• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ምሽት ዳንኪራ ከዲያስፖራ

September 1, 2014 11:36 pm by Editor Leave a Comment

ያለሁት ካናዳ፤ ቶሮንቶ ነው፡፡ ከጥቂት ሳምንታት ቆይታ በኋላ ትላንት ማታ አንዱ የኢትዮጵያ ምግብና ዳንኪራ ቤት ለማምሸት ከዘመድ እና ሰሞኑን ከተዋውቅኳቸው ጥቂት ሰዎች ጋር ሄድኩ፡፡

ቤቱ በአንድ ሰሞን በአንድ ዜማ እጅግ ታዋቂ ሆኖ በነበረ ወጣት ድምፃዊ የሚተዳደር ነው፡፡ ስገባ ወጣቱን ድምፃዊ አየሁት፡፡ እንግዶቹን ዞር ዞር እያለ ሰላም ይላል፡፡ ከማውቀው ወፍሯል፡፡

ዘመናዊም ባህላዊም ዘፈን በዲጄ ሲለቀቀቅ ጠባቧ ቤት ንዝረቷ ይጨምራል፡፡

ከምሽቱ አምስት ሰአት ገደማ ቤቷ ሞላች፡፡ ከሀበሻ ውጪ ሌላ ዘር ያለው ሰው ግን አላየሁም፡፡

ስድስት ሆነን ከተቀመጥንበት ጠረጴዛ ጀርባ ባለጌ ወንበርና ጠረጴዛ ላይ አንዲት በህንድ ዘዬ የተሰራ “እዩኝ እዩኝ” ሆደ- ግልብ ብልጭልጭ ልብስ የለበሰች ረጅምና ቀጭን፣ ቆንጅዬ ልጅ ተቀምጣ ቢራ ትጠጣለች፡፡ አላግባብ ተከምሮ ሳር ከጫነ መኪና ካመሳሰላት ፀጉሯ ውጪ ልቅም ያለች ቆንጆ ናት፡፡

ቆየት ብዬ ዞር እያልኩ አተኩሬ ሳያት እንደማውቃት ገባኝ፡፡ እሷም ወጣትና ታዋቂ ዘፋኝ ናት፡፡

“እዩ….ሕይወት፤ ስደትና የጠጅ ቤት አግዳሚ ሰውን እኩል ያደርጋል!” አለኝ ሰሞኑን ከተዋወቅኳቸው ኢትዮጵያዊያን አንዱ፡፡ ሰላሳ ሊሞላው ትንሽ ለቀረው አመት እዚህ ሀገር ኖሯል፡፡

“እንዴት ማለት?” ሙዚቃውን ለማሸነፍ እንጥሌ እስኪርገበገብ መጮህ አለብኝና ጮክ ብዬ ጠየኩት፡፡

“እዚህ ምታይው ሰው እኩል አይደለም፡፡ ግማሹ በሱዳን የወገኑ ሬሳ ላይ እየተረማመደ የገባ ነው፡፡ ግማሹ ደግሞ በወግ በቦሌ በአውሮፕላን የመጣ ነው፡፡ አንዳንድ ሰው የገደለም አይጠፋም…እዚህ ከገባ በኋላ ግን ሁሉም እኩል ነው….ገባሽ?”

“ገባኝ…” አልኩና እሱን ለመስማት ቀና ካልኩበት ወደ ወንበሬ ተመለስኩ፡፡

ዲጄው የትግርኛ ዘፈን ከፈተ፡፡

“ኤ….ጭ!” አለ ሌላኛው፡፡ ነገሩ ቢገባኝም “ምነው… ምን ሆንክ?” አልኩት፡፡
“እዚህም አዲሳባም ትግርኛ ብቻ!…በዛ !አሁንስ በዛ…!” ብሎ ጠረጴዛውን ትቶ ወደ አላወቅኩት ቦታ ሄደ፡፡

እሱ በሄደበት አቅጣጫ የቆመ ሌላ ሰው ሙዚቃው መከፈቱን ተከትሎ የሁለቱንም እጆቹን ባለጌ ጣቶች ሲቀስር አየሁ፡፡

ዲጄው ሰምቶና አይቷቸው “ይለይላችሁ” ብሎ ነው መሰለኝ በመሃል ሌላ ዘፈን ተጫውቶ እንዳለቀ ሌላ ትግርኛ ዘፈን ሲለቅ ቅድም የተበሳጨው ልጅ ሳቅ አለና፤ “ይሄውልሽ ሕይወት…!ላለው ይጨመርለታል ማለት ይሄ ነው!” አለና ጮህ ብሎ ሳቀ፡፡

ከግማሽ ሰአት ቆይታ በኋላ የሁሉንም ብሄር ዘፈን ስሰማ የአንዱ መረሳቱ ስለከነከነኝ፤ “ የእንትን ዘፈን ለምን አይጫወትም?” ብዬ ቅድም በትግርኛ ዘፈን መደራረብ ሲበሳጭ የነበረውን ልጅ ጠየቅኩት፡፡

“አንቺ ደግሞ እንኳን አዘፍነናቸው ጩኸታቸውን እንዲሁም አልቻልነውም!” ብሎ መለሰለኝ፡፡

ትንሽ ቆይቶ ፤ የዲጄ ሰአት አበቃና ኋላችን ተቀምጣ የነበረቸው ዘፋኝ መድረክ ወጣች፡፡

እኛን እያስገሳች “አንበሳው አገሳ”ን ስትዘፍን ቤቱ በአንድ እግሩ ቆመ፡፡

“አድማስም ማዶ እዚህም ያለን
እንደትላንቱ ዛሬም አንድ ነን… !”
ሲባል ጩኸት በረከተ፡፡

ድምፅዋ የሚያምረው ዘፋኝ፤

“ይሄም ከኦሮሞ ይሄም ከአማራ ነው፣
ይሄም ከጉራጌ ይሄም ከትግራይ ነው፣
ይሄ ሰው ከደቡብ ይሄም ከምስራቅ ነው፣
ቢለያይም ቋንቋው ደማችን አንድ ነው፣
ቢለያይም ቋንቋው ደማችን አንድ ነው!”

ስትል፤ ቅድም በትግርኛ ዘፈን ድግግሞሽ ቆሽቱ ያረረውና የእንትን ብሄር ዘፈን ለምን አይከፈትም ስለው “አንቺ ደግሞ እነሱን እንኳን አዘፍነናቸው ጩኸታቸውን እንዲሁም አልቻልነው” ያለኝ ልጅና ደጋፊዎቹ እጃቸውን ወደ ላይ አድርገው በፍፁም “ኢትዮጵያዊ” ስሜት ዳንኪራውን ሲያስነኩት አይቼ ተቃርኖው አጅግ ከነከነኝም አሳቀኝም፡፡ ባለባለጌ ጣቱም ባለጌ ጣቶቹን ደብቆ እጁን ከፍ ከፍ እያደረገ ሲዘል ተመለከትኩት፡፡

ተምታታብኝ፡፡

በዚህ የተዘባረቀ ስሜት ውስጥ ሆኜና ተምታቶብኝ ሳለሁ የጉራጊኛ ሙዚቃ ሲከፈት ጥቂት ሰዎች ቦታውን ሰፋ ሰፋ አድርገው ጭፈራውን ያደሩት ጀመር፡፡

አንደኛው በተለይ ወደር የለውም፡፡

“አንቺ እንዴት ጎበዝ ነው?!” አልኩ ወደ እህቴ ዞሬ፡፡
“በጣም…በጣም!” አለች አሱ እሱን ማየቷን ሳታቆም፡፡
“ታውቂዋለሽ?”
“በስም…”
“ማን ይባላል?”
“ገመቹ”
“ማ?”
“ገመቹ!”

በድቅድቅ ጨለማ መሃል የብርሃን ፍንጣቂ ያየሁ መሰለኝና ፈገግ አልኩ፡፡

ፈገግ እንዳልኩ ልጅቱ ዘፈኗን ጨርሳ ወደ እኛ መጣች፡፡ በ አንበሳው አገሳ ሲጨፍሩ ላብ በላብ ከሆኑት ልጆች አንዱ ጋር ጠጋ ብላ ረጅም ቁመቷን በማጎንበስ ሰብራ ኮስተር ያለ የሚመስል ነገር ታወራዋለች፡፡
የሙዚቃው ጩኸት የሚሉትን ባያሰማኝም እሱ በእሺታ ጭንቅላቱን ላይና ታች ሲነቀንቅ ይታየኛል፡፡
ልጅቱ ስትሄድ “ሰላም ነው?” ብዬ ጠየቅኩት፡፡

“አዬ! ይቺን ምስኪን ልጅ የካናዳ መንግስት ከሀገር ሊያስወጣት ነው ባክሽ…” አለኝ፡፡
“ለምን?”
“ስድስት ወር ሞልቷታል፡፡ ማክሰኞ “ኢንተርቪው” አላት፡፡ ሊመልሷት ነው”
“ እና አንተን ለምን ፈለገችህ?”
“ፎቶግራፍ አነሳ የለም?”
“እና?”
“ከዶክተር ብርሃኑ ጋር ያነሳኋትን ፎቶ እንድሰጣት ነው ምትጠይቀኝ፡፡ እሱን ካሳየቻቸው ያለምንም ችግር እንድትቀር ይፈቅዱላታል” አለኝ፡፡

ወደ ዘፋኝቱ ዞርኩና ከደቂቃዎች በፊት መድረክ ላይ በስሜት ስታወርድ የነበረውን ግጥም አሰብኩ፡፡

“በእናቴም አንድ ነኝ ፤ በአባቴም አንድ ነኝ
ከኢትዮጵያ ሀገሬ የለም የሚለየኝ”

ከረጅሙ ምሽት ደስ ያሰኘኝን የገመቹን የጉራጊኛ ዳንኪራ ብቻ እያሰብኩ ወደ ቤታችን ሄድን፡፡

(ምንጭ: ነቆራ እና ሌሎችም ወጎች ከሕይወት እምሻው ጋር – Hiwot Emishaw፡፡ፎቶ ለማሳያነት የቀረበ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Social Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእምዬ ምኒልክ አዳራሽ October 30, 2023 10:27 am
  • የኢትዮጵያ መከላከያ መሥራች አጼ ምኒልክ መሆናቸውን ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ተናገሩ October 26, 2023 01:30 pm
  • ጥቅምት 15 ለምን? October 26, 2023 01:29 am
  • “በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት” October 26, 2023 12:57 am
  • “ውትድርና ሕይወቴ ነው” October 26, 2023 12:13 am
  • መከላከያ በሁሉም መስክ ኢትዮጵያን የሚመጥን ኃይል እየገነባ ነው October 20, 2023 05:07 pm
  • “ሁሉም ኢትዮጵያዊ ትምህርት ቤት እኩል ነው በችሎታው ነው እንጂ የሚመዘነው” ፕ/ር ብርሃኑ October 20, 2023 04:47 pm
  • 42 የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አመራሮች እና ሠራተኞች ታሰሩ October 18, 2023 04:29 pm
  • በተማሪዎች ፈተና ውጤት ለታየው ውድቀት ትምህርት ሚ/ር ኃላፊ መሆን አለበት ተባለ October 18, 2023 04:00 pm
  • ቀይ ባሕር እና ዓባይ “የኅልውና ጉዳይ ናቸው”፤ “መተንፈሻ ወደብ ያስፈልገናል” October 13, 2023 10:04 pm
  • ከ3,106 ትምህርት ቤቶች 1,328ቱ (44%) አንድም ተማሪ አላሳለፉም October 10, 2023 01:51 pm
  • “አቋጥሬ” በአማራ ክልል እያጫረሰ ነው፤ ” ኑሮውን መቋቋም አልቻልንም ” ነዋሪዎች October 10, 2023 09:07 am
  • እሸቴ አሸባሪ፤ ቲዲኤፍ/ትሕነግ “ሰማዕት” – የዘመናችን ጉድ! October 7, 2023 06:47 am
  • በወልቃይት 1.1ሚሊዮን ኩንታል ሰሊጥ ለመሰብሰብ ከ1 ሚሊዮን በላይ ሠራተኛ ይፈለጋል September 27, 2023 10:42 am
  • በአማራ ክልል ሰላም ዕጦት ከ90.5 ቢሊዮን ብር በላይ ፕሮጀክቶች ቆመዋል September 27, 2023 08:41 am
  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule