• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ግድያ፣ ሥቃይና መፈናቀል በእኛ ይቁም!

September 16, 2017 09:42 pm by Editor Leave a Comment

ሰሞኑን የትግሬ ወያኔ ዘረኛ አገዛዝ አሰልጥኖ ጃዝ ባላቸው ቅልብ ነፍሰ ገዳዮቹ፣ በኦሮሞ እህት ወንድሞቻችን ላይ እያደረሰ ያለውን ግድያና ማፈናቀል፣ የዐማራ ኅልውና ለኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት በጽኑ ያወግዛል። ይህ አንዱን ነገድ በሌላው ነገድ ላይ በማስነሳት፣ አንደኛው ሌላውን ከክልሌ ውጣ ማለት የወያኔ የሥልጣን ዘመን ማራዘሚያና ኢትዮጵያን የማፈራረሻ ስልቱ እንደሆነ፣ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ነኝ ብሎ የሚያምን ሁሉ ዐውቆ ፣ወያኔ ሆን ብሎ ከሚያጠምደው የራስ በራስ መጠፋፋት ተግባር ራሱን ሊቆጥብ ይገባል ብለን እናምናለን።

ይህ ሰሞኑን ወያኔ ሆን ብሎ በሶማሌና በኦሮሞ ነገዶች መካከል የለኮሰው ብጥብጥ ፣ ከገጠመው ሕዝባዊ ቁጣና ተቃውሞ የሕዝቡን የትብብር እንቅስቃሴ ለማዳከምና ሕዝባዊ አመጹን በሚሻው መልኩ ለማጨናገፍ ፣ የትግሉን አቅጣጫ ለማሳትና የአገዛዙን ዕድሜ ለማራዘም ያጠመደው ወጥመድ መሆኑን በግራ በቀኙ ያሉ የሁለቱ ነገድ አባሎች ሊያስተውሉት ይገባል። የኦሮሞና የሶማሊያ ነጎዶች ዘላለማዊ ሲሆኑ፣ የትግሬ ወያኔ አገዛዝ ጊዜአዊ ነው። ጠፊና ተለዋጭ ነው። ኦሮሞና ሶማሌ ለዘመናት አብረው የኖሩትን ያህል ወደፊትም ተፈጥሮ በአንድ መልከዐምድር አቆራኝቷቸዋልና ማንም ሊለያያቸው አይችልም። ይህን ወያኔ አስቦና አቅዶ በሁለቱ ነገዶች መካካል ከራሱ ፍጡር «የሶማሊያ ክልል» ርዕሰ መስተዳድር ነኝ፣ ከሚለው ግለሰብ በስተኋላ ሆኖ፣በኦሮሞ እህት ወንድሞቻችን ላይ የወሰደው የግድያና የማፈናቀል ተግባር፣ እኛ ለራሳችን ነገድ ኅልውና እና መብት የምንታገል እና በእኛ ላይ በከፋ ሁኔታ ላለፉት 27 ዓመታት ሲፈጸምብን የኖርንና ያለን የዐማራው ልጆች፣ በተመሳሳይ ሁኔታ፣ በሌሎች ላይ ሲፈጸም ስናይ የዝሆን ጀሮ ይስጠኝ ልንል አይቻለንም። በመሆኑም በኦሮሞ ወገኖቻችን ላይ የተፈጸመውን ግድያ፣ ስቃይና ማፈናቀል በጥብቅ ከማውገዝ አልፈን፣ ኢትዮጵያ ማለት በውስጧ የሚኖሩ ነገድና ጎሳዎች አንድነት የፈጠሩት አገርና የነርሱ ማንነት መለያና መታወቂያ ናት፤ ይህ ማንነትና መታወቂያ ተጠናክሮና ዳብሮ ሊቀጥል ይገባል ከሚሉ ቡድኖችና ስብስቦች ጋር በመሆን፣ የወያኔን የመከፋፈል ሤራ ከማክሸፍ ማሻገር፣ ወያኔን ገፍትሮ ለመጣል ለሚደረገው ግብግብ፣የዐማራ ኅልውና ለኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት የሚችለውን ሁሉ ለማድረግ ዝግጁ ነው። (የመግለጫውን ሙሉ ቃል ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am
  • የኦነግ ሸኔ አባላትን ዕድሜ ለማሳጠር የጂፒኤስ ቴክኖሎጂ ጥቅም ላይ እየዋለ ነው December 7, 2020 12:38 am
  • የቆሰሉ ወታደሮች በጠቅላይ ሚኒስትሩ ተጎበኙ December 6, 2020 11:41 pm
  • “ከዚህ በኋላ ይዘን እንታገላለን እንጂ ሠጥተን አንጠይቅም” ኮሎኔል ደመቀ December 2, 2020 12:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule