• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በወልድያ ከተማ ነዋሪዎች ላይ የተፈጸመውን ግፍ፣ የሞረሽ ወገኔ ዐማራ ድርጅት በጽኑ ያወግዛል!

January 22, 2018 10:45 pm by Editor 2 Comments

እስከ መቼ ዋይታ! መከራና ለቅሶ!
በእኛ ላይ ይደርሳል መልሶ መላልሶ!

«የትግራይ ተራሮች የዐማራ መቃብር ይሆናሉ» በሚል መፈክር፣ ለኢትዮጵያ አንድነትና ሉዓላዊነት ዘብ የቆሙ ኢትዮጵያውያንን ከ1967 እስከ 1983 ባሉት 17 ዓመታት ውስጥ፣ የሁሉንም ነገድ ልጆች በዐማራነት ፈርጀው በግፍ መጨፍጨፋቸውን፣ በምርኮ የያዙዋቸውን ወታሮች የወባ መድኃኒት ነው ብለው፣ የውሻ መግደያ መርዝ ግተው በምድር ውስጥ በገነቧቸው እስር ቤቶች መፍጀታቸውን እናውቃለን። ሁሉም ግን የተገደሉት በዐማራነት ስም መሆኑን ስንገነዘብ ደግሞ፣ የትግሬ ወያኔ በዐማራ ላይ ያለው ጥላቻ የቱን ያህል ከፍተኛ እንደሆነ ያሳያል። ዛሬ ይህ መፈክር፣«የኢትዮጵያ ተራሮችና ሸለቆች፣ ከተሞችና ገጠሮች የዐማራ መቀበረያ ይሆናሉ»፣ በሚል የተቀየረ እንደሆነ፣ በአገሪቱ ውስጥ በዐማራው ነገድ ላይ የሚፈጸሙት ግድያዎችና ግፎች አፍ አውጥተው እየተናገሩ ነው። «ዐማራ ካልጠፋ የትግራይ ሕዝብ ማኅበራዊ ሰላም አያገኝም» በሚለው መመሪያቸው መሠረት ለአንድነትና ለኢትዮጵያዊነት የቆሙ የሁሉንም ኢትዮጵያዊ ነገድ ልጆች በግፍ መገደላቸውን ከትግሬ-ወያኔ በቀር የሌሎች ነገድ ልጆች አናውቅም ሊሉ የሚችሉ፣ አንድም መረጃ የሌላቸው፣ ሌላም በጥቅም የተገዙ ሆድ አደሮች ብቻ ናቸው። ይህ ካልሆነ አቶ ገብረመድኅን አርኣያ በተከታታይ በጠለምት፣ ወይቃይት፣ ተንቤን፣ ሽሬ፣ ደጀና፣ ዐድዋ ወዘተ በሚገኙ የባዶ ስድስት የማሰቃያ ጉድጓዶች ያለቁትን ወገኖቻችንን ያለመሰልቸት በዝርዝር ነግሮናል። የእኛ ችግር የመረጃ እጦ ሳይሆን፣ ዕውነቱ ሲነገረን፣ ነግ ለእኔ ብለን አስፈላጊውን ዝግጅት አለማድረጋችን ነው።

ይህም በመሆኑ፣ የትግሬ-ወያኔ ሥልጣንን ከተቆጣጠረ በኋላ፣ ዐማራውን በገዥ መደብነት፣ በጨቋኝነት፣ በትምክህተኝነት፣ ባለፉ ሥርዓቶች አቀንቃኝነት ስሞች ፈርጀው፣ የጎጃምንና የጎንደር ክፍለ ሀገር ነዋሪ ዐማራን «ሽፍታ ምንጠራ፣ መሬት ድልድል» የሚሉ የዘመቻ ስሞችን ሰጥተው ዐማራውን ትጥቁን ማስፈታታቸውን፣ መሬቱን መቀማታቸውን የምናስታውሰው በምሬት ነው። ድርጊቱ ትክክል አይደለም ያሉትን ልበ ሙሉ ጀግኖቻችንን በገፍ መግደላቸውና ማሰራቸው እንዲሁም ማሰደዳቸውን እናስታውሳለን። የወልቃይት፣ ጠገዴ፣ ጠለምትና ሠቲት ወረዳዎችን በመሬቱ ላይ ትግሬን ለማስፈር ከ1972 ዓም ጀምሮ በተከታታይ ዐማራዎቹን በግፍ መግደላቸው፣ ማሰራቸውና እንዲሰደዱ መደረጉ የአደባባይ ምስጢር ነው። በ1985 ጎንደር አደባባይ ኢየሱስ ለፀሎት በተሰበሰቡ የከተማው ነዋይዎች ላይ የደደቢት ሠራዊት በመትረጌስ የጨፈጨፋቸው ሰዎች ደም ዛሬም እየጨኸ ነው። በ1985 ዓም የቡትሮስ ቡትሮስን የወቅቱ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ፀሐፊን የኢትዮጵያን ጉብኝት ዓላማ በመቃወም ሰላማዊ ሰልፍ በወጡ ተማሪዎች ላይ የአገዛዙ አፋኝ ወታደራዊ ቡድን የገደላቸውን ተማሪዎች «በኢሠፓ» አባልነት እና በዐማራነት የወነጀላቸው እንደሆነ እናስታውሳለን።

መግለጫውን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Filed Under: Opinions Tagged With: eprdf, moresh, Right Column - Primary Sidebar, tplf, Woldiya Massacre

Reader Interactions

Comments

  1. Mulugeta Andargie says

    January 24, 2018 12:59 am at 12:59 am

    Guys!!! Bene bekul ijigun yemizegnen Zena new!!!

    Reply
  2. Mulugeta Andargie says

    January 24, 2018 07:16 am at 7:16 am

    ሰዎች!! የፖሊሶች ድርሻ ቀንሷል ባይ ነኝ!!!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
Copyright © 2026 · Goolgule