• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በወልድያ ከተማ ነዋሪዎች ላይ የተፈጸመውን ግፍ፣ የሞረሽ ወገኔ ዐማራ ድርጅት በጽኑ ያወግዛል!

January 22, 2018 10:45 pm by Editor 2 Comments

እስከ መቼ ዋይታ! መከራና ለቅሶ!
በእኛ ላይ ይደርሳል መልሶ መላልሶ!

«የትግራይ ተራሮች የዐማራ መቃብር ይሆናሉ» በሚል መፈክር፣ ለኢትዮጵያ አንድነትና ሉዓላዊነት ዘብ የቆሙ ኢትዮጵያውያንን ከ1967 እስከ 1983 ባሉት 17 ዓመታት ውስጥ፣ የሁሉንም ነገድ ልጆች በዐማራነት ፈርጀው በግፍ መጨፍጨፋቸውን፣ በምርኮ የያዙዋቸውን ወታሮች የወባ መድኃኒት ነው ብለው፣ የውሻ መግደያ መርዝ ግተው በምድር ውስጥ በገነቧቸው እስር ቤቶች መፍጀታቸውን እናውቃለን። ሁሉም ግን የተገደሉት በዐማራነት ስም መሆኑን ስንገነዘብ ደግሞ፣ የትግሬ ወያኔ በዐማራ ላይ ያለው ጥላቻ የቱን ያህል ከፍተኛ እንደሆነ ያሳያል። ዛሬ ይህ መፈክር፣«የኢትዮጵያ ተራሮችና ሸለቆች፣ ከተሞችና ገጠሮች የዐማራ መቀበረያ ይሆናሉ»፣ በሚል የተቀየረ እንደሆነ፣ በአገሪቱ ውስጥ በዐማራው ነገድ ላይ የሚፈጸሙት ግድያዎችና ግፎች አፍ አውጥተው እየተናገሩ ነው። «ዐማራ ካልጠፋ የትግራይ ሕዝብ ማኅበራዊ ሰላም አያገኝም» በሚለው መመሪያቸው መሠረት ለአንድነትና ለኢትዮጵያዊነት የቆሙ የሁሉንም ኢትዮጵያዊ ነገድ ልጆች በግፍ መገደላቸውን ከትግሬ-ወያኔ በቀር የሌሎች ነገድ ልጆች አናውቅም ሊሉ የሚችሉ፣ አንድም መረጃ የሌላቸው፣ ሌላም በጥቅም የተገዙ ሆድ አደሮች ብቻ ናቸው። ይህ ካልሆነ አቶ ገብረመድኅን አርኣያ በተከታታይ በጠለምት፣ ወይቃይት፣ ተንቤን፣ ሽሬ፣ ደጀና፣ ዐድዋ ወዘተ በሚገኙ የባዶ ስድስት የማሰቃያ ጉድጓዶች ያለቁትን ወገኖቻችንን ያለመሰልቸት በዝርዝር ነግሮናል። የእኛ ችግር የመረጃ እጦ ሳይሆን፣ ዕውነቱ ሲነገረን፣ ነግ ለእኔ ብለን አስፈላጊውን ዝግጅት አለማድረጋችን ነው።

ይህም በመሆኑ፣ የትግሬ-ወያኔ ሥልጣንን ከተቆጣጠረ በኋላ፣ ዐማራውን በገዥ መደብነት፣ በጨቋኝነት፣ በትምክህተኝነት፣ ባለፉ ሥርዓቶች አቀንቃኝነት ስሞች ፈርጀው፣ የጎጃምንና የጎንደር ክፍለ ሀገር ነዋሪ ዐማራን «ሽፍታ ምንጠራ፣ መሬት ድልድል» የሚሉ የዘመቻ ስሞችን ሰጥተው ዐማራውን ትጥቁን ማስፈታታቸውን፣ መሬቱን መቀማታቸውን የምናስታውሰው በምሬት ነው። ድርጊቱ ትክክል አይደለም ያሉትን ልበ ሙሉ ጀግኖቻችንን በገፍ መግደላቸውና ማሰራቸው እንዲሁም ማሰደዳቸውን እናስታውሳለን። የወልቃይት፣ ጠገዴ፣ ጠለምትና ሠቲት ወረዳዎችን በመሬቱ ላይ ትግሬን ለማስፈር ከ1972 ዓም ጀምሮ በተከታታይ ዐማራዎቹን በግፍ መግደላቸው፣ ማሰራቸውና እንዲሰደዱ መደረጉ የአደባባይ ምስጢር ነው። በ1985 ጎንደር አደባባይ ኢየሱስ ለፀሎት በተሰበሰቡ የከተማው ነዋይዎች ላይ የደደቢት ሠራዊት በመትረጌስ የጨፈጨፋቸው ሰዎች ደም ዛሬም እየጨኸ ነው። በ1985 ዓም የቡትሮስ ቡትሮስን የወቅቱ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ፀሐፊን የኢትዮጵያን ጉብኝት ዓላማ በመቃወም ሰላማዊ ሰልፍ በወጡ ተማሪዎች ላይ የአገዛዙ አፋኝ ወታደራዊ ቡድን የገደላቸውን ተማሪዎች «በኢሠፓ» አባልነት እና በዐማራነት የወነጀላቸው እንደሆነ እናስታውሳለን።

መግለጫውን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: eprdf, moresh, Right Column - Primary Sidebar, tplf, Woldiya Massacre

Reader Interactions

Comments

  1. Mulugeta Andargie says

    January 24, 2018 12:59 am at 12:59 am

    Guys!!! Bene bekul ijigun yemizegnen Zena new!!!

    Reply
  2. Mulugeta Andargie says

    January 24, 2018 07:16 am at 7:16 am

    ሰዎች!! የፖሊሶች ድርሻ ቀንሷል ባይ ነኝ!!!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule