• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የወያኔ ሴራና ግፍ ለማን አቤት እንበል??

November 15, 2013 10:33 am by Editor 1 Comment

ኢትዮጵያውያን ብዙ ጮኽን ያዳመጠን ግን የለም፡ ፡ ለሰው ጩኽን፤ ለፈጣሪ ጩኽን፤ ለመሬትም ጮህን፤ አንዳች ምላሽ በመሻት፤ ጩኽታችን ግን ለሠማይና ለምድርም ጮህን፤ ጩኸታችን ግን የቁራ ጩኽት ሆኖ ቀረ፡፡ የተፈረደብን የመከራ ዘመን ከማለቅ ወይ ከመገባደድ ይልቅ እየጨመረ ሄደ፡፡

በግልፅ የሚታየውን ችግራችንን፣ ከፊታችን ሳይቀር የሚነበበው ጉስቁልናችን፣ ሚሊዮኖችን ምርኮኝ ያደረገ ርሃባችን፣ ፀሐይ የሞቀው የርስበርስ ፍጅታችንን ደመናን ቀርቶ የጎጇችንን ጣሪያ ማለፍ የተሳነው ምህላና ፀሎታችን ብዙዎች በየቀኑ ሽቅብ የምንረጨው እንባችን፤ ሁሉም በማንም ዘንድ ተሰሚነት አላገኘም፡፡ አሁንም ለቅሶና ዋይታችን ተባብሶ እንደቀጠለ ነው ሲባል።አሁንማ ማን የማይጮህ አለ? ሁሉንም የሚያስጮኸው ግን አንድ ነገር ነው፣የወያኔ ግፍ።

ክርስትያኑ ይጮሃል
ሙስሊሙም ይጮሃል
የመንግስትሰራተኛ ይጮሃል
የግልተቀጣሪ ይጮሃል
ቀጣሪው ይጮሃል
ስራ እጡ ይጮሃል
ነጋዴው ይጮሃል
ሸማቹ ይጮሃል
ሰራዊቱ ይጮሃል
ጋዜጠኛው ይጮሃል
እምነት የሌለው ይጮሃል
የጠገበው ይጮሃል
የራበው ይጮሃል
ይጮሃል ይጮሃል
ፖለቲከኛው ይጮሃል
ፍትህ ያጣው ይጮሃል
እስረኛው ይጮሃል
ታሪክ ይጮሃል
ሰሚአልባ ይጮሃል
 እራሱ ጩኸት ይጮሃል
እሪ በከንቱ

ተንኮለኞች ያጠመዱትን ወጥመድ የደገሱልን መከራና የሰቆቃ ድግስ ከዘመናት በፊት በሴራ መክረው ያወጁብን የጥፋት ዘመን በብሄርና በጎሳ ከፋፍለው የኢትዮጵያን አንድነት ለመነጣጠል በመካከላችን የከተቱብን የተኩላ መንጋ ሁሉም እንዳሰቡት ሆኖ ትንቢታቸው ሲይዝላቸውና ምኞታቸው ሲሳካላቸው በስቃያችን ይደሰታሉ፡፡ በቁስላችን የጋለ ብረት እየሰደዱ ለቅሷችንን እንደ ጥጋብ፣ ጭንቀት ጥበታችንን እንደ ደስታ፣ ጦርነታችንን እንደ መዝናኛ፣ መባዘናችንን እንደ በረከት፣ የርስ በርስ እልቂታችንን እንደሰላም በመቁጠር ያላግጡብናል፡፡ እውነቱን የማያውቁ ይመስል የላኳቸውን እንደራሴዎች የሚሰሩትን የማይረዱ ይመስል፡፡ የእኛን መከራና ችግር እንደማያውቁ ሆነው በመቆለል በጣት የሚቆጠሩ የተሻለ ኑሮ የሚኖሩ በገጠር በግብርና የሚተዳደሩትን ከተማ ያሉ ሃብታችን በመመልከት ብቻ ጥሩ ኑሮ ላይ ነን ይላሉ፡፡ እነዚያም ተቀብለው “ይኽ መቸ አነሳችሁ፤ ጥሩ ኑሮ እየኖራችሁ ነው” በማለት ይሳለቁብናል፡፡

ጥቂት የምትባል የመናገር፣ የመፃፍ ግድብ (ዴሞክራሲ) መብት በማየት ብቻ ዴሞክራሲያችን እዚህ ደርሷል በማለት አዎንታዊ አብነት ወስደው ከእኛ አልፈው ለሌሎች አገሮች ማስተማሪያ ሊሆን እንደሚገባ ይሰብካሉ፡ ፡ ይህ ድርጊታቸው በዴሞክራሲ ላይ ብቻ ሳይሆን በሰው ልጆችም ላይ እንደማፌዝ የሚቆጠር ከመሆኑም በተጨማሪ ለይስሙላ ያህል በውሸት በሚያመልኩት በእግዚአብሄርም ዘንድ በእጅጉ አስነዋሪና ሃጢያት መሆኑን ሊገነዘቡት ይገባቸው ነበር፡፡ ፈጣሪ የሰውን ልጅ በቀለምና በዘር በስልጣኔና በመልካም ምድር ልዩነት እየፈጠራችሁ ተፋጁ (አፋጁ) አላለም፡፡ ከዚህ ነጥብ አኳያ ተምረዋል የተባሉት አማረዋል፡፡ እነዚህ ወገኖች እየሰሩት ያለው ግፍና በደል ሲጤን መሰልጠናቸው ሳይሆን መስይጤናቸውንና ፀረ ሰውም፣ ፀረ ፈጣሪም መሆናቸውን የሚያሳይ ነው፡፡

ሀገራዊም ሆነ አለም አቀፋዊ ሁኔታዎች ለእኛ ለኢትዮጵያውያን የሚመቹ ባለመሆናቸው ተናግረን የምንደመጥበት፣ አኩርፈን የምንጠጋበት፣ ፍትህን የምናገኝበት አንድም አለኝታ የለንም፡፡ ሁሉም ነገር ያዘነበለው ወደ ገዢዎቻችን በመሆኑ የችግራችን መጠን ስፋትና ጥልቀት ተነግሮ አያልቅም፡፡ ፈጣሪ ጭምር አስጨናቂ ዘመን እንድንገፋ የፈረደብን ይመስላል፡፡ ከታሰርንበት የኑሮ ሰንሰለት ከገባንበት ምድራዊ ሲኦል ነበልባላዊ እቶን የሚታደገን ከቶ ማነው? ዳዊት በመዝሙሩ አቤቱ ጌታ ሆይ እስከመቼ ነው የምትተወኝ ያለው ወዶ አይደለም፡፡ እንደኛ ክፉኛ ቢጨንቀው እንጂ፡፡ በርግጥ መከራ ሲበዛ ያነሆልላል፤ ስቃይ ሲበዛ መፈጠርን ያስረግማል፤ ግፍና በደል ከአንድ ሰው የመሸከም አቅም ሲያልፍ ራስን ብቻ ሳይሆን ፍጣሪን ድረስ ሊያስክድ ይደርሳል፡፡

ምንም እንኳን “እረኛ ቢያኮርፍ ምሳው እራት ይሆነዋል” እንዲሉ አኩራፊ ቢያኮርፍ ከራሱ በላይ የሚጎዳው ባይኖርም የችግሩ ክረት ፈጣሪን እስከ መውቀስ ቢያደርሰው ቢያንስ ሊያስነውረው የሚገባ አይመስለኝም፡፡ በክርስቲያኑ ህይወት እንግልትና የቁም ስቅልን የሚያሳይ አሳር ሲገጥም በመፅናናት የሚጠቀስ አንድ መፅሐፍ ቅዱሳዊ ምሳሌ ነው፡ ፡ የኢዮብ ስቃይ ከእኛ ከኢትዮጵያውያን ስቃይ ማወዳደር የሚቻል አይመስለኝም፡፡ ለዘመንም ሆነ ከሌሎች መሰል ፖለቲካዊና ሃይማኖታዊ ችግሮች አንፃር የኢዮብን ከእኛ አስቸጋሪ ህይወት ላነፃፅር አልችልም፡፡

የመከራ ዶፍ የወረደበት ኢዮብ በደረሰበት ስቃይ ሰማይ ምድሩ ተደፍቶበት ጭንቅ ውስጥ በነበረበት ወቅት ከተናገረው ጥቂት እናስታውስና እኛ ከተዘፈቅንበት የችግር ማጥ አኳያ ብሶት ምን ያህል እንደሚያናግር እንመልከት፡፡ ከችግርና ከረሃብ ብዛት የተነሳ በለሊት ተነስተው ወደ በረሃ እየሄዱ ስራ ስሮችን ያኝኩ ነበር፡፡ ጨው ጨው የሚል የበርሃ ቅጠላ ቅጠሎን ይለቅሙ ነበር፡፡ ሰዎች ሌቦችን እየጮሁ እንደሚያባርሩ እነርሱም ከህብረተሰቡ መካከል ያባርሯቸው ነበር፡፡ መኖሪያቸውም በየዋሻውና በየገደሉ ስር በተቆፈረ ጉድጓድ ውስጥ ነበር፡፡

በየጫካው እየዞሩ እንደዱር አውሬ ይጮሁ ነበር:: በየቁጥቋጦው ስር ተጠግተው ይኖሩ ነበር፡፡ አሁን ግን ልጆቻቸው እየሰደቡኝ ይዘባበቱብኛል:: ተፀይፈውኝ ከእኔ ይርቃሉ ያለ አንዳች ፍርሃት እፊቴ ምራቃቸውን ይተፋሉ እግዚአብሄር ሃይሌን አድክሞ ስላዋረደኝ እነርሱም ልጓሙ እንደወለቀለት ፈረስ በላዬ ይፈነጩብኛል፡፡ የኛ ሲቃይም ከላይ ከተጠቀሰው ከኢዮብ ሲቃይና መከራ ቢበልጥ እንጂ አያንስም ችግራችን በዝቷል፤ ሸክማችን ከብዷል፤ እንዲቀልልን ለማን አቤት እንበል?

የኢትዮጵያዊያን መከራ በወያኔ ገዢዎቻቸው-ወያኔዎችም የኢትዮጵያን ልጆች በመከራ ገዙአቸው። በጽኑ ዘረኝነት፥ በስደት፥ ከስፍራ በማፈናቀል ሁሉ፥ በእስር  ቤት ሁሉ ያሉ ይጮሃል፥የእስራኤላዊያንን ነፃነት የሰጠ እግዚአብሄር ለኢትዮጵያዊያንም ነፃነታችንን እንድንጎናፀፍ ይረዳናል። እኔ ለኢትዮጵያ የጉብኝት ዘመን እንደደረሰ አምናለሁ፥እስከዛው በአንድነታችን ፀንተን ጬኸታችንን ወደ ነፃነት እንቀይረዋለን።

ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!

ዳዊት ገሰሰ  ከኖርዌይ

Revolution4ethiopia@gmail.com

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions

Reader Interactions

Comments

  1. Elias kebede says

    November 21, 2013 01:47 am at 1:47 am

    በአሁን ሰአት እንደግብፅ የአለቀው አልቆ ወያኔን ከነስሩ መንቀል ነው።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule