• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ወጣቱ የሰሜን ኮሪያ መሪ አጎታቸውን ገደሉ!

December 14, 2013 02:42 am by Editor 2 Comments

ወጣቱ የሰሜን ኮሪያ ፕሬዚዳንት ኪም ጆንግ ኧን አጎታቸውንና በሰሜን ኮሪያ የሥልጣን እርከን ሁለተኛ የነበሩትን ጃንግ ሶንግ-ታዬክ አስገደሉ፡፡ ግድያውን በተመለከተ የተለያዩ አስተያየቶች እየተሰጡ ቢሆንም የመንግሥት ሚዲያ እንዳለው ከሆነ አጎትየው ጃንግ “መንግሥት ለመገልበጥ ሙከራ በማድረግ አስጸያፊ ወንጀል ሰርተዋል” ብሏል፡፡

jang3
መካከል የሚታዩት ጃንግ ሶንግ-ታዬክ በቀኝ ያሉት ወጣቱ መሪ ኪም ጆንግ ኧን ናቸው

ሰሜን ኮሪያን ለረጅም ዓመታት ሲመሩ የነበሩትንና ሥልጣናቸውን ከመጀመሪያው የሰሜን ኮሪያ ፕሬዚዳንት ኪም ኤል ሱንግ የተረከቡት ኪም ጆንግ ኢል ባልተጠበቀ ፍጥነት ሲሞቱ ወጣቱ ኪም ጆንግ ኧን ሥልጣን መንበር ላይ ተቆናጠጡ፡፡ በወቅቱ በሃያዎቹ መጨረሻ ዕድሜ ላይ የሚገኙት ኧን ከልምድ ማነስ ችግር ውስጥ እንዳይገቡ በማሰብ አባታቸው ኪም ጆንግ ኢል አስቀድመው ከጎናቸው የሚሆኑ ሞግዚትና አለማማጅ አዘጋጅተው ነበር፡፡

ኪም ጆንግ ኢል የጤናቸው ሁኔታ እየተቃወሰ መምጣቱን በአብዛኛው ይፋ ሆኖ ባይታወቅም ለእርሳቸው ግን የተሰወረ ባለመሆኑ የሥልጣኑን መንበር ሲያዘጋጁና ሲመቻቹ ከአንድ ዓመት በላይ አልፏቸዋል፡፡ በመንግሥት ውስጥ ያለውን አመራርና አሠራር እንዲያስተምሯቸው አጎት ጃንግ ሶንግ-ታዬክ ተመደቡ፡፡ ኪም ጆንግ ኢል ከሞቱም በኋላ ልጃቸው ኪም ጆንግ ኧን በፕሬዚዳንትነት ሥልጣኑን ቢረከቡም ወሳኝ የሆነው የአገሪቱ ሥልጣንና አስተዳደር በሞግዚታቸው አጎት ጃንግ የተያዘ ነበር፡፡ ሰሞኑን ከሥልጣን እስኪወገዱ ድረስ አጎት ጃንግ ከታላቁ መሪ ወሳኝ ፖሊሲ አማካሪነት በተጨማሪ የብሔራዊ መከላከያ ኮሚሽን ምክትል ሊቀመንበር ነበሩ፡፡Jang2

የአጎት ጃንግ ወንጀል ይፋ ከሆነ በኋላ በድንገት ከፖሊት ቢሮ ስብሰባ ላይ በወታደሮች እንዲወገዱ ተደረገ፡፡ ከዚያም ወደ ወታደራዊ ፍርድቤት እንዲቀርቡ በመደረግ በሞት እንዲቀጡ ተወሰነባቸው፡፡ የሞት ቅጣቱ ከተፈጸመ በኋላ የሰሜን ኮሪያ ዜና አገልግሎት አጎት ጃንግ “አሳፋሪና አጸያፊ ህይወት ሲመሩ” የነበሩ መሆናቸውን በመግለጽ ረጅም ዘገባ አወጣ፡፡ “ስኳሮቻቸው” ምን እንደነበሩ በዝርዝርም ተነገረባቸው፡፡ ገንዘብ አባካኝ፣ አደንዛዥ ዕጽ ተጠቃሚ፣ ለህክምና ወደ ውጭ አገር ተልከው በርካታ ገንዘብ ያባክኑ፣ ቁማርተኛ፣ ሴት አውል (ሴሰኛ)፣ ሙሰኛ፣ … ፡፡ ወዲያውም በሰሜን ኮሪያ ታሪክ ተፈጽሞ በማያውቅ መልኩ በይፋ ከፖሊት ቢሮ በወታደር ታጅበው ዘብጥያ ወረዱ፤ ከማንኛውም መንግሥታዊ ሥልጣናቸውም ተገፈፈ፡፡ ሰሜን ኮሪያ ከዚህ በፊት እንዲህ አይነት “የማጽዳት ሥራ” አካሂዳ ታውቃለች ነገር ግን በዚህ መልኩ በይፋ ተደርጎ አያውቅም፡፡

jang6
በግራ በኩል በሚታየው ፎቶ ጃንግ ሶንግ-ታዬክ የነበሩ ሲሆን እርምጃው ከተወሰደባቸው በኋላ በሰሜን ኮሪያ ቲቪ ምስላቸው ተቆርጦዋል

የክሱ መዝገብም ዳጎስ እንዲል መንግሥት ለመገልበጥ የሞከሩ የሚል ተጨመረበት፡፡ ባስቸኳይ የጦር ፍርድቤት ተወስደው ሞት ተበየነባቸው፡፡ ተገደሉ፤ የኮሪያ ዜናም ሃተታውን አወጣ፤ ከዚያም አልፎ በፊት በሞግዚትነት ከሚረዷቸው ኧን ጋር የተነሱት ፎቶዎች በሙሉ የአጎት ጃንግ ምስል በፎቶ ማረሚያ ጥበብ እንዲወገድ ተደረገ፡፡ አጎት ጃንግ ከሰሜን ኮሪያ ታሪክ፣ አመራር፣ ህይወት፣ … ተሰረዙ፡፡ ማንነታቸውም ጭምር ተወገደ፡፡ ግን ይህ ሁሉ ለምን መደረግ አስፈለገው? ታላቁ መሪ ኧን ለምን በሞግዚትና አጎታቸው ላይ ይህንን ዓይነት አሰቃቂ ፍርድ ፈረዱ?

በኮሪያ ጉዳይ ላይ አጥኚ የሆኑት አንድሬ ላንኮቭ ሦስት ምክንያቶችን ያቀርባሉ፡-

  1. ሞግዚቶች ብዙውን ጊዜ ሥራቸው ሲጠናቀቅ ይወገዳሉ፡፡ ወጣቱ ኧን ወደ ሥልጣን መንበር ሲመጡ ብዙ ልምድ ስላልነበራቸው በአጎት ጃንግ ትዕዛዝና አመራር ነበር በርካታ ጉዳዮችን ሲፈጽሙ የቆዩት፡፡ አሁን ግን ሰላሳዎቹን ደፍነዋል በሚባበት ወቅት ላይ ስለሚገኙ የአመራር ብቃታቸውንም ሆነ በግላቸው የሚወስኑ መሆናቸውን ለማሳይት ይፈልጋሉ፡፡ ከዚህም በላይ በፊት እንደ አለቃ ይህንን አድርግ ይህንን አታድርግ ሲሏቸው የነበሩትን ሰው ማስወገድ ቀዳሚ ተግባራቸው መሆን አለበት፡፡ ተፈሪ ለመሆን ይህንን ማድረግ የግድ ሆኖባቸዋል፡፡ የዚያኑ ያክልም ይኸው ድርጊት በሌላ አቅጣጫ ኧን ራሳቸውን መቆጣጠር የማይችሉና አሁንም ብስለት የሌላቸው አድርጎ ሊያስገምታቸው ይችላል፡፡
  2. ኧን የተከፈለው ተከፍሎ የራሳቸውን የአገዛዝ መስመር ለመጀመር ፈልገዋል፡፡ የበፊቱ ፕሬዚዳንት ኪም ጆንግ ኢል ከአባታቸው ኪም ኤል ሱንግ ሥልጣን በተረከቡ ጊዜ በአገሪቱ ላይ ረሃብ በመንገሡ ሥልጣን ለመረከብ ብዙም ፈቃደኛ አልነበሩም፡፡ የወደፊቱን አስተዳደራቸውን ለመገንባትም የግድ የአባታቸውን ባለሟሎች በሥልጣናቸው ማካተት ነበረባቸው፡፡ በአንጻሩ ኪም ጆንግ ኧን እንዳባታቸው ሥልጣኑን ላለመረከብ የፈለጉ አይመስሉም፡፡ በሥልጣን መንበር ላይ ከተቀመጡበት ጊዜ ጀምሮ በሚዲያ ላይ በደጋጋሚ በመቅረብ የተለያዩ የልማት ሃሳቦችን በማቅረብ ሲታዩ ከርመዋል፡፡ በመሆኑም አሁን አዲስና የራሳቸው የሆነ ሥርዓት ለመገንባት በሚያደርጉት ጥረት የቀድሞ ባለሥልጣናትን ማስወገድ መፈለጋቸው እሙን ነው፡፡ አጎት ጃንግ ዓይነት መጠጥ ያሉ ባለሥልጣናትን ለማስወገድ በሚደረገው እርምጃ ተቃውሞ ሊኖር እንደሚችል ስለሚገመት አስቀድሞ ትልቁን ግንድ መገርሰስ ለሌሎቹ የሚሰጠው ትምህርት አለ፡፡ ለዚህም ነው በአጎት ጃንግ ላይ የተወሰደው እርምጃ በይፋ እንዲታይ የተደረገውም ለዚህ ነው፡፡
  3. በኮሪያ አመራር ውስጥ ያሉ አዛውንት አመራሮችን ሰጥ ለጥ ብለው እንዲገዙ ለማድረግ ነው፡፡ እንደሚታወቀው ሰሜን ኮሪያ በርካታ በዕድሜ የገፉ አመራሮች በሥልጣን ላይ የሚገኙ በመሆናቸው አዲሱንና ወጣቱን መሪ ለመታዘዝ ያላቸው ተነሳሽነት ዝቅተኛ እንደሚሆን ግልጽ ነው፡፡ በመሆኑም ሁሉንም ታዛዥ እንዲሆኑና ለኧን ሥልጣናቸውን በሙላት እንደለማመዱ ለማድረግ አዛውንቶቹን አመራሮች ማስደንገጥ የግድ ይላል፡፡ በሰሜን ኮሪያ ሁለተኛ በነበሩት አጎት ጃንግ ላይ እንዲህ ዓይነት እርምጃ ከተወሰደ ሌሎች ለመገዛት መዘጋጀት አለባቸው አለበለዚያ የአጎት ጃንግ ዕጣ የእነርሱም ይሆናል፡፡

አፋኝ ሥርዓት በሕዝባቸው ላይ የደነገጉ አገዛዞች ተመሳሳይ አካሄዶችን እንደሚከተሉ በሙያው ላይ ጥናት ያደረጉ ምሁራን ይናገራሉ፡፡ ህወሃት/ኢህአዴግ በሚገዛት ኢትዮጵያም በተመሳሳይ የሥጋ ዝምድና ያላገደው መበላላት ሲካሄድ ቆይቷል፡፡ የማርክሲስት ሌኒንስት ሊግ ትግራይ (ማሌሊት) ፈጣሪ የነበሩትና ሞት የቀደማቸው አቶ መለስም ኮሚኒስት እንደመሆናቸው በተቀናቃኞቻቸውና በወደፊት ባላንጣዎቻቸው ላይ ተመሳሳይ እርምጃ ሲወስዱ ቆተዋል፡፡(ዜናውን ከተለያዩ የዜና አውታሮች የተጠናቀረ)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. tesfaye g w says

    December 25, 2013 10:23 pm at 10:23 pm

    ሁል ግዜ ግራ የሚገባኝና የሚገርመኝ በምንም መልኩ የማይገናኝ የአገር ውስጥም ዜና ሆነ የውጭ ዜና ለምሳሌ፦ስለ ሳውዲ አረቢያ፣ስለ ሰሜን ኮርያ ፣ስለማንዴላ ሞት ፣ወዘተ,,,,,,,,ትነግሩንና ማጠቃለያው በግድ አቀራርባችሁ የኢትዮጲያን መንግስት ወይም በናንተ አጠራር (ወያኔን) ማውገዝ ነው. እውነቴን ነው የምለው አንዳንዴ ሳስበው የክርስቲያን መጽሐፍ ቅዱስ እንኲዋን ሴይጣንን ይህን ያህል የምታወግዘው አይመስለኝም .አይይይይይ በዛ በዛ በገዛ እጃችሁ ተሰለቻችሁም ታስቃላችሁም።

    Reply
  2. tesfaye g w says

    December 25, 2013 10:43 pm at 10:43 pm

    የህናንተን ሀሳብ ያልደገፈ አስተያየት ትሰርዙታላችሁ አይደል እንግዲህ ይህ ነው የእናንተ ዴሞክራሲ .ቀልደኛ በዝቷል

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule