• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በአዲስ አበባ ውሃ እስከ 20ቀናት ይጠፋል

March 16, 2014 11:44 pm by Editor 2 Comments

* “የውኃ ምርት ችግር የለብንም የኤሌክትሪክና የማሰራጨት እንጂ” የውኃና ፍሳሽ ባለሥልጣን

የፌዴራል መንግሥት መቀመጫና የአፍሪካ መዲና በሆነችው በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ፣ ለሁለትና ሦስት ቀናት ይጠፋ የነበረው የውኃ ችግር እስከ 20 ቀናት እየጠፋ  መሆኑንና ችግሩ ተባብሶ መቀጠሉን ነዋሪዎች እየገለጹ ነው፡፡

በተለይ ከሳሪስ እስከ ቃሊቲ፣ አየር ጤና፣ ወይራ ሠፈር፣ ለቡ፣ ጉለሌ፣ ኮልፌ ቀራኒዮ፣ ፒያሳ፣ ሽሮ ሜዳ፣ መርካቶ፣ የካ በተለያዩ ወረዳዎች አራት ኪሎ (አልፎ አልፎ) በአጠቃላይ በከተማው ከአምስት እስከ 20 ቀናት ውኃ ጠፍቶ እንደሚሰቃዩ ገልጸዋል፡፡ ወ/ሮ ስንታየሁ አበበ የተባሉ የሳሪስ አቦ ማዞሪያ አካባቢ ነዋሪ እንደገለጹት፣ የውኃ ችግር ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ መምጣቱ ያስገርማቸዋል፡፡ ቀን ቀን ይጠፋና እኩለ ሌሊት ይመጣላቸው በነበረው ውኃ ሲማረሩ፣ ይባስ ብሎ የመጥፋቱ ሁኔታ ወደ ሦስት፣ አራትና አምስት ቀናት አድጐ አሁን እስከ 20 ቀናት ውኃ እንደማያገኙ ጠቁመዋል፡፡ በመንገድ ግንባታ ምክንያት በሚል በተለይ ከ2001 ዓ.ም. እስከ 2004 ዓ.ም. መጀመርያ ወር ድረስ በፈረቃ በሁለትና ሦስት ቀናት ቆይታ ያገኙት የነበረው ውኃ፣ መንገዱ ከተጠናቀቀ በኋላ ብሶበት ወደ ወር ሊቃረብ መድረሱንና አሁን ባለው ሁኔታ በቅርቡ ወር ሙሉ ላያገኙ እንደሚችሉ ተናግረዋል፡፡

መንግሥት ከፍታ ባላቸው አካባቢዎች ውኃ ማዳረስ እንዳቃተው አምኖ ሲገልጽ የከረመ ቢሆንም አሁን ግን በለገዳዲ፣ ገፈርሳና አቃቂ ቃሊቲ የከርሰ ምድር ውኃ አካባቢ ያሉ ነዋሪዎችም ውኃ እያጡ በመሆኑ ‹‹ምን ተፈጠረ?›› የሚል ጥያቄ እየተፈጠረባቸው መሆኑን ወ/ሮ ስንታየሁ ገልጸዋል፡፡ ቀደም ባሉት ጊዜያት ውኃና ኤሌክትሪክ  የሚጠፉበት ጊዜና ቀናት በመገናኛ ብዙኃን ይነገር እንደነበር ያስታወሱት ወይዘሮዋ፣ አሁን መንግሥት ሰልችቶት ይሁን አሳፍሮት ዝምታን መምረጡ እያሰጋቸው መሆኑን አክለዋል፡፡

ከመሀል አዲስ አበባ (ፒያሳ) ጀምሮ እስከ ዳር ከተማና አቀበት በሚባሉ አካባቢዎች የሚኖሩ ሁሉ እንደ ወ/ሮ ስንታየሁ ‹‹የውኃ ያለህ›› እያሉ ሲሆን፣ የውኃና ፍሳሽ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶች፣ በክፍለ ከተማና እስከ ማዘጋጃ ድረስ እየሄዱ አቤት ቢሉም ምላሽ ሊያገኙ እንዳልቻሉ እየገለጹ ነው፡፡ ከሁለት ሳምንት በፊት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ድሪባ ኩማ ባቀረቡት የግማሽ በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ላይ፣ ውኃን በሚመለከት ያቀረቡትን ሪፖርት በተለይ በውኃ ችግር water lineውስጥ ያሉ ነዋሪዎች አምርረው እየተቃወሙ ነው፡፡ አንድ ስማቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉ የሽሮ ሜዳ ነዋሪ እንደገለጹት፣ ‹‹እኛስ መጣች መጣች ብለን ሌሊቱን ስንሯሯጥ መኖሩን ለምደነዋል፡፡ የኛ ዕጣ ፈንታ የደረሳቸው የመሀል ከተማ ነዋሪዎች ግን ያሳዝኑኛል፡፡ ይበልጥ ደግሞ ያዘንኩት የታደለ አገር በዘመናዊ መንገድ ማንኛውንም አቅርቦት እንደልቡ ሲቀርብለት፣ እኛ የውኃ ጥም ለማርካት ቦቴ መኪና እንደሚገዛልን እየተነገረን ነው፤›› በማለት የከንቲባውን ሪፖርት ተገቢ አለመሆኑን በመግለጽ ተቃውመዋል፡፡

አስተዳደሩ ትኩረት በመስጠት ከተንቀሳቀሰባቸው ተግባራት አንዱ የውኃ ምርትን መጨመር መሆኑን የገለጹት ከንቲባ ድሪባ፣ በአቃቂ ቃሊቲ 19 ጥልቅ ጉድጓዶች መቆፈራቸውንና 80 ሺሕ ሜትር ኩብ ውኃ ማምረት መቻሉን፣ በለገዳዲም 11 ጥልቅ ጉድጓዶች እየተቆፈሩ መሆኑን፣ ለገዳዲን በማስፋትና የድሬ ግድብን በማሻሻል የውኃ ማምረት አቅምን ወደ 195 ሺሕ ሜትር ኩብ ለማሳደግ የሚያስችል ሥራ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በአጠቃላይ ወደ 260 ሺሕ ሜትር ኩብ የሚጠጋ ውኃ ማምረት የሚያስችል ሥራ እየተሠራ መሆኑንና ሁሉም ሥራዎች ሲጠናቀቁ 610 ሺሕ ሜትር ኩብ የውኃ ምርት ከፍ እንደሚልም በሪፖርታቸው ከንቲባው አብራርተዋል፡፡

ነዋሪዎች ግን ሥራውና ዕቅዱ ወይም እንቅስቃሴው ከወረቀት ላይ እንደማያልፍ  በመግለጽ፣ የዕለት ጥማቸውን የሚያስታግሱበት መፍትሔ እንዲፈለግላቸው እየጠየቁ ነው፡፡

የአዲስ አበባ ውኃና ፍሳሽ ባለሥልጣን ግን በነዋሪዎቹ አቤቱታና ሮሮ አይስማማም፡፡ ‹‹የውኃ ምርት እጥረት የለብንም፣ ችግራችን የሥርጭት ነው፡፡ ለዚህ ደግሞ የመንገድ ግንባታዎችና በተደጋጋሚ የኤሌክትሪክ መጥፋት ከፍተኛ ችግር እየፈጠረብን ነው፤›› ሲሉ የባለሥልጣኑ ኮሙዩኒኬሽን ኃላፊ የሥራ ሒደት ባለቤት አቶ ሙሉጌታ ከምሴ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

ባለሥልጣኑ ችግር ያለባቸውን አካባቢዎች ለይቶ ማወቁንና ከፍተኛ ችግር አለባቸው የተባሉትን ንፋስ ስልክ ላፍቶ፣ ጉለሌ፣ የካና ኮልፌ ቀራኒዮ ክፍላተ ከተማዎች ውስጥ ለሚገኙ ነዋሪዎች፣ ለተወሰኑት ጊዜያዊ የፕላስቲክ መስመር እየዘረጋ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ አቀበት ለሆኑት ደግሞ በመከላከያ ኢንጂነሪንግ ያሠራቸውን ታንከሮች እየተተከለ መሆኑን፣ ዘላቂ መፍትሔ ለማምጣት ደግሞ ጄኔሬተር እየተገዛና የፀሐይ ኃይል ለመጠቀም ጥናት እየተካሄደ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ (ሪፖርተር)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. liku says

    March 17, 2014 07:28 am at 7:28 am

    It is really a shame to have water distribution problem in the capital city of Africa union head quarter And this a country which was boasting electric power distribution to neighboring countries

    Reply
  2. Tesfaye says

    March 17, 2014 12:27 pm at 12:27 pm

    It is now a month since we got clean water around Betel Hospital. Who will resign from his or her post because of this failure?? I know none!!!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule