• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ለየካቲት ፲፪ ቀን ፲፱፻፳፱ ዓ.ም. ሠማዕታት ቋሚ ጠበቃ መሆን የሁሉም ኢትዮጵያዊ ግዴታ ነው

February 20, 2016 11:10 am by Editor Leave a Comment

«ከታሪክ የማይማሩ ደግመው፣ ደጋግመው ለመሣሣት ይጋለጣሉ፤» የሚለው ብሂል ለዚህ ብሔራዊ በዓል መደብዘዝ አብይ ማጣቀሻ ነው። በደርግ የአገዛዝ ዘመን ይህ ዕለት ከብሔራዊ በዓልነት ደረጃ ወርዶ በመታሠቢያ ቀን ደረጃ እንዲከበር መደረጉ ትልቅ ታሪካዊ ስህተት ነበር። በትግሬ-ወያኔ አገዛዝ ይብስ ስህተቱ ወደማይታረምበት ደረጃ ደርሷል። ይህንን ለማለት የሚያስደፍረው የትግሬ-ወያኔ አገዛዝ ፋሽስት ኢጣሊያን ሲፋለሙ በሠማዕትነት ያለፉትን የአቡነ ጴጥሮስን፣ የደጃዝማጅ አፈወርቅ ወልደሰማዕትን እና ከሁሉም በላይ የማይጨው አርበኞቻችንን የመታሠቢያ ኃውልቶች አፍርሷል፣ ሌሎችንም ታሪካዊ ኃውልቶች አፍርሶ ድራሻቸውን ለማጥፋት እንቅስቃሴውን ቀጥሏል። ችግሩ የሰማዕታቱ መታሠቢያ የሆኑት ኃውልቶችን በማፍረስ ብቻ የሚገደብ አልሆነም፣ እንዲያውም ታሪካዊቱን አገር ኢትዮጵያን እስከመበታተን የሚደርስ ታላቅ ብሔራዊ ክህደት የሚፈጸመበት የታሪክ ወቅት ላይ እንገኛለን። ይህ ታሪካዊ ክህደት ከአሁኑ ትውልድ ተሻግሮ የተተኪው ትውልድም ማፈሪያ እንዳይሆን ጊዜው ሣይመሽ ዛሬውኑ ለተግባራዊ እርምጃ መነሣት ይኖርብናል።

ኢትዮጵያ እና ዜጎቿ በዚህ የታሪክ ማጥ ውስጥ ሲዳክሩ፣ በፋሽስት ኢጣሊያ ለተጨፈጨፉት ሠማዕታት ቋሚ ጠበቃ ሆኖ የቆመው “Global Alliance for Justice: The Ethiopian Cause” በመባል የሚታወቀው ተቋም ነው። ይህ ተቋም ከተመሠረተበት ጊዜ አንስቶ ለሠማዕቶቻችን ቀዳሚ ጠበቃ ነው ቢባል ማጋነን አይደለም። ሆኖም የሌሎቻችን ኢትዮጵያውያን ድጋፍ ግን እዚህ ግባ የሚባል አይደለም። ያጋጠመንን ብሔራዊ ፈተና በአሸናፊነት ለመወጣት፣ ከእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ዜጋ ጀምሮ በኢትዮጵያዊነት ስም እስከከተደራጁት ሁሉም ዓይነት ድርጅቶች እና ተቋሞች ከፍተኛ የሆነ ብሔራዊ አስተዋፅዖ ይጠበቃል። ስለሆነም ሠማዕቶቻችንን ከመዘከር ባሻገር ብሔራዊ ግዴታችንን ለመወጣት ሁላችንም በያለንበት የድርሻችንን መወጣት ይገባናል። የሺህ ኪሎሜትሮች ጉዞ የሚጀመረው በአንድ እርምጃ ነውና ይህንን ታሪካዊ ዕለት ኢትዮጵያውያን በያለንበት ከብሔራዊ በዓሎቻችን አንዱ አድርገን እንድናከብረው ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት የአደራ ጥሪውን ያቀርባል።

ለሠማዕታት ተገቢውን ክብር እንስጥ!

ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule