• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሰሞኑን በተደረገው ጦርነት ከ10ሺህ በላይ የትህነግ ታጣቂዎች ተገድለዋል

September 5, 2021 03:07 pm by Editor Leave a Comment

የኢትዮጵያ መካለከያ ሠራዊት ቅዳሜ በሰጠው መግለጫ በከሃዲው ጄነራል ምግበይ ይመራል የሚመራው “አርሚ 1” የተባለ ኃይል ሙሉ በሙሉ መደምሰሱን በይፋ አሳወቀ።

መግለጫውን የሰጡት የመከላከያ ሚኒስቴር የሠራዊት ግንባታ ዋና አስተባባሪ ሌተናል ጀኔራል ባጫ ደበሌ ሲሆኑ የኢትዮጵያ ሰራዊትን ግዳጅ አፈጻጸምና ወቅታዊ ሁኔታ በተመለከተ ዝርዝር ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ህወሓት ህፃናትን አሰልፎ በአማራ ክልል ወረራ መፈፀሙን ያነሱት ሌ/ጄነራል ባጫ የቡድኑ ፍላጎት ኢትዮጵያ የምትባልን ሀገር መበታተን ነው ብለዋል።

ህወሓት ስልጠና ያልወሰዱ ህፃናትን ወደ ጦርነት በመማገድ ላይ ነው ሲሉም አክለዋል። የትግራይ ወጣቶችን ከተቻለ ሁለት ቀን አሰልጥኖ አንድ ጠመንጃ ለአምስት ሰጥቶ ወደግምባር ካስገቡ በኋላ መሪዎቹ ውጊያውን ስለሚያውቁ ተኩስ ሲበዛባቸው ወደኋላ የሚሸሹትን እንደሚገድል ነው የገለጹት።

ሌ/ጄነራሉ በመግለጫቸው፥ ህወሓት በ10 ሺዎች የሚቆጠሩ የትግራይ ወጣቶችን አሰልፎ በ4 አርሚ ራሱን በማደራጀት በአማራ ክልል የሚያደርገውን ወረራ እንደቀጠለ ጠቁመዋል።

በ4 አርሚዎች ካደራጃቸው ኃይሎች መካከል አንደኛው በጀነራል ምግበይ የሚመራ ሲሆን ይህ ኃይል አርሚ 1 ተብሎ የሚጠራ እንደሆነ አስረድተዋል።

ሌ/ጄነራል ባጫ፥ ይኸው ኃይል በሁመራ አካባቢ አደርቃይ እና ማይ ፀብሪ አካባቢ ደባርቅንና ዳባትን በመቁረጥ ጎንደርን በመያዝ ከዚያ በኋላ ሁመራን ነፃ ለማድረግ ቢንቀሳቀስም ሙሉ በሙሉ ተደምስሷል ብለዋል።

በ3 ክፍለ ጦሮች የተደራጀው ይህ የአሸባሪ ኃይል በእያንዳንዱ ክፍለ ጦር ስር ሶስት ኮሮችን ያቀፈ ሲሆን ሰሞኑን በተደረገ ውጊያ ከ5 ሺ 600 በላይ ሙት ከ2 ሺ 300 በላይ ደግሞ ቁስለኛ ሲሆኑ፣ 2 ሺ አባላቱ ተማርከው ቀሪዎቹም ተበታትነውበታል።

በዚህም ህወሓት ወደሱዳን ለመውጣት ያቀደው ሙከራ ሳይሳካለት ቀርቷል፥ ሙሉ በሙሉም ተዘግቶበታል ሲሉ ተናግረዋል።

ከዚህ በተጨማሪ በሜ/ጀነራል ዮሐንስ ወ/ጊዮርጊስ የሚመራ አርሚ 2 የተባለ ሃይል በጋሸና ከክምር ድንጋይ ጀምሮ በተደረገ ውጊያ ሁለቱ ክፍለጦሮች እንደተደመሰሱበት፤ በውጭ በብ/ጀነራል ፍስሃ የሚመራ እና የሰለጠነ አርሚ 3 የሚባል ኃይል በሽንፋ በኩል ከቅማንት ቅጥረኛ ቡድን ጋር በመተባባር ጥቃት ቢሰነዝርም ተደምስሷል የተረፈውም ወደመጣበት ተመልሷል ብለዋል።

“ይህ ሃይል በተለይ የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ስራ ለማስተጓጎል ቢያስብም እቅዱ በጀግናው ሃይላችን ተደምስሷል” ብለዋል ሌ/ጄነራል ባጫ።

አሸባሪ ቡድኑ እየደረሰበት ያለው ኪሳራ በጣም ብዙ ነው ያሉት ጄነራል ባጫ በተለይ የትግራይ ወጣቶችን እያስጨረሰ መሆኑን ገልጸዋል።

ጦርነቱ በተደረገባችው አካባቢዎቸ በጣምመ አስቀያሚ የሆኑ ኢሰብአዊ ድርጊቶችንና የጁንታውን የአሸባሪነት ተግባርም አይተናል ብለዋል ሌ/ጀነራሉ።

በጦርነቱ የቆሰሉትን ለይቶ በተለይ ከባድ አደጋ የደረሰባቸውን ባሉበት ገድሎ እንደሚሸሽ የገለጹት ጀነራል ባጫ ደበሌ ይህም የቡድኑን ባሕርይ ያመላከተ ነው ብለዋል።

አሸባሪው ህወሓት በከፈተው አወደውጊያ ሁሉ ሽንፈት ቢያጋጥመውም ያሰለፋቸውን ህጻናት ጭምር ለመግደል ያልሳሳ አረመኔ መሆኑን ገልጸዋል።

እያንዳንዱ የትግራይ ወጣት ነፃ እናወጣሃለን በሚሉ የጁንታ ጥርቅም አመራሮች ግድያ ህይወቱ እየጠፋ መሆኑ አሳዛኝ ነው ብለዋል ሌተናል ጀነራል ባጫ ደበሌ። (ቲክቫህ፤ ኢብኮ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: operation dismantle tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule