• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በወልድያ ከተማ ነዋሪዎች ላይ የተፈጸመውን ግፍ፣ የሞረሽ ወገኔ ዐማራ ድርጅት በጽኑ ያወግዛል!

January 22, 2018 10:45 pm by Editor 2 Comments

እስከ መቼ ዋይታ! መከራና ለቅሶ!
በእኛ ላይ ይደርሳል መልሶ መላልሶ!

«የትግራይ ተራሮች የዐማራ መቃብር ይሆናሉ» በሚል መፈክር፣ ለኢትዮጵያ አንድነትና ሉዓላዊነት ዘብ የቆሙ ኢትዮጵያውያንን ከ1967 እስከ 1983 ባሉት 17 ዓመታት ውስጥ፣ የሁሉንም ነገድ ልጆች በዐማራነት ፈርጀው በግፍ መጨፍጨፋቸውን፣ በምርኮ የያዙዋቸውን ወታሮች የወባ መድኃኒት ነው ብለው፣ የውሻ መግደያ መርዝ ግተው በምድር ውስጥ በገነቧቸው እስር ቤቶች መፍጀታቸውን እናውቃለን። ሁሉም ግን የተገደሉት በዐማራነት ስም መሆኑን ስንገነዘብ ደግሞ፣ የትግሬ ወያኔ በዐማራ ላይ ያለው ጥላቻ የቱን ያህል ከፍተኛ እንደሆነ ያሳያል። ዛሬ ይህ መፈክር፣«የኢትዮጵያ ተራሮችና ሸለቆች፣ ከተሞችና ገጠሮች የዐማራ መቀበረያ ይሆናሉ»፣ በሚል የተቀየረ እንደሆነ፣ በአገሪቱ ውስጥ በዐማራው ነገድ ላይ የሚፈጸሙት ግድያዎችና ግፎች አፍ አውጥተው እየተናገሩ ነው። «ዐማራ ካልጠፋ የትግራይ ሕዝብ ማኅበራዊ ሰላም አያገኝም» በሚለው መመሪያቸው መሠረት ለአንድነትና ለኢትዮጵያዊነት የቆሙ የሁሉንም ኢትዮጵያዊ ነገድ ልጆች በግፍ መገደላቸውን ከትግሬ-ወያኔ በቀር የሌሎች ነገድ ልጆች አናውቅም ሊሉ የሚችሉ፣ አንድም መረጃ የሌላቸው፣ ሌላም በጥቅም የተገዙ ሆድ አደሮች ብቻ ናቸው። ይህ ካልሆነ አቶ ገብረመድኅን አርኣያ በተከታታይ በጠለምት፣ ወይቃይት፣ ተንቤን፣ ሽሬ፣ ደጀና፣ ዐድዋ ወዘተ በሚገኙ የባዶ ስድስት የማሰቃያ ጉድጓዶች ያለቁትን ወገኖቻችንን ያለመሰልቸት በዝርዝር ነግሮናል። የእኛ ችግር የመረጃ እጦ ሳይሆን፣ ዕውነቱ ሲነገረን፣ ነግ ለእኔ ብለን አስፈላጊውን ዝግጅት አለማድረጋችን ነው።

ይህም በመሆኑ፣ የትግሬ-ወያኔ ሥልጣንን ከተቆጣጠረ በኋላ፣ ዐማራውን በገዥ መደብነት፣ በጨቋኝነት፣ በትምክህተኝነት፣ ባለፉ ሥርዓቶች አቀንቃኝነት ስሞች ፈርጀው፣ የጎጃምንና የጎንደር ክፍለ ሀገር ነዋሪ ዐማራን «ሽፍታ ምንጠራ፣ መሬት ድልድል» የሚሉ የዘመቻ ስሞችን ሰጥተው ዐማራውን ትጥቁን ማስፈታታቸውን፣ መሬቱን መቀማታቸውን የምናስታውሰው በምሬት ነው። ድርጊቱ ትክክል አይደለም ያሉትን ልበ ሙሉ ጀግኖቻችንን በገፍ መግደላቸውና ማሰራቸው እንዲሁም ማሰደዳቸውን እናስታውሳለን። የወልቃይት፣ ጠገዴ፣ ጠለምትና ሠቲት ወረዳዎችን በመሬቱ ላይ ትግሬን ለማስፈር ከ1972 ዓም ጀምሮ በተከታታይ ዐማራዎቹን በግፍ መግደላቸው፣ ማሰራቸውና እንዲሰደዱ መደረጉ የአደባባይ ምስጢር ነው። በ1985 ጎንደር አደባባይ ኢየሱስ ለፀሎት በተሰበሰቡ የከተማው ነዋይዎች ላይ የደደቢት ሠራዊት በመትረጌስ የጨፈጨፋቸው ሰዎች ደም ዛሬም እየጨኸ ነው። በ1985 ዓም የቡትሮስ ቡትሮስን የወቅቱ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ፀሐፊን የኢትዮጵያን ጉብኝት ዓላማ በመቃወም ሰላማዊ ሰልፍ በወጡ ተማሪዎች ላይ የአገዛዙ አፋኝ ወታደራዊ ቡድን የገደላቸውን ተማሪዎች «በኢሠፓ» አባልነት እና በዐማራነት የወነጀላቸው እንደሆነ እናስታውሳለን።

መግለጫውን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: eprdf, moresh, Right Column - Primary Sidebar, tplf, Woldiya Massacre

Reader Interactions

Comments

  1. Mulugeta Andargie says

    January 24, 2018 12:59 am at 12:59 am

    Guys!!! Bene bekul ijigun yemizegnen Zena new!!!

    Reply
  2. Mulugeta Andargie says

    January 24, 2018 07:16 am at 7:16 am

    ሰዎች!! የፖሊሶች ድርሻ ቀንሷል ባይ ነኝ!!!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule