• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኦብነግና ኢህአዴግ ንግግር አቆሙ!

October 19, 2012 12:52 am by Editor 2 Comments

የኦጋዴን ብሄራዊ ነጻ አወጪ ግንባር /ኦብነግ/ እና ኢህአዴግ ጀምረው የነበሩት ድርድር መጨናገፉ ታወቀ። ድርድሩ የተጨናገፈው በኢህአዴግ በኩል በቀረበ ቅድመ ሁኔታ መሆኑ ተገልጿል። መግለጫው ለሁለት ተከታታይ ቀናት ስለተደረገው ንግግር በዝርዝር ሳያብራራ ህዝበ ውሳኔን በመፍትሄነት አስቀምጧል። 74 ንጹሃንን የገደሉት የኦብነግ ሰዎች ጉዳይ በድርድሩ ስለመካተቱ እስካሁን የተገለጸ ነገር የለም።

ኦብነግ በድረገጹ ኦክቶበር 17 ቀን 2012 በይፋ እንዳስታወቀው የሰላም ድርድሩ የተጀመረው የኢትዮጵያ መንግሥት ለኬኒያ መንግስት ባቀረበው የአሸማግሉኝ ጥያቄ መሰረት ነበር። በዚሁ ጥያቄ መሰረት የኬንያ መንግስት አሸማጋዮች ለግንባሩ አመራሮች ጥያቄውን አቅርቦ ቀና ምላሽ በማግኘቱ የመጀመሪያ ደረጃ ንግግር ተደርጎ ነበር።

የግንባሩ አመራሮች በቀናነት የድርድር ሃሳቡን ተቀብለው እንደነበር ያስታወቀው መግለጫ የመጀመሪያው ንግግር በድርድሩ መርህ፣ ቅርጽና አጠቃላይ የመደራደሪያ አጀንዳዎች ዙሪያ መግባባት ላይ ተደርሶ እንደነበር አስታውሷል። በዚሁ መነሻ ኦክቶበር 15 እስከ 17 በተደረገው ሁለተኛ ንግግር ላይ ቀደም ሲል ያለአንዳች ቅድመ ሁኔታ ለማካሄድ የተደረሰውን ስምምነት ኢህአዴግ ጥሶታል።

በመከላከያ ሚኒስትሩ አቶ ሲራጅ ፈጌሳ የሚመራው የኢትዮጵያ ልዑካን “ኦብነግ በቅድሚያ ህገ መንግስቱን መቀበል አለበት” በማለት ቅድመ ሁኔታ ማስቀመጡ በመግለጫው ተወስቷል። ድርድር ለማካሄድ ያመች ዘንድ በተደረገው የመጀመሪያ ንግግር ሁለቱም ወገኖች ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ የሰላም ድርድሩን የሚያሰናክሉ ጉዳዮችን ወደ ጎን በመተው ለመነጋገር ተስማምተው ሳለ ከኢትዮጵያ ወገን በቀረበ አስገዳጅ ቅድመ ሁኔታ ሳቢያ የሰላም ድርድር ለማካሄድ የተጀመረው ጥረት መቋረጡን አስታውቋል። በማያያዝም አቋሙን ይፋ አድርጓል። ግምባሩ በጥቅል በቀረበለት ቅድመ ሁኔታ ሳቢያ የሰላም ድርድሩን መጨናገፍ ሲያስታውቅ ሰነድ ሰንቆ ማሰረጃ አደራጅቶ ለሁለት ቀናት በናይሮቢ ስለተካሄደው ድርድር ዝርዝር ጉዳይ ዝምታን መምረጡ ለድርድሩ መቋረጥ ተጨማሪ ምክንያቶች እንዳሉ አመላካች ነው ተብሏል።

“በእኛ እምነት” ሲል የግንባሩን አቋም ያስታወቀው መግለጫው በኦብነግ እምነት በኦጋዴን ውስጥ ያለው ግጭት መፍትሄ ሊያገኝ የሚችለው የክልሉ ህዝብ ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታና ገደብ የራስን ዕድል በራስ የመወሰን መብታቸውን እንዲጠቀሙ ሲደረግ ብቻ ነው። ግንባሩ በዚህ መሰረታዊ እምነቱ ሳቢያ ለድርድር የቀረበለትን አስገዳጅ ቅድመ ሁኔታ አለመቀበሉን ይፋ አድርጓል። በመጀመሪያው ንግግር መሰረት ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ የሰላም ድርድሩ ቢቀጥል ፈቃደኛ እንደሆነም አስታውቋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ኦክቶበር 17 ቀን 2012 ኦብነግ ድርድሩ መጨናገፉን ይፋ ሲያደርግ አዲሱ ጠ/ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ ለተወካዮች ምክር ቤት ስም ሳይጠቅሱ ከተለያዩ ድርጅቶች ጋር ድርድር በመደረግ ላይ መሆኑን ተናግረዋል። በማብራሪያቸው ተቃዋሚዎችን ያወገዙት አቶ ሃይለማርያም መንግስታቸው ለመቻቻልና ለሰላም ያለውን ቁርጠኛነት ባስታወቁበት የንግግራቸው ክፍል ከቶውንም የማይደራደሯቸው ክፍሎች እንዳሉ አስታውቀዋል። እርስ በርሱ በሚጋጨው ገለጻቸው ስለ ሰላምና ስለ ኃይል እርምጃ አይቀሬነት ከማስጠንቀቂያ ጋር መልዕክት ያስተላለፉት ጠ/ሚኒስትሩ በተለይ ስለ ኦብነግ በስም ጠቅሰው የተናገሩት ነገር የለም።

በኦጋዴን፣ ከደገሃቡር 19 ኪ/ሜትር ርቀት ላይ በሚገኘው ኢቦሌ የነዳጅ ፍለጋ ስራ ላይ በተሰማሩ 68 የኢትዮጵያ፣ 9 የቻይና ዜጎች ላይ አፕሪል 24/2007 በድንገት ለደረሰው ጭፍጨፋ ኦብነግ ሃላፊነቱን መውሰዱ አይዘነጋም። በ74ቱ ያልታጠቁ ሲቪል ሰራተኞች ላይ የተፈጸመውን አሰቃቂ ግድያ ተከትሎ በተደረገ አሰሳ መንግስት ወንጀሉን በዋናነት በማስተባበር ፈጽመዋል ያላቸውን ዘጠኝ ሰዎች በቁጥጥር ስር በማዋል በሶማሌ ክልል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ክስ መስርቶ በሞት ፍርድ እንዲቀጡ መወሰኑም አይዘነጋም። ይሁንና ኢህአዴግ ከሁለት ዓመት ተኩል በፊት ከኦጋዴን ነጻ አውጪ ግንባር አንድ ክንፍ ጋር ሰላም ማውረዱን ይፋ ባደረገበት ወቅት አቶ አባይ ጸሃዬ በሸራተን አዲስ መግለጫ ሲሰጡ “ … በስምምነቱ መሰረት የታሰሩና በህግ ለሚጠየቁ ምህረት ይደረጋል። የሚታየው የወደፊቱ ዘለቄታዊ ሰላም ነው” በማለት ሞት የተፈረደባቸው በድርድሩ አስገዳጅነት እንደሚፈቱ አስታውቀው ነበር። የሞት ፍርድ የተፈረደባቸው ፍርደኞች ከሶማሌ ክልል ወህኒ ቤት ወደ ዝዋይ ተዛውረው፣ ቤተሰቦቻቸውም ዝዋይ ከተማ ቤት ተከራይተው እየጎበኟቸው መሆኑን ከጎልጉል የኦሮሚያ ፖሊስ ምንጮች ገለጻ ለመረዳት ተችሏል።

ፍርደኞቹ ዝዋይ ማረሚያ ቤት ጨለማ ክፍል ውስጥ በልዩ ጥበቃ ለተወሰነ ጊዜ ከኖሩ በኋላ ቤተሰቦቻቸውን የሚያነጋግሩበት የተለየ ኮሪደር ተዘጋጅቶላቸው ከሁሉም በተሻለ ቤት ውስጥ እንዲኖሩ መደረጉን የዓይን ምስክሮች ይናገራሉ። አዲስ ተጀምሮ የተሰናከለው ድርድር እነሱን ስለማካተቱ እስካሁን ከኦብነግ በኩል የተባለ ነገር የለም። ከመንግስት ጋር ስምምነት ላይ የደረሱትን ክፍሎች አስመልክቶ ኦብነግ ውስን ወታደር ያላቸው አነስተኛ አፈንጋጮች በሚል ግንባሩን እንደማይወክሉ በተደጋጋሚ መግለጹ አይዘነጋም።

ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. serbedin says

    October 23, 2012 10:01 am at 10:01 am

    it is sad news to learn about Ethiopia and this TPLF news specially about democracy those who started their struggle for independence it is real Story OGADEN is not the part of Ethiopia and Ethiopia is the christian part of the LAND that is our last choice our unity never brings democracy it brings domination against Islam and Muslims only so we have to struggle for our freedom until l the drop of our blood we considered as part of Ethiopian Somali but things are different on the ground so from today i will go to my motherland OGHADEN and fight for our independence as our constitution article 39 allows us to go for secession alhamdulillah we don’t need wuyyane at all if this government change only we can negotiate about living together

    Reply
    • Christian says

      October 24, 2012 07:32 am at 7:32 am

      You serbedin u’r the only idiot person among the ogaden people

      Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule