• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ለየካቲት ፲፪ ቀን ፲፱፻፳፱ ዓ.ም. ሠማዕታት ቋሚ ጠበቃ መሆን የሁሉም ኢትዮጵያዊ ግዴታ ነው

February 20, 2016 11:10 am by Editor Leave a Comment

«ከታሪክ የማይማሩ ደግመው፣ ደጋግመው ለመሣሣት ይጋለጣሉ፤» የሚለው ብሂል ለዚህ ብሔራዊ በዓል መደብዘዝ አብይ ማጣቀሻ ነው። በደርግ የአገዛዝ ዘመን ይህ ዕለት ከብሔራዊ በዓልነት ደረጃ ወርዶ በመታሠቢያ ቀን ደረጃ እንዲከበር መደረጉ ትልቅ ታሪካዊ ስህተት ነበር። በትግሬ-ወያኔ አገዛዝ ይብስ ስህተቱ ወደማይታረምበት ደረጃ ደርሷል። ይህንን ለማለት የሚያስደፍረው የትግሬ-ወያኔ አገዛዝ ፋሽስት ኢጣሊያን ሲፋለሙ በሠማዕትነት ያለፉትን የአቡነ ጴጥሮስን፣ የደጃዝማጅ አፈወርቅ ወልደሰማዕትን እና ከሁሉም በላይ የማይጨው አርበኞቻችንን የመታሠቢያ ኃውልቶች አፍርሷል፣ ሌሎችንም ታሪካዊ ኃውልቶች አፍርሶ ድራሻቸውን ለማጥፋት እንቅስቃሴውን ቀጥሏል። ችግሩ የሰማዕታቱ መታሠቢያ የሆኑት ኃውልቶችን በማፍረስ ብቻ የሚገደብ አልሆነም፣ እንዲያውም ታሪካዊቱን አገር ኢትዮጵያን እስከመበታተን የሚደርስ ታላቅ ብሔራዊ ክህደት የሚፈጸመበት የታሪክ ወቅት ላይ እንገኛለን። ይህ ታሪካዊ ክህደት ከአሁኑ ትውልድ ተሻግሮ የተተኪው ትውልድም ማፈሪያ እንዳይሆን ጊዜው ሣይመሽ ዛሬውኑ ለተግባራዊ እርምጃ መነሣት ይኖርብናል።

ኢትዮጵያ እና ዜጎቿ በዚህ የታሪክ ማጥ ውስጥ ሲዳክሩ፣ በፋሽስት ኢጣሊያ ለተጨፈጨፉት ሠማዕታት ቋሚ ጠበቃ ሆኖ የቆመው “Global Alliance for Justice: The Ethiopian Cause” በመባል የሚታወቀው ተቋም ነው። ይህ ተቋም ከተመሠረተበት ጊዜ አንስቶ ለሠማዕቶቻችን ቀዳሚ ጠበቃ ነው ቢባል ማጋነን አይደለም። ሆኖም የሌሎቻችን ኢትዮጵያውያን ድጋፍ ግን እዚህ ግባ የሚባል አይደለም። ያጋጠመንን ብሔራዊ ፈተና በአሸናፊነት ለመወጣት፣ ከእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ዜጋ ጀምሮ በኢትዮጵያዊነት ስም እስከከተደራጁት ሁሉም ዓይነት ድርጅቶች እና ተቋሞች ከፍተኛ የሆነ ብሔራዊ አስተዋፅዖ ይጠበቃል። ስለሆነም ሠማዕቶቻችንን ከመዘከር ባሻገር ብሔራዊ ግዴታችንን ለመወጣት ሁላችንም በያለንበት የድርሻችንን መወጣት ይገባናል። የሺህ ኪሎሜትሮች ጉዞ የሚጀመረው በአንድ እርምጃ ነውና ይህንን ታሪካዊ ዕለት ኢትዮጵያውያን በያለንበት ከብሔራዊ በዓሎቻችን አንዱ አድርገን እንድናከብረው ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት የአደራ ጥሪውን ያቀርባል።

ለሠማዕታት ተገቢውን ክብር እንስጥ!

ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
Copyright © 2026 · Goolgule