• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ምሽት ዳንኪራ ከዲያስፖራ

September 1, 2014 11:36 pm by Editor Leave a Comment

ያለሁት ካናዳ፤ ቶሮንቶ ነው፡፡ ከጥቂት ሳምንታት ቆይታ በኋላ ትላንት ማታ አንዱ የኢትዮጵያ ምግብና ዳንኪራ ቤት ለማምሸት ከዘመድ እና ሰሞኑን ከተዋውቅኳቸው ጥቂት ሰዎች ጋር ሄድኩ፡፡

ቤቱ በአንድ ሰሞን በአንድ ዜማ እጅግ ታዋቂ ሆኖ በነበረ ወጣት ድምፃዊ የሚተዳደር ነው፡፡ ስገባ ወጣቱን ድምፃዊ አየሁት፡፡ እንግዶቹን ዞር ዞር እያለ ሰላም ይላል፡፡ ከማውቀው ወፍሯል፡፡

ዘመናዊም ባህላዊም ዘፈን በዲጄ ሲለቀቀቅ ጠባቧ ቤት ንዝረቷ ይጨምራል፡፡

ከምሽቱ አምስት ሰአት ገደማ ቤቷ ሞላች፡፡ ከሀበሻ ውጪ ሌላ ዘር ያለው ሰው ግን አላየሁም፡፡

ስድስት ሆነን ከተቀመጥንበት ጠረጴዛ ጀርባ ባለጌ ወንበርና ጠረጴዛ ላይ አንዲት በህንድ ዘዬ የተሰራ “እዩኝ እዩኝ” ሆደ- ግልብ ብልጭልጭ ልብስ የለበሰች ረጅምና ቀጭን፣ ቆንጅዬ ልጅ ተቀምጣ ቢራ ትጠጣለች፡፡ አላግባብ ተከምሮ ሳር ከጫነ መኪና ካመሳሰላት ፀጉሯ ውጪ ልቅም ያለች ቆንጆ ናት፡፡

ቆየት ብዬ ዞር እያልኩ አተኩሬ ሳያት እንደማውቃት ገባኝ፡፡ እሷም ወጣትና ታዋቂ ዘፋኝ ናት፡፡

“እዩ….ሕይወት፤ ስደትና የጠጅ ቤት አግዳሚ ሰውን እኩል ያደርጋል!” አለኝ ሰሞኑን ከተዋወቅኳቸው ኢትዮጵያዊያን አንዱ፡፡ ሰላሳ ሊሞላው ትንሽ ለቀረው አመት እዚህ ሀገር ኖሯል፡፡

“እንዴት ማለት?” ሙዚቃውን ለማሸነፍ እንጥሌ እስኪርገበገብ መጮህ አለብኝና ጮክ ብዬ ጠየኩት፡፡

“እዚህ ምታይው ሰው እኩል አይደለም፡፡ ግማሹ በሱዳን የወገኑ ሬሳ ላይ እየተረማመደ የገባ ነው፡፡ ግማሹ ደግሞ በወግ በቦሌ በአውሮፕላን የመጣ ነው፡፡ አንዳንድ ሰው የገደለም አይጠፋም…እዚህ ከገባ በኋላ ግን ሁሉም እኩል ነው….ገባሽ?”

“ገባኝ…” አልኩና እሱን ለመስማት ቀና ካልኩበት ወደ ወንበሬ ተመለስኩ፡፡

ዲጄው የትግርኛ ዘፈን ከፈተ፡፡

“ኤ….ጭ!” አለ ሌላኛው፡፡ ነገሩ ቢገባኝም “ምነው… ምን ሆንክ?” አልኩት፡፡
“እዚህም አዲሳባም ትግርኛ ብቻ!…በዛ !አሁንስ በዛ…!” ብሎ ጠረጴዛውን ትቶ ወደ አላወቅኩት ቦታ ሄደ፡፡

እሱ በሄደበት አቅጣጫ የቆመ ሌላ ሰው ሙዚቃው መከፈቱን ተከትሎ የሁለቱንም እጆቹን ባለጌ ጣቶች ሲቀስር አየሁ፡፡

ዲጄው ሰምቶና አይቷቸው “ይለይላችሁ” ብሎ ነው መሰለኝ በመሃል ሌላ ዘፈን ተጫውቶ እንዳለቀ ሌላ ትግርኛ ዘፈን ሲለቅ ቅድም የተበሳጨው ልጅ ሳቅ አለና፤ “ይሄውልሽ ሕይወት…!ላለው ይጨመርለታል ማለት ይሄ ነው!” አለና ጮህ ብሎ ሳቀ፡፡

ከግማሽ ሰአት ቆይታ በኋላ የሁሉንም ብሄር ዘፈን ስሰማ የአንዱ መረሳቱ ስለከነከነኝ፤ “ የእንትን ዘፈን ለምን አይጫወትም?” ብዬ ቅድም በትግርኛ ዘፈን መደራረብ ሲበሳጭ የነበረውን ልጅ ጠየቅኩት፡፡

“አንቺ ደግሞ እንኳን አዘፍነናቸው ጩኸታቸውን እንዲሁም አልቻልነውም!” ብሎ መለሰለኝ፡፡

ትንሽ ቆይቶ ፤ የዲጄ ሰአት አበቃና ኋላችን ተቀምጣ የነበረቸው ዘፋኝ መድረክ ወጣች፡፡

እኛን እያስገሳች “አንበሳው አገሳ”ን ስትዘፍን ቤቱ በአንድ እግሩ ቆመ፡፡

“አድማስም ማዶ እዚህም ያለን
እንደትላንቱ ዛሬም አንድ ነን… !”
ሲባል ጩኸት በረከተ፡፡

ድምፅዋ የሚያምረው ዘፋኝ፤

“ይሄም ከኦሮሞ ይሄም ከአማራ ነው፣
ይሄም ከጉራጌ ይሄም ከትግራይ ነው፣
ይሄ ሰው ከደቡብ ይሄም ከምስራቅ ነው፣
ቢለያይም ቋንቋው ደማችን አንድ ነው፣
ቢለያይም ቋንቋው ደማችን አንድ ነው!”

ስትል፤ ቅድም በትግርኛ ዘፈን ድግግሞሽ ቆሽቱ ያረረውና የእንትን ብሄር ዘፈን ለምን አይከፈትም ስለው “አንቺ ደግሞ እነሱን እንኳን አዘፍነናቸው ጩኸታቸውን እንዲሁም አልቻልነው” ያለኝ ልጅና ደጋፊዎቹ እጃቸውን ወደ ላይ አድርገው በፍፁም “ኢትዮጵያዊ” ስሜት ዳንኪራውን ሲያስነኩት አይቼ ተቃርኖው አጅግ ከነከነኝም አሳቀኝም፡፡ ባለባለጌ ጣቱም ባለጌ ጣቶቹን ደብቆ እጁን ከፍ ከፍ እያደረገ ሲዘል ተመለከትኩት፡፡

ተምታታብኝ፡፡

በዚህ የተዘባረቀ ስሜት ውስጥ ሆኜና ተምታቶብኝ ሳለሁ የጉራጊኛ ሙዚቃ ሲከፈት ጥቂት ሰዎች ቦታውን ሰፋ ሰፋ አድርገው ጭፈራውን ያደሩት ጀመር፡፡

አንደኛው በተለይ ወደር የለውም፡፡

“አንቺ እንዴት ጎበዝ ነው?!” አልኩ ወደ እህቴ ዞሬ፡፡
“በጣም…በጣም!” አለች አሱ እሱን ማየቷን ሳታቆም፡፡
“ታውቂዋለሽ?”
“በስም…”
“ማን ይባላል?”
“ገመቹ”
“ማ?”
“ገመቹ!”

በድቅድቅ ጨለማ መሃል የብርሃን ፍንጣቂ ያየሁ መሰለኝና ፈገግ አልኩ፡፡

ፈገግ እንዳልኩ ልጅቱ ዘፈኗን ጨርሳ ወደ እኛ መጣች፡፡ በ አንበሳው አገሳ ሲጨፍሩ ላብ በላብ ከሆኑት ልጆች አንዱ ጋር ጠጋ ብላ ረጅም ቁመቷን በማጎንበስ ሰብራ ኮስተር ያለ የሚመስል ነገር ታወራዋለች፡፡
የሙዚቃው ጩኸት የሚሉትን ባያሰማኝም እሱ በእሺታ ጭንቅላቱን ላይና ታች ሲነቀንቅ ይታየኛል፡፡
ልጅቱ ስትሄድ “ሰላም ነው?” ብዬ ጠየቅኩት፡፡

“አዬ! ይቺን ምስኪን ልጅ የካናዳ መንግስት ከሀገር ሊያስወጣት ነው ባክሽ…” አለኝ፡፡
“ለምን?”
“ስድስት ወር ሞልቷታል፡፡ ማክሰኞ “ኢንተርቪው” አላት፡፡ ሊመልሷት ነው”
“ እና አንተን ለምን ፈለገችህ?”
“ፎቶግራፍ አነሳ የለም?”
“እና?”
“ከዶክተር ብርሃኑ ጋር ያነሳኋትን ፎቶ እንድሰጣት ነው ምትጠይቀኝ፡፡ እሱን ካሳየቻቸው ያለምንም ችግር እንድትቀር ይፈቅዱላታል” አለኝ፡፡

ወደ ዘፋኝቱ ዞርኩና ከደቂቃዎች በፊት መድረክ ላይ በስሜት ስታወርድ የነበረውን ግጥም አሰብኩ፡፡

“በእናቴም አንድ ነኝ ፤ በአባቴም አንድ ነኝ
ከኢትዮጵያ ሀገሬ የለም የሚለየኝ”

ከረጅሙ ምሽት ደስ ያሰኘኝን የገመቹን የጉራጊኛ ዳንኪራ ብቻ እያሰብኩ ወደ ቤታችን ሄድን፡፡

(ምንጭ: ነቆራ እና ሌሎችም ወጎች ከሕይወት እምሻው ጋር – Hiwot Emishaw፡፡ፎቶ ለማሳያነት የቀረበ)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Social Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule