይነት ሚዲያ እየተስተጋባ ነው።

በተያያዘ ወሬ አዲስ አበባ ላይ ያለውና ሰሞኑን በመጠኑ ሥራውን መሥራት የጀመረውን “ፓርላማ” ህወሓት ሊበትነው እያቀደ ነው የሚል መረጃ ተሰምቷል። ከዚህ በተጨማሪም ከትግራይና ሌሎች ታማኝ ክልል/ሎች በስተቀር በክልል የሚገኙ ምክርቤቶችን በሙሉ ህወሓት ሊበትናቸው አሢሯል የሚል መረጃ ባለፉት ጥቂት ቀናት ውስጥ እየተሰማ ነው።

ከገቢ አንጻር የሰበር ዜና ልክፍት የተጠናወተው ሚዲያ ይህ መሰሉን “መረጃ” ሲያስተላልፍ ከመረጃው ጋር ሕዝብ ማወቅ ያለበት ምንድነው የሚለውን ኃላፊነት የዘነጋው ይመስላል። ኃይለማርያም ደሳለኝ በሟቹ መለስ ተመልምሎ ወደ ሥልጣን መንበር ከቀረበ በኋላ በመለሳዊነት ለመጠመቅ እየተማረ ባለበት ጊዜ ነው “መምህሩ”ን ሞት የቀደመው። መጽሐፉ ተከፍቶ፣ የተጀመረው ምዕራፍ ሳይጠናቀቅ መለስ በማምለጡ ኃይለማርያም እዚያው የተከፈተ ገጽ ላይ ነው ያለው። ለዚህም ይመስላል እንደ ሃይማኖተኛነቱ ለፈጣሪው ዘላለማዊ ክብር መስጠት ሲገባው ለመለስ “ዘላለማዊ ክብር” ሲሰጥ እስካሁን የቆየው።

“ግምገማ!” በተባለው ኢህአዴግ በሚያካሂደው የስድብ ሃይማኖት፤ በተደጋጋሚ ከመስመር የወጡ ከፍተኛ የንቀት ንግግሮች ሲሰነዘሩበት የኖረው ኃይለማርያም ከሁለት ዓመት በፊት በተካሄደው ግምገማ፤ “ብቃት የለህም” ተብሎ አሁን በዝግ እየተካሄደ ባለ ዓይነት ስብሰባ ላይ ተሰድቧል። እርሱም በምላሹ፤ መጽሐፍ ማንበብ አልወድም፤ ዕቅድ ማዘጋጀት አልችልበትም፤ ለውጥ ማድረግ ያቅተኛል፤ … በማለት ውንጀላውን አምኗል።

በዚህ ዓይነት የውርደት ህይወት የሌለውን ሥልጣን ይዞ የቆየ ሰው ከሌለው ሥልጣን ላይ ይወርዳል ብሎ በዘገባነት ማጠናቀር ህወሓትን እንደ ኅብረብሔራዊ ድርጅት ቆጥሮ ሥልጣኑን በሐቅ አጋርቷ ብሎ ከማመን ተለይቶ የሚታይ አይደለም። ህወሓት ኃይለማርያምን ለማንሳት ቢሞክር ወይም ቢያስነሳው አሁን ባለው የፖለቲካ ሂደት ላይ የሚያመጣው ፋይዳ የበረታ አይመስለንም። ምናልባት በደኢህዴን ውስጥ ያለው ተገዢነት በተለይ የኃይለማርያም “መዘምራን” ላይ መጠነኛ ለውጥ ሊያመጣ ይችል ይሆናል። ኃይለማርያም ገና ከጅምሩ አገሪቱ (እንደ ማኅበር) በኅበረት አስተዳደር (“ኮሌክቲቭ ሊደርሺፕ”) ትመራለች በማለት ጠ/ሚሩ ይዞት የነበረውን ሥልጣን ሁሉ በክላስተር ሸንሽኖ ራሱን ሥልጣን አልባ አድርጎ የተቀመጠ ነው። አሁን ከሌለው ሥልጣን ሊወርድ የሚችልበት ምክንያት አይታየንም።

ሥልጣን አልባው “ፓርላማ”ም ሆነ የክልል ምክርቤቶች የተባሉት ከሌላቸው የሕዝብ ተወካይነትም ሆነ “ሥልጣን” በህወሓት ይበተናሉ ማለት በፊት ህወሓት በአሳታፊ ፖለቲካ ያምናል፤ የሕዝብ ውክልና በህወሓት የአገዛዝ ዘመን ነበር ብሎ ካድሬያዊ ዲስኩር ከመስጠት የተለየ አይሆንም። አተነፋፈሱ ብቻ ሳይሆን ሳንባውም በህወሓት የተገጠመለት “ፓርላማ” ሰሞኑን መጠነኛ ጥያቄዎች ሲያቀርብ በመሰማቱ “ሰበር ዜና” መሆኑ ምን ያህል ነው ቁልቁል የወረድነው ብለን ራሳችንን እንድንጠይቅ የሚያስገድድ ነው እንላለን። ሚዲያው እዚህ ላይ ቆም ብሎ ራሱን ወሬ ተኮር ነኝ፣ “ክሊክ” ተኮር ነኝ ወይስ አጀንዳ ተኮር ነኝ ብሎ እንዲጠይቅ ሳንጠቁም አናልፍም።

ስለዚህ የሚናገረው፣ የሚወስነው፣ የሚያስበው እየተመጠነ፣ እየተሰፈረ ሲሰጠው የነበረው ኃይለማርያም “ከሥልጣን ይወርዳል” ማለት ህወሓትን ዴሞክራሲያዊ ማድረግ ይመስለናል። ከሌሎች አገራት ፓርላማዎች ጋር በእኩል ስያሜ የመጠራት ብቃት የሌለው የኢህአዴግ ሸንጎ (ፓርላማ) እና የክልል ምክርቤቶች ይበተናል (“ዲዞልቭ” ይደረጋል) ማለት እንደ አገር የሌለንን አለን በማለት ለህወሓት/ኢህአዴግ ክብር መስጠት ነው።

ሕዝባዊው እንቅስቃሴ የህወሓት አፈና፣ ጥርነፋ አልበግረው ብሎ እዚህ ደርሷል። ከዚህ በፊት እንደዘገብነው የህወሓት የገጠር መዋቅር ፈርሷል፤ ትውልድ አምጿል፤ በቃኝ ብሏል። ከዚህ በኋላ በድጋሚ የሚወጣ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አይሠራም። በጥልቅ መታደስ ያመጣው “ውጤት” በጥልቀት መበስበስ ነው። ከዚህ በኋላ ኃይለማርያም ከሌለው ሥልጣን ቢወርድ፣ “ፓርላማ”ው ቢበተን የሚያመጣው ፋይዳ የለም። ስለዚህ ሚዲያው ከክሊክ ተኮርነት ወጣ ብሎ ከስሜትና ከምናባዊ አስተሳሰቡ ነቅቶ አጀንዳ የማስያዝ ሥራ ላይ ቢጠመድ ለአገር የሚበጅ ይመስለናል። ሕዝብ በቃኝ ብሏል፤ ትውልድ አምጿል!


ይህ ርዕሰ አንቀጽ የ“ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ™” አቋም ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Editorial Tagged With: dissolve, eprdf, Full Width Top, hailemariam, meles, Middle Column, paliament, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Abegaz says

    December 29, 2017 01:23 am at 1:23 am

    This is simplistic analysis. If Hailemariam is removed, there is a chance for people from the OPDO or ANDM to come to premiership and this is a positive step. Hailemariam staying in power and not doing his job by itself is bad. He will be considered as a willing collaborator and that allows TPLF to do things the way they want. So removing him is a big step forward. Likewise the parliament has a lot of power. What is left is courage. The continued protest by the Ethiopian people is a big energy for parliament to do its job. Again it is flimsy reasoning to suggest that parliament cannot do anything positive. Let us not get confused and confuse the public. This is not a worthy article.

    Reply
    • Ali says

      January 3, 2018 06:17 am at 6:17 am

      Abegaz,
      This comment of yours doesn’t seem a genuine and honest by its very “camouflaging” nature. You know, I can guess who you wanted to pretend to look like; at the same time, I do not want to speculate who you could be or any other with out having any proof. What you are missing here, my friend, is that it is NOT whether what you and me are commenting and suggesting here; its what we the 100 million Ethiopians who are experiencing the day to day death, suffering, hunger, hopelessness that matters most. Are you not seeing that people are still, as we speak, revolting? There is a limit to any kind of suffering that a human being can shoulder. Be fair and try to remotely feel the pain of the Ethiopian people!

      Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule