• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በመልካም አስተዳደር ከአፍሪካ 52 አገራት ኢትዮጵያ 32ኛ!

March 7, 2015 08:40 am by Editor Leave a Comment

* የናሚቢያው ፕሬዚዳንት የሞ ኢብራሂም ሽልማትን አሸነፉ

የሞ ኢብራሂም ፋውንዴሽን በየዓመቱ በሚያወጣው የአፍሪካ መልካም አስተዳደር ጠቋሚ ኢትዮጵያ ከ52 አገሮች 32ኛ ወጣች፡፡

እ.ኤ.አ. የ2014 የሞ ኢብራሂም የመልካም አስተዳደር ጠቋሚ ከ30 ገለልተኛ የአፍሪካና ዓለም አቀፍ ታማኝ ምንጮች የተገኙ ከመቶ በላይ መለኪያዎችን በመገምገም ነው የአገሮች የመልካም አስተዳደር ደረጃን ማውጣቱን የገለጸው፡፡ ዋነኛ መለኪያዎቹ አራት ምሰሶዎች መሆናቸውን የሚገልጸው ሞ ኢብራሂም ፋውንዴሽን፣ እነዚህም ሕዝቦች ከመንግሥታቸው የሚጠብቋቸውና መንግሥትም ማቅረብ የሚጠበቅበት ግዴታዎችን የሚዳስስ ነው፡፡ እነዚህ መሠረታዊ ምሰሶዎች የመሠረተ ልማት ዝርጋታ፣ የመናገር ነፃነት፣ የንፅህናና የንብረት ባለቤትነት መብቶች ጥበቃን የሚዳስሱ ናቸው፡፡ በዚህም መሠረት ሞሪሺየስ፣ ኬፕ ቨርዴና ቦትስዋና ከአንድ እስከ ሦስተኛ ወጥተዋል፡፡ ደቡብ አፍሪካ፣ ሲሸልስ፣ ናሚቢያ፣ ጋና፣ ቱኒዚያ፣ ሴኔጋልና ሌሴቶ እስከ አሥረኛ ደረጃ ላይ ይገኛሉ፡፡

ከምሥራቅ አፍሪካ አገሮች መካከል ሩዋንዳ በ11ኛ ደረጃ፣ ኬንያ 17ኛ ደረጃ፣ ኡጋንዳ 19ኛ ደረጃ ላይ ሲገኙ ኢትዮጵያ 32ኛ ላይ ትገኛለች፡፡ ሶማሊያ የመጨረሻው ደረጃ ላይ ስትገኝ ማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክና ኤርትራ ይከተሏታል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ የሞ ኢብራሂም ፋውንዴሽን በየዓመቱ ለአፍሪካ መሪዎች የሚሰጠውን ሽልማት የሥልጣን ዘመናቸውን በማጠናቀቅ ላይ ለሚገኙት የናሚቢያው ፕሬዚዳንት አድርጓል፡፡ ይህ ሽልማት ላለፉት አራት ዓመታት ብቁ የሆነ መሪ ባለመገኘቱ ሳይካሄድ መቆየቱ ይታወሳል፡፡

ሽልማቱ በሥልጣን ላይ እያለ ለአገሩ መልካም አስተዳደር ላሰፈነ፣ የሕዝቦቹን የኑሮ ደረጃ ከፍ ላደረገና በሰላማዊ ሽግግር ከሥልጣን ለወረደ መሪ የሚሰጥ ነው፡፡ ሽልማቱም በአሥር ዓመት ጊዜ ውስጥ ተከፍሎ የሚጠናቀቅ አምስት ሚሊዮን ዶላርና እስከ ዕድሜ ልክ ደግሞ በየዓመቱ 200 ሺሕ ዶላር ያስገኛል፡፡

እ.ኤ.አ. ከ2004 ጀምሮ ሁለት የሥልጣን ጊዜያትን ያሳለፉት የናሚቢያው ፕሬዚዳንት ሂፈክፑንዬ ፓሃምባ፣ በቅርቡ በተደረገ ምርጫ ላሸነፉትና ገና ሥልጣን ላልተረከቡት ሄግ ጌንጐበ ይለቃሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

የዛሬ ዓመት አካባቢ የኢሕአዴግ ምክር ቤት የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በዘላቂነት መፍታት የሚቻለው “በልማታዊነት ላይ በተመሠረተ የተራዘመ ትግል ነው” በማለት በዚህ ረገድ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የሚያስችሉ አቅጣጫዎች መቀመጣቸውን አስታውቋል፡፡ በዚህም የሕዝብን እርካታ ለማረጋገጥ የተጀመረው ልማታዊ መንገድ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጿል፡፡

በአሁኑ ጊዜ በመላ አገሪቱ የመልካም አስተዳደር ችግር መኖሩ ሁላችንንም ያግባባናል፡፡ የዚህ ችግር መሠረታዊ ምክንያት ምንድነው ብለን ስንጠይቅ መልሱን በቀላሉ እናገኘዋለን፡፡ በመላ አገሪቱ በመንሰራፋት ላይ ያለው ሙስና የመጀመሪያው ተጠያቂ ሲሆን የተሿሚዎች ብቃት ማነስ፣ የሕዝብ አገልጋይነት መንፈስ መኮስመን፣ ደንታ ቢስነትና በራስ ያለመተማመን ይጠቀሳሉ፡፡

የመልካም አስተዳደር ችግር ዋነኛ ጠንቅ የሆነው ሙስና ከአነስተኛው የአስተዳደር እርከን ከወረዳ ጀምሮ የፌዴራል መንግሥት መዋቅር ውስጥ ሰርጎ ገብቷል፡፡ አንድን አዋጅ ለማስፈጸም የሚወጡ መመርያዎችና ደንቦች የሚፈጥሯቸውን ክፍተቶች በመጠቀም ባለጉዳዮችን በማጉላላት በሕገወጥ መንገድ የሚጠቀሙ በዝተዋል፡፡ በመሬት አስተዳደር፣ በግንባታ ፈቃድ፣ በብቃት ማረጋገጫ፣ በንግድ ፈቃድ አሰጣጥና ዕድሳት፣ በገቢዎችና ጉምሩክ አሠራሮች፣ ማስረጃ በማረጋገጥ፣ በኮንዶሚኒየም ቤቶች አሰጣጥ፣ ወዘተ ተገልጋዩ ሕዝብ በሕግ የተከበረለት መብት ተጥሶ የሙሰኞች ሲሳይ እየሆነ ነው፡፡ አንገታቸውን ደፍተው የሚሠሩ ትጉሃን  ሠራተኞችን የሚያሳቅቁ ድርጊቶች ይፈጸማሉ፡፡

በብዙዎቹ የአስተዳደር እርከኖች ላይ ተሿሚ የሆኑ ግለሰቦች ማንነት ሲታይ ደግሞ ሙሉ ለሙሉ በሚቻል ሁኔታ የገዥው ፓርቲ አባላት ናቸው፡፡ አባል በመሆናቸው ብቻ የማይመጥኑት ኃላፊነት ላይ ተቀምጠው ከሚያግበሰብሱት ሕገወጥ ጥቅም በተጨማሪ፣ በአቅም ማነስ ምክንያት ሥራ መሥራት ያቃታቸው አሉ፡፡ ድሮ ጠንካራ ግምገማና ቁጥጥር ስለነበር ራሱን ያላዘጋጀ ሰው ሥልጣን አያገኝም ነበር፡፡ ዛሬ የመልካም አስተዳደር ችግር የዜጎችን አዕምሮ እያወከ የለብ ለብ ግምገማ ሲደረግ እንኳን አይታይም፡፡ በዚህ ላይ ደንታ ቢስነትና በራስ ያለመተማመን ጣሪያ በመንካታቸው የሕዝቡ ምሬተ በየዕለቱ እየጨመረ ነው፡፡ እንዲህ ዓይነቱ ችግር ለያዥ ለገናዥ ሲያስቸግር እንዴት የተራዘመ ትግል ያስፈልጋል ይባላል? ደፋርና በራሱ የሚተማመን የነበረ ዜጋ ተሸማቆ አድርባይነት ሲነግሥ እንዴት ዝም ይባላል?

በየወረዳው፣ በየክፍለ ከተማውና የተለያዩ የአስተዳደር መዋቅሮች ለጉዳይ ሲኬድ ስብሰባ፣ ሥልጠና፣ ትምህርታዊ ጉብኝት፣ የአቅም ግንባታ፣ ልምድ ልውውጥ፣ ወዘተ እየተባለ ለስንት ጉዳዮች የሚውለው የአገሪቱ ሀብት ይባክናል፡፡ ከዚህ ሁሉ ግርግር በኋላ የአሠራር ወይም የአመለካከት ለውጥ አይታይም፡፡ ሥልጠናውና አቅም ግንባታው አስፈላጊ መሆኑ ባያጠራጥርም፣ ሥራ እየቆመ ለውሳኔ የሚፈለጉ ሹማምንት በየሰበቡ ሥራ ላይ አለመገኘታቸው ሌላው የመልካም አስተዳደር ጠንቅ ነው፡፡ ለአበልና ለተለያዩ ጥቅማ ጥቅሞች አንድ ወይም የተወሰኑ ሹማምንት ከአንድ መሥርያ ቤት በተደጋጋሚ ሲጠፉ ለስንቶች መከራ እንደሆነ አይታሰብም፡፡ ለዚህ ዓይነቱ ችግር ፈጣን ዕርምጃ ወይስ የተራዘመ ትግል? (ምንጭ: ሪፖርተር)

Filed Under: News Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
Copyright © 2026 · Goolgule