• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ግብረሰዶማውያን ከተፈጥሮ ውጪና አጸያፊ ናቸው”

February 25, 2014 10:08 am by Editor 9 Comments

የዑጋንዳው ፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቪኒ “አከራካሪ” ሲባል የቆየውን የጸረ ግብረሰዶማዊ ህግ በፊርማቸው አጸደቁ፡፡ ግብረሰዶማውያንን “ከተፈጥሮ ውጪ የሆኑ” እና “አጸያፊ” ሲሉ ገልጸዋቸዋል፡፡ ግብረሰዶማዊነት በምዕራቡ ዓለም አማካኝነት ወደ አፍሪካ እየተስፋፋ የመጣ ነው ብለዋል፡፡

ለበርካታ ዓመታት አከራካሪ ሆኖ የቆየውን የጸረ ግብረሰዶማዊነት ሕግ ትላንት ዑጋንዳ አጽድቃለች፡፡ ከምዕራቡ ዓለም እና ሰዶማዊነት የመብት ጉዳይ እንደሆነ ከሚከራከሩ ተቋማት የደረሰባትን ውትወታ ወደ ጎን በማለት ዑጋንዳ በሕግ ማጽደቋ የበርካታ ዓለምአቀፍ መገናኛ ብዙሃንን ሽፋን የሰጡበት ርዕስ ሆኗል፡፡ የሕጉን መጽደቅ አስመልክቶ ጥቂት ዑጋንዳውያን ተቃውሞ ሰልፍ የወጡ ሲሆን በርካታዎች ደግሞ ድጋፋቸውን ለፕሬዚዳንቱ ገልጸዋል፡፡

uganda 1ሕጉን በፊርማቸው ያጸደቁት ዩዌሪ ሙሴቪኒ ሲኤንኤን ላይ ለቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱ ግብረሰዶማውያን “አጸያፊ ሰዎች ናቸው፤ ምን ዓይነት ድርጊት ይፈጽሙ እንደሆነ አላውቅም ነበር፤ በቅርቡ የሰማሁት ግን በጣም አስደንጋጭ ነው፤ ጸያፍ ነው” ብለዋል፡፡ ፕሬዚዳንቱ ሲቀጥሉም ሰዶማውያን ሲወለዱ ጀምሮ እንደዚሁ ናቸው ስለተባለ ሁኔታውን እውነት አድርገው በመውሰድ ቸል ሊሉት እንደነበር ሆኖም ግን እስካሁን ምንም ሳይንሳዊ ማስረጃ እንዳልቀረበበት ተናግረዋል፡፡

ሙሴቪኒ ሕጉን እንዲያጸድቁ ያደረጋቸውን አንዱን ምክንያት ሲጠቅሱም፤ ግብረሰዶማዊነት ከጄኔቲክስ ጋር በተያያዘ ከውልደት ጀምሮ የሚመጣ የተፈጥሮ ጉዳይ ነው በማለት ይገምቱ እንደነበር ሆኖም የአገራቸው ሳይንቲስቶች ይህንን መከራከሪያ ውድቅ ማድረጋቸውን ጨምረው ገልጸዋል፡፡

ሕጉ በፕሬዚዳንቱ ፊርማ ከጸደቀ በኋላ ወዲያውኑ በሥራ ላይ የዋለ ሲሆን ግብረሰዶማዊ ወሲብ ሲፈጽም የተገኘ ማንኛውም ሰው እስከ ዕድሜ ይፍታህ በሚደርስ እስራት እንደሚቀጣ ይደነግጋል፡፡ በወንጀሉ ለመጀመሪያ ጊዜ የተገኘ በ14ዓመት እስር ይቀጣል፡፡ በተደጋጋሚ ወንጀሉን ሲፈጽሙ የተገኙ፣ ዕድሜያቸው ካልደረሱ ጋር እንዲሁም ከአካለ ስንኩል ወይም ከኤችአይቪ ተጠቂ ጋር ወንጀሉን የፈጸሙ በዕድሜ ልክ እስራት እንዲቀጡ ሕጉ ያዛል፡፡

ናይጄሪያም ከአንድ ወር በፊት ተመሳሳይ ሕግ ያወጣች ሲሆን የዑጋንዳው ሕግ በረቂቅነት ከወጣ የዛሬ አራት ዓመት ጀምሮ ምዕራባውያን ከፍተኛ ተጽዕኖ በማድረግ ሕጉ ተግባራዊ እንዳይሆን፤ ከሆነም በአብዛኛው የህጉ ክፍል እንዲሸራረፍ በርካታ ሙከራዎችን፣ ማስፈራሪያዎችንና ውስወሳዎችን ሲያካሂዱ ቆይተዋል፡፡no homosexual

በአሜሪካ የፕሬዚዳንት ኦባማ አፈቀላጤ የህጉን መጽደቅ “አጸያፊ” ሲሉ ገልጸውታል፡፡ ዑጋንዳ ባስቸኳይ ሕጉን እንድትሰርዝ የጠየቁ ሲሆን አሜሪካ ከዑጋንዳ ጋር ያላትን ግንኙነት እንደገና እንደምታጤነውም ተናግረዋል፡፡ አውሮጳውያንም በበኩላቸው የሕጉን መጽደቅ የኮነኑ ሲሆን የተወሰኑ የአውሮጳ አገራት ለዑጋንዳ የሚሰጡትን ዕርዳታ እንደሚያቋርጡ ዝተዋል፡፡ ሌሎች አገራት ግን እንዲህ ዓይነቱ የዕርዳታ ማቋረጥ ውሳኔ ዑጋንዳውያንን የሚጎዳ በመሆኑ እርምጃው መወሰድ የለበትም ይላሉ፡፡

የዑጋንዳ ሕግ አውጪዎች ያረቀቁትን ሕግ በፈረሙበት ጊዜ ሙሴቪኒ እንዳሉት ምዕራባውያን በዑጋንዳ ጉዳይ በግልጽ ጣልቃ እየገቡ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ “አፍሪካውያን በሌሎች ላይ የራሳችንን አመለካከት አንጭንም” ያሉት ሙሴቪኒ ምዕራባውያን እስካሁን ያደረጉት ጣልቃገብነት ትክክለኛ እንዳልነበረ እና ይህም ደግሞ “ማኅበራዊ ኢምፔሪያዝም” ነው ሲሉ ኮንነውታል፡፡ ግትርና ግዴለሽ ምዕራባዊ ድርጅቶች የራሳቸውን አጀንዳ ለማስፋፋት እየጣሩ መሆናቸውንና ለዚህም ሰዶማዊነት ተግባር የኡጋንዳን ህጻናት እየደለሉ ወደ ግብረሰዶማዊነት ወንጀል እንደሚያስገቧቸው ከሰዋል፡፡ በምዕራቡ ዓለም ያሉ ሰዶማውያን ደሃ ዑጋንዳውያንን ዒላማቸው በማድረግ በገንዘብ በመደለል ለግብረሰዶማዊነት እንደሚጋብዟቸውና ቀጥሎም ለግብረሰዶማዊ አዳሪነት እንደሚዳርጓቸው ሙሴቪኒ ተናግረዋል፡፡

የዑጋንዳን ውሳኔ አስመልክቶ የማኅበራዊ ጉዳይ ባለሙያ የሆኑ በፌስቡክ በኩል ለጎልጉል በሰጡት አስተያየት “ኢህአዴግም ከየምዕራቡ ለሚለቃቅመው ዕርዳታ ብሎ የአገርን ባህልና ማኅበራዊ እሴት ከሚያጠፋ ይልቅ ተመሳሳይ ተግባር ሊወስድ ይገባዋል፤ የተቃወመውን ሁሉ “አሸባሪ” በማለት በጸረ አሸባሪ ህግ ስቃዩን ከሚያሳይ የጸረ ግብረሰዶማዊ ህግ በማውጣት ይህንን በአገራችን በፍጥነት እየተስፋፋ ያለውን ወረርሽኝ መላ ሊለው ይገባል” ብለዋል፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. sara says

    February 26, 2014 12:34 am at 12:34 am

    I am so happy when i read god blessed you Uganda, the lord hands be With Uganda
    Ppl and With this greatest leader,

    Reply
  2. andnet berhane says

    February 26, 2014 07:01 am at 7:01 am

    በግብረ ሶዶማውያን ወይም የዚህ ወረርሽኝ አስፋፊዎች የተወሰደው የህግ ረቂቅ አስፈላጊነቱ እንደ ሃገር ገደብና ተግባሩ ትክክል አለመሆኑን ለሕብረተሰቡ ሕጋዊ ጥንቃቄ መስጠት በፈጣሪም ትእዛዝ (በመጽሐፍ ቅድሱ ውስጥም ) በመተላለፍ ቅጣት ተደርጓል ስለዚህም የኡጋንዳ መንግስት ያስተላለፈው ያጸደቀው ውሳኔ ሰባዊ መብትን የሚጻረር ባለመሆኑ እንደ ግለሰብ እደግፋለሁ፡ ነገርግን ለሚደረገው ምንኝውም ቅጣት እርምጃ ከተግባሩ እሚታቀብበት የሕክምና የስነአይምሮ የሃይማኖት እርዳታ በመድረግ ተፈላጊው እንክብካቤና ምክር በመስጠት እንዲረዱ እንጂ እስርቤት በበለጠ የከፋና የተዛመተ አደርገዋል የሃገሪቱን ምጣኔ ሃብትም ለድነዚህ ያለ አሳፋሪ ተፈጥራዊና ባህላዊ ከማጥፋት በዚህ ተግባር የተሰማሩ ወይም የተለከፉ ወገኞች በተማሩትና ባላቸው ሞያ ሀገርና ሕብረተሰቡን በመርዳት የሚችሉበት ከበሽታው እሚፈወስበት መንገድ ይፈጠር እላለሁ፡ ማሰር መፍትሄ የለውም ። በጣም ከሚገርመው ጉዳይ በዚህ ሕግ ላይ የአሜሪካው ጆን ኬሪ የሰጡት መግለጫ ይህ ሕግ ለኡጋንዳውያን አሳሻኝ ነው ሰባዊ መብትም መጣስ ነው ሲሉ ድጎማውም እንዲቋረጥ ሲሉም ተሰምተዋል፡ ያሳዝናል በኢትዮጵያ ሕዝብና ሀገር እየተፈጸመያለውን የመብት ጥሰት የፍትህ መጓደል ያለውን እምባ ገነን ሰርዓት ለመኮነን በየትኛውም መድረክ ድምጻቸው አልተሰማም ይህ ጉዳይ አሜሪካንን በውጭ አለም ያላትን አቋም ፍንትው አርጎ የሚያሳይ በዓለም ሕብረተሰብ ውስጥ በሃገራቸው የተሰራፋውን ባሕልና የእምነት መዛባት በሌላው ለማሰራጨት ግብረ ሰደማውያንን መደገፍና ከሰባዊ ረገጣ ማገናኘት ያስተዛዝባል፡ ይህ ጉዳይ ተፈጥራዊ ሳይሆን በራስ አለመተማመን የሚመጣ እንጂ ፈጣሪያችን ሁሉንም አስተካክሎ ለሁሉም ፍጥረቶች አድሏል፡ በፍላጎቱ መሆን የሚፈልግ የግል ውሳኔው ስለሆነ ተቃውሞ የለኝም ነገር ግን ሕግን መጣስ አልደግፍም፡ የወጣው ሕግ መተግበር ይገባል የረጅም ጊዜ እስራት የሚለው ተገቢነት የለውም መሻሻል ያስፈልጋል፡ ወያኔ የሀገሪቱን ባህልና ልምድ ለማኮላሸት ግብረሰዶማውያን ተቀብሎ በኢትዮጵያ ስብሰባ አድርጓል ተቃዋሚዎችን አስሯል ደብድቧል ይህንንም በግልጽ እንደተቀበልው የተረዱት ሞሶቬኒ በግልጽ ተናግረውታል፡

    Reply
  3. bella says

    February 26, 2014 11:48 am at 11:48 am

    tnx god this should also happen everywhere and our country

    Reply
  4. Tewodros says

    February 26, 2014 03:05 pm at 3:05 pm

    ይህ በሃገራችን ከአጸያፊም አልፎ ከህብረተሰቡም ገለልተኛ የሚያደርግ ነዉ ወሬዉን ስትሰማ እንኴን ይሰቀጥጣል ሴት ወይም ወንድ ባልጠፋበት ይህን ተግባር መፈጸም ለጆሮም ይሰቀጥጣል በፈጣሪም ትእዛዝ(በመጽሐፍ ቅድሱ ውስጥም ) በመተላለፍ ቅጣት ተደርጓል እስኪ ከታች የተጻፈዉን እነሱ የሚሉትን እንኴን በማንበብ ብቻ ምን ያሀል እንደሚያስጠላ
    በአሜሪካ የፕሬዚዳንት ኦባማ አፈቀላጤ የህጉን መጽደቅ “አጸያፊ” ሲሉ ገልጸውታል ዑጋንዳ ባስቸኳይ ሕጉን እንድትሰርዝ የጠየቁ ሲሆን አሜሪካ ከዑጋንዳ ጋር ያላትን ግንኙነት እንደገና እንደምታጤነውም ተናግረዋል፡፡ አውሮጳውያንም በበኩላቸው የሕጉን መጽደቅ የኮነኑ ሲሆን የተወሰኑ የአውሮጳ አገራት ለዑጋንዳ የሚሰጡትን ዕርዳታ እንደሚያቋርጡ ዝተዋል
    በበኩሌ አሳፋሪ ሆኖ አግኝቸዋለሁ በመጨረሻም አገራችንም የዑጋንዳን ፈለግ መከተል እንዳለባት አምናለሁ

    Reply
  5. ሰላም says

    February 26, 2014 05:55 pm at 5:55 pm

    ጎልጉሎች፣ ይህን ጉዳይ ማቅረባችሁ ያስመሰግናችኋል። ከታች ያለውን አግኝቼ ላክሁላችሁ። በደህና ቆዩ።
    http://ethiopianchurch.org/en/editorial2/102-%E1%8B%A8%E1%88%B5%E1%8A%90-%E1%88%9D%E1%8C%8D%E1%89%A3%E1%88%AD-%E1%8A%A5%E1%88%B4%E1%89%B6%E1%89%BD.html#disqus_thread

    Reply
  6. Solomon says

    February 27, 2014 05:07 pm at 5:07 pm

    የሞራል ዝቅጠትን እንታገል፡፡ እነኝህ ሰዎች የአለምን ህዝብ ማዝቀጥና እንደእንሰሳ መግዛት የሚፈልጉ ናቸው፡፡

    Reply
  7. MASRESHA says

    March 5, 2014 11:48 pm at 11:48 pm

    የእኛስ መሪዎች የሃይማኖት አባቶችና የፖለቲካ መሪዎች መንግሥት ምን ይላሉ? ትውልድ እያበላሸ ያለውን ይህንን ተግባር በአደባባይ ሊዋጉት ይገባል፡፡ ድህነት ሰዶማዊነትን በመቀበል ወይም በማስተናገድ አይጠፋም ይከፋል እንጂ፡፡

    Reply
  8. Zemen says

    March 6, 2014 08:53 pm at 8:53 pm

    “አላየሁም : አልሰማሁም : አልናገርም” የሚል ወግ አጥባቂ ባህል ውስጥ አየኖርን የህን ጉዳይ አንደ አንድ ተዓኣምር አድርገን ማውራት መጀመራችን ያስቀኛል፥፥ ወደድንም ጠላነም ለተመሳሳያ ጾታ ፈላጎት ያላቸው ሰወች በአግራችን ከድሮም ነበሩ ፥ አሁንም አሉ ፥ ወደፊትም ይኖራሉ፥፥ ለዚህ በቂ ማስረጃው “ሚስቱ ናቀችው” “ሚስቱ ከጎረቤት ወለደች” “ሴታሴት ወንድ” “ወንዳወንድ ሴት” “ፍናፍንት” አና መሰል አባባሎች ሞኝ አይዎራም በሚል ዘይቤ ታፍነው ሰሜቱም ያላቸው በባህል በሃይማኖት ሰበብ የውስጣቸውን አፍነው ለአመታት ይኖራሉ ። ትልቁ ጥያቄ “ለምን አንደዚህ ሆኑ?” የሄም ጥፍት ከሆነ መስተካከል የሚችልም ነገር ከሆነ በምን መልኩ ልንረዳቸው አንችላለን ብሎ በመጠየቅ የመጽሃፍ ቀዱሰንና ሌሎች የሃይመኖት መጽሃፎች በማጣቀስ ያገደሉ ያታሰሩ ማለት ምን ያህል አርቆ ማሰብ ማስተዋል የተሳነን ጫካ ውስጥ አንደሚኖር ያልሰለጠነ ማህበረሰብ ሰበዓዊነት የጎደለን ሑዋላ ቀር መሆናችንን ያሳያል::

    ሲጀመር ሲጀመር የሄን ጉዳይ ሆን በሎ መንግስት ያቀናበረው ካሉት ማህበረሰባዊ ፥ ኢኮኖሚያዊ ጥያቀዎች መመለሰ ባለመቻሉና ለቀጣዩ መርጫ ተፈቃሪ መስሎ ለመቅረብ የጠነሰሰው ሴራ ነው አንጂ አሁን ማን የሙት የሄ ጉዳይ በሃገራችን አንዲህ ጉድ ሆኖ ከኑሮዋችን የሚያሰናክለን ተልቅ ጥያቄ ነው?? አይደለም። ችግር ያለባቸውን በቁጥር አዚህ ገቡ የማይባሉ አቅም የሌላቸውን ሚስኪን ወጣቶችን መርጦ አንዲህ ያለ የጥላቻ ዘመቻ ማካሄድ ሀሊና ካለው ሰው የሚጠበቅ ነው?? በበኩሌ አንደዚህ ያሉን ሰዎች የሰነ-ልቦና መክር መስጠት : ፍቅር ማሳየት አና ወደባሰ የብችኝነትና ራስን የመጉዳት አዝቅት ሳይገቡ መርዳት አንጂ አንደ ወደቀ ዛፍ ምሳር አብዝቶ የራሴን ወንድም አና አህቶች መግደል አልፈልገም ::

    Reply
  9. gizachew says

    March 11, 2014 04:12 pm at 4:12 pm

    this is realy immoral every body must fight against this

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule