• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ለየካቲት ፲፪ ቀን ፲፱፻፳፱ ዓ.ም. ሠማዕታት ቋሚ ጠበቃ መሆን የሁሉም ኢትዮጵያዊ ግዴታ ነው

February 20, 2016 11:10 am by Editor Leave a Comment

«ከታሪክ የማይማሩ ደግመው፣ ደጋግመው ለመሣሣት ይጋለጣሉ፤» የሚለው ብሂል ለዚህ ብሔራዊ በዓል መደብዘዝ አብይ ማጣቀሻ ነው። በደርግ የአገዛዝ ዘመን ይህ ዕለት ከብሔራዊ በዓልነት ደረጃ ወርዶ በመታሠቢያ ቀን ደረጃ እንዲከበር መደረጉ ትልቅ ታሪካዊ ስህተት ነበር። በትግሬ-ወያኔ አገዛዝ ይብስ ስህተቱ ወደማይታረምበት ደረጃ ደርሷል። ይህንን ለማለት የሚያስደፍረው የትግሬ-ወያኔ አገዛዝ ፋሽስት ኢጣሊያን ሲፋለሙ በሠማዕትነት ያለፉትን የአቡነ ጴጥሮስን፣ የደጃዝማጅ አፈወርቅ ወልደሰማዕትን እና ከሁሉም በላይ የማይጨው አርበኞቻችንን የመታሠቢያ ኃውልቶች አፍርሷል፣ ሌሎችንም ታሪካዊ ኃውልቶች አፍርሶ ድራሻቸውን ለማጥፋት እንቅስቃሴውን ቀጥሏል። ችግሩ የሰማዕታቱ መታሠቢያ የሆኑት ኃውልቶችን በማፍረስ ብቻ የሚገደብ አልሆነም፣ እንዲያውም ታሪካዊቱን አገር ኢትዮጵያን እስከመበታተን የሚደርስ ታላቅ ብሔራዊ ክህደት የሚፈጸመበት የታሪክ ወቅት ላይ እንገኛለን። ይህ ታሪካዊ ክህደት ከአሁኑ ትውልድ ተሻግሮ የተተኪው ትውልድም ማፈሪያ እንዳይሆን ጊዜው ሣይመሽ ዛሬውኑ ለተግባራዊ እርምጃ መነሣት ይኖርብናል።

ኢትዮጵያ እና ዜጎቿ በዚህ የታሪክ ማጥ ውስጥ ሲዳክሩ፣ በፋሽስት ኢጣሊያ ለተጨፈጨፉት ሠማዕታት ቋሚ ጠበቃ ሆኖ የቆመው “Global Alliance for Justice: The Ethiopian Cause” በመባል የሚታወቀው ተቋም ነው። ይህ ተቋም ከተመሠረተበት ጊዜ አንስቶ ለሠማዕቶቻችን ቀዳሚ ጠበቃ ነው ቢባል ማጋነን አይደለም። ሆኖም የሌሎቻችን ኢትዮጵያውያን ድጋፍ ግን እዚህ ግባ የሚባል አይደለም። ያጋጠመንን ብሔራዊ ፈተና በአሸናፊነት ለመወጣት፣ ከእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ዜጋ ጀምሮ በኢትዮጵያዊነት ስም እስከከተደራጁት ሁሉም ዓይነት ድርጅቶች እና ተቋሞች ከፍተኛ የሆነ ብሔራዊ አስተዋፅዖ ይጠበቃል። ስለሆነም ሠማዕቶቻችንን ከመዘከር ባሻገር ብሔራዊ ግዴታችንን ለመወጣት ሁላችንም በያለንበት የድርሻችንን መወጣት ይገባናል። የሺህ ኪሎሜትሮች ጉዞ የሚጀመረው በአንድ እርምጃ ነውና ይህንን ታሪካዊ ዕለት ኢትዮጵያውያን በያለንበት ከብሔራዊ በዓሎቻችን አንዱ አድርገን እንድናከብረው ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት የአደራ ጥሪውን ያቀርባል።

ለሠማዕታት ተገቢውን ክብር እንስጥ!

ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am
  • ከያቤሎ አዲስ አበባ የተላከ ኮንትሮባንድ ጉለሌ ተያዘ September 7, 2023 01:40 pm
  • “እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መሻገር አቅቶናል” September 7, 2023 01:31 am
  • ራሱን መሪ አልባ የሚያደርገው አማራ ክልል August 24, 2023 11:50 pm
  • ጀብደኛው August 24, 2023 10:06 am
  • ጎንደርና ባሕር ዳር ከተሞች ወደ ቀድሞ ሰላማቸው ተመልሰዋል August 13, 2023 10:55 pm
  • ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያውን ግዙፍ ወታደራዊ ኃይል አስመረቀች August 13, 2023 10:26 pm
  • ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ August 13, 2023 09:11 pm
  • ወደ ኤርትራ በኮንትሮባንድ የሚሻገሩ ቆሳቁሶች እየተያዙ ነው August 11, 2023 12:52 pm
  • የአማራ ክልል ትልልቅ ከተሞች ተኩስ ዓልባ ሆነው ውለዋል August 10, 2023 04:31 pm
  • “አንድ ሰው ለመግደል ኅንፃውን ማቃጠል” የኢ-ዲሞክራሲና ጽንፈኛ ኃይሎች ቅዠት፤ (ክፍል ሁለት) August 10, 2023 09:44 am
  • “አርበኛ” መሳይ – “የድል ዜና” ሳይበርድ 50ሺህ ዶላር በጎፈንድሚ August 10, 2023 09:08 am
  • በሕዝቡ ድጋፍ ከተሞች ከዘራፊው መንጋ ሥጋት ነጻ መሆናቸው ይፋ ሆነ August 9, 2023 11:47 am
  • ትህነግ አራተኛውን ሞት ሞተ  August 8, 2023 05:47 pm
  • “ሃሳብ ሲነጥፍ ነፍጥ አንግቤ እዋጋለሁ” የሚሉ አካላት ላይ እርምጃ ይወሰዳል – የመከላከያ ሠራዊት August 1, 2023 09:25 am
  • ደቡብ አፍሪካ የመሸጉ ወንጀለኞች ለሕግ ተላልፈው ሊሰጡ ነው July 31, 2023 09:27 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule