• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በወልድያ ከተማ ነዋሪዎች ላይ የተፈጸመውን ግፍ፣ የሞረሽ ወገኔ ዐማራ ድርጅት በጽኑ ያወግዛል!

January 22, 2018 10:45 pm by Editor 2 Comments

እስከ መቼ ዋይታ! መከራና ለቅሶ!
በእኛ ላይ ይደርሳል መልሶ መላልሶ!

«የትግራይ ተራሮች የዐማራ መቃብር ይሆናሉ» በሚል መፈክር፣ ለኢትዮጵያ አንድነትና ሉዓላዊነት ዘብ የቆሙ ኢትዮጵያውያንን ከ1967 እስከ 1983 ባሉት 17 ዓመታት ውስጥ፣ የሁሉንም ነገድ ልጆች በዐማራነት ፈርጀው በግፍ መጨፍጨፋቸውን፣ በምርኮ የያዙዋቸውን ወታሮች የወባ መድኃኒት ነው ብለው፣ የውሻ መግደያ መርዝ ግተው በምድር ውስጥ በገነቧቸው እስር ቤቶች መፍጀታቸውን እናውቃለን። ሁሉም ግን የተገደሉት በዐማራነት ስም መሆኑን ስንገነዘብ ደግሞ፣ የትግሬ ወያኔ በዐማራ ላይ ያለው ጥላቻ የቱን ያህል ከፍተኛ እንደሆነ ያሳያል። ዛሬ ይህ መፈክር፣«የኢትዮጵያ ተራሮችና ሸለቆች፣ ከተሞችና ገጠሮች የዐማራ መቀበረያ ይሆናሉ»፣ በሚል የተቀየረ እንደሆነ፣ በአገሪቱ ውስጥ በዐማራው ነገድ ላይ የሚፈጸሙት ግድያዎችና ግፎች አፍ አውጥተው እየተናገሩ ነው። «ዐማራ ካልጠፋ የትግራይ ሕዝብ ማኅበራዊ ሰላም አያገኝም» በሚለው መመሪያቸው መሠረት ለአንድነትና ለኢትዮጵያዊነት የቆሙ የሁሉንም ኢትዮጵያዊ ነገድ ልጆች በግፍ መገደላቸውን ከትግሬ-ወያኔ በቀር የሌሎች ነገድ ልጆች አናውቅም ሊሉ የሚችሉ፣ አንድም መረጃ የሌላቸው፣ ሌላም በጥቅም የተገዙ ሆድ አደሮች ብቻ ናቸው። ይህ ካልሆነ አቶ ገብረመድኅን አርኣያ በተከታታይ በጠለምት፣ ወይቃይት፣ ተንቤን፣ ሽሬ፣ ደጀና፣ ዐድዋ ወዘተ በሚገኙ የባዶ ስድስት የማሰቃያ ጉድጓዶች ያለቁትን ወገኖቻችንን ያለመሰልቸት በዝርዝር ነግሮናል። የእኛ ችግር የመረጃ እጦ ሳይሆን፣ ዕውነቱ ሲነገረን፣ ነግ ለእኔ ብለን አስፈላጊውን ዝግጅት አለማድረጋችን ነው።

ይህም በመሆኑ፣ የትግሬ-ወያኔ ሥልጣንን ከተቆጣጠረ በኋላ፣ ዐማራውን በገዥ መደብነት፣ በጨቋኝነት፣ በትምክህተኝነት፣ ባለፉ ሥርዓቶች አቀንቃኝነት ስሞች ፈርጀው፣ የጎጃምንና የጎንደር ክፍለ ሀገር ነዋሪ ዐማራን «ሽፍታ ምንጠራ፣ መሬት ድልድል» የሚሉ የዘመቻ ስሞችን ሰጥተው ዐማራውን ትጥቁን ማስፈታታቸውን፣ መሬቱን መቀማታቸውን የምናስታውሰው በምሬት ነው። ድርጊቱ ትክክል አይደለም ያሉትን ልበ ሙሉ ጀግኖቻችንን በገፍ መግደላቸውና ማሰራቸው እንዲሁም ማሰደዳቸውን እናስታውሳለን። የወልቃይት፣ ጠገዴ፣ ጠለምትና ሠቲት ወረዳዎችን በመሬቱ ላይ ትግሬን ለማስፈር ከ1972 ዓም ጀምሮ በተከታታይ ዐማራዎቹን በግፍ መግደላቸው፣ ማሰራቸውና እንዲሰደዱ መደረጉ የአደባባይ ምስጢር ነው። በ1985 ጎንደር አደባባይ ኢየሱስ ለፀሎት በተሰበሰቡ የከተማው ነዋይዎች ላይ የደደቢት ሠራዊት በመትረጌስ የጨፈጨፋቸው ሰዎች ደም ዛሬም እየጨኸ ነው። በ1985 ዓም የቡትሮስ ቡትሮስን የወቅቱ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ፀሐፊን የኢትዮጵያን ጉብኝት ዓላማ በመቃወም ሰላማዊ ሰልፍ በወጡ ተማሪዎች ላይ የአገዛዙ አፋኝ ወታደራዊ ቡድን የገደላቸውን ተማሪዎች «በኢሠፓ» አባልነት እና በዐማራነት የወነጀላቸው እንደሆነ እናስታውሳለን።

መግለጫውን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: eprdf, moresh, Right Column - Primary Sidebar, tplf, Woldiya Massacre

Reader Interactions

Comments

  1. Mulugeta Andargie says

    January 24, 2018 12:59 am at 12:59 am

    Guys!!! Bene bekul ijigun yemizegnen Zena new!!!

    Reply
  2. Mulugeta Andargie says

    January 24, 2018 07:16 am at 7:16 am

    ሰዎች!! የፖሊሶች ድርሻ ቀንሷል ባይ ነኝ!!!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule