• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የወያኔ ሴራና ግፍ ለማን አቤት እንበል??

November 15, 2013 10:33 am by Editor 1 Comment

ኢትዮጵያውያን ብዙ ጮኽን ያዳመጠን ግን የለም፡ ፡ ለሰው ጩኽን፤ ለፈጣሪ ጩኽን፤ ለመሬትም ጮህን፤ አንዳች ምላሽ በመሻት፤ ጩኽታችን ግን ለሠማይና ለምድርም ጮህን፤ ጩኸታችን ግን የቁራ ጩኽት ሆኖ ቀረ፡፡ የተፈረደብን የመከራ ዘመን ከማለቅ ወይ ከመገባደድ ይልቅ እየጨመረ ሄደ፡፡

በግልፅ የሚታየውን ችግራችንን፣ ከፊታችን ሳይቀር የሚነበበው ጉስቁልናችን፣ ሚሊዮኖችን ምርኮኝ ያደረገ ርሃባችን፣ ፀሐይ የሞቀው የርስበርስ ፍጅታችንን ደመናን ቀርቶ የጎጇችንን ጣሪያ ማለፍ የተሳነው ምህላና ፀሎታችን ብዙዎች በየቀኑ ሽቅብ የምንረጨው እንባችን፤ ሁሉም በማንም ዘንድ ተሰሚነት አላገኘም፡፡ አሁንም ለቅሶና ዋይታችን ተባብሶ እንደቀጠለ ነው ሲባል።አሁንማ ማን የማይጮህ አለ? ሁሉንም የሚያስጮኸው ግን አንድ ነገር ነው፣የወያኔ ግፍ።

ክርስትያኑ ይጮሃል
ሙስሊሙም ይጮሃል
የመንግስትሰራተኛ ይጮሃል
የግልተቀጣሪ ይጮሃል
ቀጣሪው ይጮሃል
ስራ እጡ ይጮሃል
ነጋዴው ይጮሃል
ሸማቹ ይጮሃል
ሰራዊቱ ይጮሃል
ጋዜጠኛው ይጮሃል
እምነት የሌለው ይጮሃል
የጠገበው ይጮሃል
የራበው ይጮሃል
ይጮሃል ይጮሃል
ፖለቲከኛው ይጮሃል
ፍትህ ያጣው ይጮሃል
እስረኛው ይጮሃል
ታሪክ ይጮሃል
ሰሚአልባ ይጮሃል
 እራሱ ጩኸት ይጮሃል
እሪ በከንቱ

ተንኮለኞች ያጠመዱትን ወጥመድ የደገሱልን መከራና የሰቆቃ ድግስ ከዘመናት በፊት በሴራ መክረው ያወጁብን የጥፋት ዘመን በብሄርና በጎሳ ከፋፍለው የኢትዮጵያን አንድነት ለመነጣጠል በመካከላችን የከተቱብን የተኩላ መንጋ ሁሉም እንዳሰቡት ሆኖ ትንቢታቸው ሲይዝላቸውና ምኞታቸው ሲሳካላቸው በስቃያችን ይደሰታሉ፡፡ በቁስላችን የጋለ ብረት እየሰደዱ ለቅሷችንን እንደ ጥጋብ፣ ጭንቀት ጥበታችንን እንደ ደስታ፣ ጦርነታችንን እንደ መዝናኛ፣ መባዘናችንን እንደ በረከት፣ የርስ በርስ እልቂታችንን እንደሰላም በመቁጠር ያላግጡብናል፡፡ እውነቱን የማያውቁ ይመስል የላኳቸውን እንደራሴዎች የሚሰሩትን የማይረዱ ይመስል፡፡ የእኛን መከራና ችግር እንደማያውቁ ሆነው በመቆለል በጣት የሚቆጠሩ የተሻለ ኑሮ የሚኖሩ በገጠር በግብርና የሚተዳደሩትን ከተማ ያሉ ሃብታችን በመመልከት ብቻ ጥሩ ኑሮ ላይ ነን ይላሉ፡፡ እነዚያም ተቀብለው “ይኽ መቸ አነሳችሁ፤ ጥሩ ኑሮ እየኖራችሁ ነው” በማለት ይሳለቁብናል፡፡

ጥቂት የምትባል የመናገር፣ የመፃፍ ግድብ (ዴሞክራሲ) መብት በማየት ብቻ ዴሞክራሲያችን እዚህ ደርሷል በማለት አዎንታዊ አብነት ወስደው ከእኛ አልፈው ለሌሎች አገሮች ማስተማሪያ ሊሆን እንደሚገባ ይሰብካሉ፡ ፡ ይህ ድርጊታቸው በዴሞክራሲ ላይ ብቻ ሳይሆን በሰው ልጆችም ላይ እንደማፌዝ የሚቆጠር ከመሆኑም በተጨማሪ ለይስሙላ ያህል በውሸት በሚያመልኩት በእግዚአብሄርም ዘንድ በእጅጉ አስነዋሪና ሃጢያት መሆኑን ሊገነዘቡት ይገባቸው ነበር፡፡ ፈጣሪ የሰውን ልጅ በቀለምና በዘር በስልጣኔና በመልካም ምድር ልዩነት እየፈጠራችሁ ተፋጁ (አፋጁ) አላለም፡፡ ከዚህ ነጥብ አኳያ ተምረዋል የተባሉት አማረዋል፡፡ እነዚህ ወገኖች እየሰሩት ያለው ግፍና በደል ሲጤን መሰልጠናቸው ሳይሆን መስይጤናቸውንና ፀረ ሰውም፣ ፀረ ፈጣሪም መሆናቸውን የሚያሳይ ነው፡፡

ሀገራዊም ሆነ አለም አቀፋዊ ሁኔታዎች ለእኛ ለኢትዮጵያውያን የሚመቹ ባለመሆናቸው ተናግረን የምንደመጥበት፣ አኩርፈን የምንጠጋበት፣ ፍትህን የምናገኝበት አንድም አለኝታ የለንም፡፡ ሁሉም ነገር ያዘነበለው ወደ ገዢዎቻችን በመሆኑ የችግራችን መጠን ስፋትና ጥልቀት ተነግሮ አያልቅም፡፡ ፈጣሪ ጭምር አስጨናቂ ዘመን እንድንገፋ የፈረደብን ይመስላል፡፡ ከታሰርንበት የኑሮ ሰንሰለት ከገባንበት ምድራዊ ሲኦል ነበልባላዊ እቶን የሚታደገን ከቶ ማነው? ዳዊት በመዝሙሩ አቤቱ ጌታ ሆይ እስከመቼ ነው የምትተወኝ ያለው ወዶ አይደለም፡፡ እንደኛ ክፉኛ ቢጨንቀው እንጂ፡፡ በርግጥ መከራ ሲበዛ ያነሆልላል፤ ስቃይ ሲበዛ መፈጠርን ያስረግማል፤ ግፍና በደል ከአንድ ሰው የመሸከም አቅም ሲያልፍ ራስን ብቻ ሳይሆን ፍጣሪን ድረስ ሊያስክድ ይደርሳል፡፡

ምንም እንኳን “እረኛ ቢያኮርፍ ምሳው እራት ይሆነዋል” እንዲሉ አኩራፊ ቢያኮርፍ ከራሱ በላይ የሚጎዳው ባይኖርም የችግሩ ክረት ፈጣሪን እስከ መውቀስ ቢያደርሰው ቢያንስ ሊያስነውረው የሚገባ አይመስለኝም፡፡ በክርስቲያኑ ህይወት እንግልትና የቁም ስቅልን የሚያሳይ አሳር ሲገጥም በመፅናናት የሚጠቀስ አንድ መፅሐፍ ቅዱሳዊ ምሳሌ ነው፡ ፡ የኢዮብ ስቃይ ከእኛ ከኢትዮጵያውያን ስቃይ ማወዳደር የሚቻል አይመስለኝም፡፡ ለዘመንም ሆነ ከሌሎች መሰል ፖለቲካዊና ሃይማኖታዊ ችግሮች አንፃር የኢዮብን ከእኛ አስቸጋሪ ህይወት ላነፃፅር አልችልም፡፡

የመከራ ዶፍ የወረደበት ኢዮብ በደረሰበት ስቃይ ሰማይ ምድሩ ተደፍቶበት ጭንቅ ውስጥ በነበረበት ወቅት ከተናገረው ጥቂት እናስታውስና እኛ ከተዘፈቅንበት የችግር ማጥ አኳያ ብሶት ምን ያህል እንደሚያናግር እንመልከት፡፡ ከችግርና ከረሃብ ብዛት የተነሳ በለሊት ተነስተው ወደ በረሃ እየሄዱ ስራ ስሮችን ያኝኩ ነበር፡፡ ጨው ጨው የሚል የበርሃ ቅጠላ ቅጠሎን ይለቅሙ ነበር፡፡ ሰዎች ሌቦችን እየጮሁ እንደሚያባርሩ እነርሱም ከህብረተሰቡ መካከል ያባርሯቸው ነበር፡፡ መኖሪያቸውም በየዋሻውና በየገደሉ ስር በተቆፈረ ጉድጓድ ውስጥ ነበር፡፡

በየጫካው እየዞሩ እንደዱር አውሬ ይጮሁ ነበር:: በየቁጥቋጦው ስር ተጠግተው ይኖሩ ነበር፡፡ አሁን ግን ልጆቻቸው እየሰደቡኝ ይዘባበቱብኛል:: ተፀይፈውኝ ከእኔ ይርቃሉ ያለ አንዳች ፍርሃት እፊቴ ምራቃቸውን ይተፋሉ እግዚአብሄር ሃይሌን አድክሞ ስላዋረደኝ እነርሱም ልጓሙ እንደወለቀለት ፈረስ በላዬ ይፈነጩብኛል፡፡ የኛ ሲቃይም ከላይ ከተጠቀሰው ከኢዮብ ሲቃይና መከራ ቢበልጥ እንጂ አያንስም ችግራችን በዝቷል፤ ሸክማችን ከብዷል፤ እንዲቀልልን ለማን አቤት እንበል?

የኢትዮጵያዊያን መከራ በወያኔ ገዢዎቻቸው-ወያኔዎችም የኢትዮጵያን ልጆች በመከራ ገዙአቸው። በጽኑ ዘረኝነት፥ በስደት፥ ከስፍራ በማፈናቀል ሁሉ፥ በእስር  ቤት ሁሉ ያሉ ይጮሃል፥የእስራኤላዊያንን ነፃነት የሰጠ እግዚአብሄር ለኢትዮጵያዊያንም ነፃነታችንን እንድንጎናፀፍ ይረዳናል። እኔ ለኢትዮጵያ የጉብኝት ዘመን እንደደረሰ አምናለሁ፥እስከዛው በአንድነታችን ፀንተን ጬኸታችንን ወደ ነፃነት እንቀይረዋለን።

ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!

ዳዊት ገሰሰ  ከኖርዌይ

Revolution4ethiopia@gmail.com

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions

Reader Interactions

Comments

  1. Elias kebede says

    November 21, 2013 01:47 am at 1:47 am

    በአሁን ሰአት እንደግብፅ የአለቀው አልቆ ወያኔን ከነስሩ መንቀል ነው።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule