• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ግድያ፣ ሥቃይና መፈናቀል በእኛ ይቁም!

September 16, 2017 09:42 pm by Editor Leave a Comment

ሰሞኑን የትግሬ ወያኔ ዘረኛ አገዛዝ አሰልጥኖ ጃዝ ባላቸው ቅልብ ነፍሰ ገዳዮቹ፣ በኦሮሞ እህት ወንድሞቻችን ላይ እያደረሰ ያለውን ግድያና ማፈናቀል፣ የዐማራ ኅልውና ለኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት በጽኑ ያወግዛል። ይህ አንዱን ነገድ በሌላው ነገድ ላይ በማስነሳት፣ አንደኛው ሌላውን ከክልሌ ውጣ ማለት የወያኔ የሥልጣን ዘመን ማራዘሚያና ኢትዮጵያን የማፈራረሻ ስልቱ እንደሆነ፣ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ነኝ ብሎ የሚያምን ሁሉ ዐውቆ ፣ወያኔ ሆን ብሎ ከሚያጠምደው የራስ በራስ መጠፋፋት ተግባር ራሱን ሊቆጥብ ይገባል ብለን እናምናለን።

ይህ ሰሞኑን ወያኔ ሆን ብሎ በሶማሌና በኦሮሞ ነገዶች መካከል የለኮሰው ብጥብጥ ፣ ከገጠመው ሕዝባዊ ቁጣና ተቃውሞ የሕዝቡን የትብብር እንቅስቃሴ ለማዳከምና ሕዝባዊ አመጹን በሚሻው መልኩ ለማጨናገፍ ፣ የትግሉን አቅጣጫ ለማሳትና የአገዛዙን ዕድሜ ለማራዘም ያጠመደው ወጥመድ መሆኑን በግራ በቀኙ ያሉ የሁለቱ ነገድ አባሎች ሊያስተውሉት ይገባል። የኦሮሞና የሶማሊያ ነጎዶች ዘላለማዊ ሲሆኑ፣ የትግሬ ወያኔ አገዛዝ ጊዜአዊ ነው። ጠፊና ተለዋጭ ነው። ኦሮሞና ሶማሌ ለዘመናት አብረው የኖሩትን ያህል ወደፊትም ተፈጥሮ በአንድ መልከዐምድር አቆራኝቷቸዋልና ማንም ሊለያያቸው አይችልም። ይህን ወያኔ አስቦና አቅዶ በሁለቱ ነገዶች መካካል ከራሱ ፍጡር «የሶማሊያ ክልል» ርዕሰ መስተዳድር ነኝ፣ ከሚለው ግለሰብ በስተኋላ ሆኖ፣በኦሮሞ እህት ወንድሞቻችን ላይ የወሰደው የግድያና የማፈናቀል ተግባር፣ እኛ ለራሳችን ነገድ ኅልውና እና መብት የምንታገል እና በእኛ ላይ በከፋ ሁኔታ ላለፉት 27 ዓመታት ሲፈጸምብን የኖርንና ያለን የዐማራው ልጆች፣ በተመሳሳይ ሁኔታ፣ በሌሎች ላይ ሲፈጸም ስናይ የዝሆን ጀሮ ይስጠኝ ልንል አይቻለንም። በመሆኑም በኦሮሞ ወገኖቻችን ላይ የተፈጸመውን ግድያ፣ ስቃይና ማፈናቀል በጥብቅ ከማውገዝ አልፈን፣ ኢትዮጵያ ማለት በውስጧ የሚኖሩ ነገድና ጎሳዎች አንድነት የፈጠሩት አገርና የነርሱ ማንነት መለያና መታወቂያ ናት፤ ይህ ማንነትና መታወቂያ ተጠናክሮና ዳብሮ ሊቀጥል ይገባል ከሚሉ ቡድኖችና ስብስቦች ጋር በመሆን፣ የወያኔን የመከፋፈል ሤራ ከማክሸፍ ማሻገር፣ ወያኔን ገፍትሮ ለመጣል ለሚደረገው ግብግብ፣የዐማራ ኅልውና ለኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት የሚችለውን ሁሉ ለማድረግ ዝግጁ ነው። (የመግለጫውን ሙሉ ቃል ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አበበ እንጂ መቼ ሞተ!”          July 19, 2022 04:57 pm
  • ሸኔ አመራሮቹንና ጠንካራ ይዞታዎቹን እያጣ ነው July 19, 2022 01:55 am
  • የወልቃይት አማራ የተሰቃየባቸው የትህነግ 15 ድብቅ እስር ቤቶች! July 18, 2022 03:13 pm
  • ገቢ የማያስገኙ የዜና ርዕሶች July 17, 2022 05:36 pm
  • “ዛሬ ‘ኃያል ነን’ የሚሉ ሀገራት ኢትዮጵያ ላይ በሚዲያ /በመረጃ/፣ በዲፕሎማሲ፣ በሳይበር እና በተልእኮ የተቀነባበረ ‘ግራጫ ጦርነት’ እያካሄዱባት ነው” ጠ/ሚ ዐቢይ July 7, 2022 10:03 am
  • የኦሮሞ ልሂቃንና ፖለቲከኞች በአማራ ተወላጆች ላይ እየደረሰ ያለውን “የዘር ማጥፋት” ወንጀል እንዲያወግዙት አብን ጠየቀ July 6, 2022 01:38 pm
  • “አማራን ኦሮሚያ ውስጥ የመግደል እና የመጨፍጨፍ እቅድ የኦነግ ሳይሆን የኦሮሚያ ብልጽግና ነው” አቶ ሃንጋሳ July 6, 2022 01:53 am
  • “በኢትዮጵያዊያን የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ በመግባት ሀገሪቱን ማተራመስ አለብን” አይማን አብድልአዚዝ ግብጻዊው ፖለቲከኛ July 5, 2022 12:57 pm
  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule