• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የወያኔ ሴራና ግፍ ለማን አቤት እንበል??

November 15, 2013 10:33 am by Editor 1 Comment

ኢትዮጵያውያን ብዙ ጮኽን ያዳመጠን ግን የለም፡ ፡ ለሰው ጩኽን፤ ለፈጣሪ ጩኽን፤ ለመሬትም ጮህን፤ አንዳች ምላሽ በመሻት፤ ጩኽታችን ግን ለሠማይና ለምድርም ጮህን፤ ጩኸታችን ግን የቁራ ጩኽት ሆኖ ቀረ፡፡ የተፈረደብን የመከራ ዘመን ከማለቅ ወይ ከመገባደድ ይልቅ እየጨመረ ሄደ፡፡

በግልፅ የሚታየውን ችግራችንን፣ ከፊታችን ሳይቀር የሚነበበው ጉስቁልናችን፣ ሚሊዮኖችን ምርኮኝ ያደረገ ርሃባችን፣ ፀሐይ የሞቀው የርስበርስ ፍጅታችንን ደመናን ቀርቶ የጎጇችንን ጣሪያ ማለፍ የተሳነው ምህላና ፀሎታችን ብዙዎች በየቀኑ ሽቅብ የምንረጨው እንባችን፤ ሁሉም በማንም ዘንድ ተሰሚነት አላገኘም፡፡ አሁንም ለቅሶና ዋይታችን ተባብሶ እንደቀጠለ ነው ሲባል።አሁንማ ማን የማይጮህ አለ? ሁሉንም የሚያስጮኸው ግን አንድ ነገር ነው፣የወያኔ ግፍ።

ክርስትያኑ ይጮሃል
ሙስሊሙም ይጮሃል
የመንግስትሰራተኛ ይጮሃል
የግልተቀጣሪ ይጮሃል
ቀጣሪው ይጮሃል
ስራ እጡ ይጮሃል
ነጋዴው ይጮሃል
ሸማቹ ይጮሃል
ሰራዊቱ ይጮሃል
ጋዜጠኛው ይጮሃል
እምነት የሌለው ይጮሃል
የጠገበው ይጮሃል
የራበው ይጮሃል
ይጮሃል ይጮሃል
ፖለቲከኛው ይጮሃል
ፍትህ ያጣው ይጮሃል
እስረኛው ይጮሃል
ታሪክ ይጮሃል
ሰሚአልባ ይጮሃል
 እራሱ ጩኸት ይጮሃል
እሪ በከንቱ

ተንኮለኞች ያጠመዱትን ወጥመድ የደገሱልን መከራና የሰቆቃ ድግስ ከዘመናት በፊት በሴራ መክረው ያወጁብን የጥፋት ዘመን በብሄርና በጎሳ ከፋፍለው የኢትዮጵያን አንድነት ለመነጣጠል በመካከላችን የከተቱብን የተኩላ መንጋ ሁሉም እንዳሰቡት ሆኖ ትንቢታቸው ሲይዝላቸውና ምኞታቸው ሲሳካላቸው በስቃያችን ይደሰታሉ፡፡ በቁስላችን የጋለ ብረት እየሰደዱ ለቅሷችንን እንደ ጥጋብ፣ ጭንቀት ጥበታችንን እንደ ደስታ፣ ጦርነታችንን እንደ መዝናኛ፣ መባዘናችንን እንደ በረከት፣ የርስ በርስ እልቂታችንን እንደሰላም በመቁጠር ያላግጡብናል፡፡ እውነቱን የማያውቁ ይመስል የላኳቸውን እንደራሴዎች የሚሰሩትን የማይረዱ ይመስል፡፡ የእኛን መከራና ችግር እንደማያውቁ ሆነው በመቆለል በጣት የሚቆጠሩ የተሻለ ኑሮ የሚኖሩ በገጠር በግብርና የሚተዳደሩትን ከተማ ያሉ ሃብታችን በመመልከት ብቻ ጥሩ ኑሮ ላይ ነን ይላሉ፡፡ እነዚያም ተቀብለው “ይኽ መቸ አነሳችሁ፤ ጥሩ ኑሮ እየኖራችሁ ነው” በማለት ይሳለቁብናል፡፡

ጥቂት የምትባል የመናገር፣ የመፃፍ ግድብ (ዴሞክራሲ) መብት በማየት ብቻ ዴሞክራሲያችን እዚህ ደርሷል በማለት አዎንታዊ አብነት ወስደው ከእኛ አልፈው ለሌሎች አገሮች ማስተማሪያ ሊሆን እንደሚገባ ይሰብካሉ፡ ፡ ይህ ድርጊታቸው በዴሞክራሲ ላይ ብቻ ሳይሆን በሰው ልጆችም ላይ እንደማፌዝ የሚቆጠር ከመሆኑም በተጨማሪ ለይስሙላ ያህል በውሸት በሚያመልኩት በእግዚአብሄርም ዘንድ በእጅጉ አስነዋሪና ሃጢያት መሆኑን ሊገነዘቡት ይገባቸው ነበር፡፡ ፈጣሪ የሰውን ልጅ በቀለምና በዘር በስልጣኔና በመልካም ምድር ልዩነት እየፈጠራችሁ ተፋጁ (አፋጁ) አላለም፡፡ ከዚህ ነጥብ አኳያ ተምረዋል የተባሉት አማረዋል፡፡ እነዚህ ወገኖች እየሰሩት ያለው ግፍና በደል ሲጤን መሰልጠናቸው ሳይሆን መስይጤናቸውንና ፀረ ሰውም፣ ፀረ ፈጣሪም መሆናቸውን የሚያሳይ ነው፡፡

ሀገራዊም ሆነ አለም አቀፋዊ ሁኔታዎች ለእኛ ለኢትዮጵያውያን የሚመቹ ባለመሆናቸው ተናግረን የምንደመጥበት፣ አኩርፈን የምንጠጋበት፣ ፍትህን የምናገኝበት አንድም አለኝታ የለንም፡፡ ሁሉም ነገር ያዘነበለው ወደ ገዢዎቻችን በመሆኑ የችግራችን መጠን ስፋትና ጥልቀት ተነግሮ አያልቅም፡፡ ፈጣሪ ጭምር አስጨናቂ ዘመን እንድንገፋ የፈረደብን ይመስላል፡፡ ከታሰርንበት የኑሮ ሰንሰለት ከገባንበት ምድራዊ ሲኦል ነበልባላዊ እቶን የሚታደገን ከቶ ማነው? ዳዊት በመዝሙሩ አቤቱ ጌታ ሆይ እስከመቼ ነው የምትተወኝ ያለው ወዶ አይደለም፡፡ እንደኛ ክፉኛ ቢጨንቀው እንጂ፡፡ በርግጥ መከራ ሲበዛ ያነሆልላል፤ ስቃይ ሲበዛ መፈጠርን ያስረግማል፤ ግፍና በደል ከአንድ ሰው የመሸከም አቅም ሲያልፍ ራስን ብቻ ሳይሆን ፍጣሪን ድረስ ሊያስክድ ይደርሳል፡፡

ምንም እንኳን “እረኛ ቢያኮርፍ ምሳው እራት ይሆነዋል” እንዲሉ አኩራፊ ቢያኮርፍ ከራሱ በላይ የሚጎዳው ባይኖርም የችግሩ ክረት ፈጣሪን እስከ መውቀስ ቢያደርሰው ቢያንስ ሊያስነውረው የሚገባ አይመስለኝም፡፡ በክርስቲያኑ ህይወት እንግልትና የቁም ስቅልን የሚያሳይ አሳር ሲገጥም በመፅናናት የሚጠቀስ አንድ መፅሐፍ ቅዱሳዊ ምሳሌ ነው፡ ፡ የኢዮብ ስቃይ ከእኛ ከኢትዮጵያውያን ስቃይ ማወዳደር የሚቻል አይመስለኝም፡፡ ለዘመንም ሆነ ከሌሎች መሰል ፖለቲካዊና ሃይማኖታዊ ችግሮች አንፃር የኢዮብን ከእኛ አስቸጋሪ ህይወት ላነፃፅር አልችልም፡፡

የመከራ ዶፍ የወረደበት ኢዮብ በደረሰበት ስቃይ ሰማይ ምድሩ ተደፍቶበት ጭንቅ ውስጥ በነበረበት ወቅት ከተናገረው ጥቂት እናስታውስና እኛ ከተዘፈቅንበት የችግር ማጥ አኳያ ብሶት ምን ያህል እንደሚያናግር እንመልከት፡፡ ከችግርና ከረሃብ ብዛት የተነሳ በለሊት ተነስተው ወደ በረሃ እየሄዱ ስራ ስሮችን ያኝኩ ነበር፡፡ ጨው ጨው የሚል የበርሃ ቅጠላ ቅጠሎን ይለቅሙ ነበር፡፡ ሰዎች ሌቦችን እየጮሁ እንደሚያባርሩ እነርሱም ከህብረተሰቡ መካከል ያባርሯቸው ነበር፡፡ መኖሪያቸውም በየዋሻውና በየገደሉ ስር በተቆፈረ ጉድጓድ ውስጥ ነበር፡፡

በየጫካው እየዞሩ እንደዱር አውሬ ይጮሁ ነበር:: በየቁጥቋጦው ስር ተጠግተው ይኖሩ ነበር፡፡ አሁን ግን ልጆቻቸው እየሰደቡኝ ይዘባበቱብኛል:: ተፀይፈውኝ ከእኔ ይርቃሉ ያለ አንዳች ፍርሃት እፊቴ ምራቃቸውን ይተፋሉ እግዚአብሄር ሃይሌን አድክሞ ስላዋረደኝ እነርሱም ልጓሙ እንደወለቀለት ፈረስ በላዬ ይፈነጩብኛል፡፡ የኛ ሲቃይም ከላይ ከተጠቀሰው ከኢዮብ ሲቃይና መከራ ቢበልጥ እንጂ አያንስም ችግራችን በዝቷል፤ ሸክማችን ከብዷል፤ እንዲቀልልን ለማን አቤት እንበል?

የኢትዮጵያዊያን መከራ በወያኔ ገዢዎቻቸው-ወያኔዎችም የኢትዮጵያን ልጆች በመከራ ገዙአቸው። በጽኑ ዘረኝነት፥ በስደት፥ ከስፍራ በማፈናቀል ሁሉ፥ በእስር  ቤት ሁሉ ያሉ ይጮሃል፥የእስራኤላዊያንን ነፃነት የሰጠ እግዚአብሄር ለኢትዮጵያዊያንም ነፃነታችንን እንድንጎናፀፍ ይረዳናል። እኔ ለኢትዮጵያ የጉብኝት ዘመን እንደደረሰ አምናለሁ፥እስከዛው በአንድነታችን ፀንተን ጬኸታችንን ወደ ነፃነት እንቀይረዋለን።

ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!

ዳዊት ገሰሰ  ከኖርዌይ

Revolution4ethiopia@gmail.com

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions

Reader Interactions

Comments

  1. Elias kebede says

    November 21, 2013 01:47 am at 1:47 am

    በአሁን ሰአት እንደግብፅ የአለቀው አልቆ ወያኔን ከነስሩ መንቀል ነው።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule