• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ምሽት ዳንኪራ ከዲያስፖራ

September 1, 2014 11:36 pm by Editor Leave a Comment

ያለሁት ካናዳ፤ ቶሮንቶ ነው፡፡ ከጥቂት ሳምንታት ቆይታ በኋላ ትላንት ማታ አንዱ የኢትዮጵያ ምግብና ዳንኪራ ቤት ለማምሸት ከዘመድ እና ሰሞኑን ከተዋውቅኳቸው ጥቂት ሰዎች ጋር ሄድኩ፡፡

ቤቱ በአንድ ሰሞን በአንድ ዜማ እጅግ ታዋቂ ሆኖ በነበረ ወጣት ድምፃዊ የሚተዳደር ነው፡፡ ስገባ ወጣቱን ድምፃዊ አየሁት፡፡ እንግዶቹን ዞር ዞር እያለ ሰላም ይላል፡፡ ከማውቀው ወፍሯል፡፡

ዘመናዊም ባህላዊም ዘፈን በዲጄ ሲለቀቀቅ ጠባቧ ቤት ንዝረቷ ይጨምራል፡፡

ከምሽቱ አምስት ሰአት ገደማ ቤቷ ሞላች፡፡ ከሀበሻ ውጪ ሌላ ዘር ያለው ሰው ግን አላየሁም፡፡

ስድስት ሆነን ከተቀመጥንበት ጠረጴዛ ጀርባ ባለጌ ወንበርና ጠረጴዛ ላይ አንዲት በህንድ ዘዬ የተሰራ “እዩኝ እዩኝ” ሆደ- ግልብ ብልጭልጭ ልብስ የለበሰች ረጅምና ቀጭን፣ ቆንጅዬ ልጅ ተቀምጣ ቢራ ትጠጣለች፡፡ አላግባብ ተከምሮ ሳር ከጫነ መኪና ካመሳሰላት ፀጉሯ ውጪ ልቅም ያለች ቆንጆ ናት፡፡

ቆየት ብዬ ዞር እያልኩ አተኩሬ ሳያት እንደማውቃት ገባኝ፡፡ እሷም ወጣትና ታዋቂ ዘፋኝ ናት፡፡

“እዩ….ሕይወት፤ ስደትና የጠጅ ቤት አግዳሚ ሰውን እኩል ያደርጋል!” አለኝ ሰሞኑን ከተዋወቅኳቸው ኢትዮጵያዊያን አንዱ፡፡ ሰላሳ ሊሞላው ትንሽ ለቀረው አመት እዚህ ሀገር ኖሯል፡፡

“እንዴት ማለት?” ሙዚቃውን ለማሸነፍ እንጥሌ እስኪርገበገብ መጮህ አለብኝና ጮክ ብዬ ጠየኩት፡፡

“እዚህ ምታይው ሰው እኩል አይደለም፡፡ ግማሹ በሱዳን የወገኑ ሬሳ ላይ እየተረማመደ የገባ ነው፡፡ ግማሹ ደግሞ በወግ በቦሌ በአውሮፕላን የመጣ ነው፡፡ አንዳንድ ሰው የገደለም አይጠፋም…እዚህ ከገባ በኋላ ግን ሁሉም እኩል ነው….ገባሽ?”

“ገባኝ…” አልኩና እሱን ለመስማት ቀና ካልኩበት ወደ ወንበሬ ተመለስኩ፡፡

ዲጄው የትግርኛ ዘፈን ከፈተ፡፡

“ኤ….ጭ!” አለ ሌላኛው፡፡ ነገሩ ቢገባኝም “ምነው… ምን ሆንክ?” አልኩት፡፡
“እዚህም አዲሳባም ትግርኛ ብቻ!…በዛ !አሁንስ በዛ…!” ብሎ ጠረጴዛውን ትቶ ወደ አላወቅኩት ቦታ ሄደ፡፡

እሱ በሄደበት አቅጣጫ የቆመ ሌላ ሰው ሙዚቃው መከፈቱን ተከትሎ የሁለቱንም እጆቹን ባለጌ ጣቶች ሲቀስር አየሁ፡፡

ዲጄው ሰምቶና አይቷቸው “ይለይላችሁ” ብሎ ነው መሰለኝ በመሃል ሌላ ዘፈን ተጫውቶ እንዳለቀ ሌላ ትግርኛ ዘፈን ሲለቅ ቅድም የተበሳጨው ልጅ ሳቅ አለና፤ “ይሄውልሽ ሕይወት…!ላለው ይጨመርለታል ማለት ይሄ ነው!” አለና ጮህ ብሎ ሳቀ፡፡

ከግማሽ ሰአት ቆይታ በኋላ የሁሉንም ብሄር ዘፈን ስሰማ የአንዱ መረሳቱ ስለከነከነኝ፤ “ የእንትን ዘፈን ለምን አይጫወትም?” ብዬ ቅድም በትግርኛ ዘፈን መደራረብ ሲበሳጭ የነበረውን ልጅ ጠየቅኩት፡፡

“አንቺ ደግሞ እንኳን አዘፍነናቸው ጩኸታቸውን እንዲሁም አልቻልነውም!” ብሎ መለሰለኝ፡፡

ትንሽ ቆይቶ ፤ የዲጄ ሰአት አበቃና ኋላችን ተቀምጣ የነበረቸው ዘፋኝ መድረክ ወጣች፡፡

እኛን እያስገሳች “አንበሳው አገሳ”ን ስትዘፍን ቤቱ በአንድ እግሩ ቆመ፡፡

“አድማስም ማዶ እዚህም ያለን
እንደትላንቱ ዛሬም አንድ ነን… !”
ሲባል ጩኸት በረከተ፡፡

ድምፅዋ የሚያምረው ዘፋኝ፤

“ይሄም ከኦሮሞ ይሄም ከአማራ ነው፣
ይሄም ከጉራጌ ይሄም ከትግራይ ነው፣
ይሄ ሰው ከደቡብ ይሄም ከምስራቅ ነው፣
ቢለያይም ቋንቋው ደማችን አንድ ነው፣
ቢለያይም ቋንቋው ደማችን አንድ ነው!”

ስትል፤ ቅድም በትግርኛ ዘፈን ድግግሞሽ ቆሽቱ ያረረውና የእንትን ብሄር ዘፈን ለምን አይከፈትም ስለው “አንቺ ደግሞ እነሱን እንኳን አዘፍነናቸው ጩኸታቸውን እንዲሁም አልቻልነው” ያለኝ ልጅና ደጋፊዎቹ እጃቸውን ወደ ላይ አድርገው በፍፁም “ኢትዮጵያዊ” ስሜት ዳንኪራውን ሲያስነኩት አይቼ ተቃርኖው አጅግ ከነከነኝም አሳቀኝም፡፡ ባለባለጌ ጣቱም ባለጌ ጣቶቹን ደብቆ እጁን ከፍ ከፍ እያደረገ ሲዘል ተመለከትኩት፡፡

ተምታታብኝ፡፡

በዚህ የተዘባረቀ ስሜት ውስጥ ሆኜና ተምታቶብኝ ሳለሁ የጉራጊኛ ሙዚቃ ሲከፈት ጥቂት ሰዎች ቦታውን ሰፋ ሰፋ አድርገው ጭፈራውን ያደሩት ጀመር፡፡

አንደኛው በተለይ ወደር የለውም፡፡

“አንቺ እንዴት ጎበዝ ነው?!” አልኩ ወደ እህቴ ዞሬ፡፡
“በጣም…በጣም!” አለች አሱ እሱን ማየቷን ሳታቆም፡፡
“ታውቂዋለሽ?”
“በስም…”
“ማን ይባላል?”
“ገመቹ”
“ማ?”
“ገመቹ!”

በድቅድቅ ጨለማ መሃል የብርሃን ፍንጣቂ ያየሁ መሰለኝና ፈገግ አልኩ፡፡

ፈገግ እንዳልኩ ልጅቱ ዘፈኗን ጨርሳ ወደ እኛ መጣች፡፡ በ አንበሳው አገሳ ሲጨፍሩ ላብ በላብ ከሆኑት ልጆች አንዱ ጋር ጠጋ ብላ ረጅም ቁመቷን በማጎንበስ ሰብራ ኮስተር ያለ የሚመስል ነገር ታወራዋለች፡፡
የሙዚቃው ጩኸት የሚሉትን ባያሰማኝም እሱ በእሺታ ጭንቅላቱን ላይና ታች ሲነቀንቅ ይታየኛል፡፡
ልጅቱ ስትሄድ “ሰላም ነው?” ብዬ ጠየቅኩት፡፡

“አዬ! ይቺን ምስኪን ልጅ የካናዳ መንግስት ከሀገር ሊያስወጣት ነው ባክሽ…” አለኝ፡፡
“ለምን?”
“ስድስት ወር ሞልቷታል፡፡ ማክሰኞ “ኢንተርቪው” አላት፡፡ ሊመልሷት ነው”
“ እና አንተን ለምን ፈለገችህ?”
“ፎቶግራፍ አነሳ የለም?”
“እና?”
“ከዶክተር ብርሃኑ ጋር ያነሳኋትን ፎቶ እንድሰጣት ነው ምትጠይቀኝ፡፡ እሱን ካሳየቻቸው ያለምንም ችግር እንድትቀር ይፈቅዱላታል” አለኝ፡፡

ወደ ዘፋኝቱ ዞርኩና ከደቂቃዎች በፊት መድረክ ላይ በስሜት ስታወርድ የነበረውን ግጥም አሰብኩ፡፡

“በእናቴም አንድ ነኝ ፤ በአባቴም አንድ ነኝ
ከኢትዮጵያ ሀገሬ የለም የሚለየኝ”

ከረጅሙ ምሽት ደስ ያሰኘኝን የገመቹን የጉራጊኛ ዳንኪራ ብቻ እያሰብኩ ወደ ቤታችን ሄድን፡፡

(ምንጭ: ነቆራ እና ሌሎችም ወጎች ከሕይወት እምሻው ጋር – Hiwot Emishaw፡፡ፎቶ ለማሳያነት የቀረበ)

Filed Under: Social Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
Copyright © 2026 · Goolgule