• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በመልካም አስተዳደር ከአፍሪካ 52 አገራት ኢትዮጵያ 32ኛ!

March 7, 2015 08:40 am by Editor Leave a Comment

* የናሚቢያው ፕሬዚዳንት የሞ ኢብራሂም ሽልማትን አሸነፉ

የሞ ኢብራሂም ፋውንዴሽን በየዓመቱ በሚያወጣው የአፍሪካ መልካም አስተዳደር ጠቋሚ ኢትዮጵያ ከ52 አገሮች 32ኛ ወጣች፡፡

እ.ኤ.አ. የ2014 የሞ ኢብራሂም የመልካም አስተዳደር ጠቋሚ ከ30 ገለልተኛ የአፍሪካና ዓለም አቀፍ ታማኝ ምንጮች የተገኙ ከመቶ በላይ መለኪያዎችን በመገምገም ነው የአገሮች የመልካም አስተዳደር ደረጃን ማውጣቱን የገለጸው፡፡ ዋነኛ መለኪያዎቹ አራት ምሰሶዎች መሆናቸውን የሚገልጸው ሞ ኢብራሂም ፋውንዴሽን፣ እነዚህም ሕዝቦች ከመንግሥታቸው የሚጠብቋቸውና መንግሥትም ማቅረብ የሚጠበቅበት ግዴታዎችን የሚዳስስ ነው፡፡ እነዚህ መሠረታዊ ምሰሶዎች የመሠረተ ልማት ዝርጋታ፣ የመናገር ነፃነት፣ የንፅህናና የንብረት ባለቤትነት መብቶች ጥበቃን የሚዳስሱ ናቸው፡፡ በዚህም መሠረት ሞሪሺየስ፣ ኬፕ ቨርዴና ቦትስዋና ከአንድ እስከ ሦስተኛ ወጥተዋል፡፡ ደቡብ አፍሪካ፣ ሲሸልስ፣ ናሚቢያ፣ ጋና፣ ቱኒዚያ፣ ሴኔጋልና ሌሴቶ እስከ አሥረኛ ደረጃ ላይ ይገኛሉ፡፡

ከምሥራቅ አፍሪካ አገሮች መካከል ሩዋንዳ በ11ኛ ደረጃ፣ ኬንያ 17ኛ ደረጃ፣ ኡጋንዳ 19ኛ ደረጃ ላይ ሲገኙ ኢትዮጵያ 32ኛ ላይ ትገኛለች፡፡ ሶማሊያ የመጨረሻው ደረጃ ላይ ስትገኝ ማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክና ኤርትራ ይከተሏታል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ የሞ ኢብራሂም ፋውንዴሽን በየዓመቱ ለአፍሪካ መሪዎች የሚሰጠውን ሽልማት የሥልጣን ዘመናቸውን በማጠናቀቅ ላይ ለሚገኙት የናሚቢያው ፕሬዚዳንት አድርጓል፡፡ ይህ ሽልማት ላለፉት አራት ዓመታት ብቁ የሆነ መሪ ባለመገኘቱ ሳይካሄድ መቆየቱ ይታወሳል፡፡

ሽልማቱ በሥልጣን ላይ እያለ ለአገሩ መልካም አስተዳደር ላሰፈነ፣ የሕዝቦቹን የኑሮ ደረጃ ከፍ ላደረገና በሰላማዊ ሽግግር ከሥልጣን ለወረደ መሪ የሚሰጥ ነው፡፡ ሽልማቱም በአሥር ዓመት ጊዜ ውስጥ ተከፍሎ የሚጠናቀቅ አምስት ሚሊዮን ዶላርና እስከ ዕድሜ ልክ ደግሞ በየዓመቱ 200 ሺሕ ዶላር ያስገኛል፡፡

እ.ኤ.አ. ከ2004 ጀምሮ ሁለት የሥልጣን ጊዜያትን ያሳለፉት የናሚቢያው ፕሬዚዳንት ሂፈክፑንዬ ፓሃምባ፣ በቅርቡ በተደረገ ምርጫ ላሸነፉትና ገና ሥልጣን ላልተረከቡት ሄግ ጌንጐበ ይለቃሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

የዛሬ ዓመት አካባቢ የኢሕአዴግ ምክር ቤት የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በዘላቂነት መፍታት የሚቻለው “በልማታዊነት ላይ በተመሠረተ የተራዘመ ትግል ነው” በማለት በዚህ ረገድ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የሚያስችሉ አቅጣጫዎች መቀመጣቸውን አስታውቋል፡፡ በዚህም የሕዝብን እርካታ ለማረጋገጥ የተጀመረው ልማታዊ መንገድ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጿል፡፡

በአሁኑ ጊዜ በመላ አገሪቱ የመልካም አስተዳደር ችግር መኖሩ ሁላችንንም ያግባባናል፡፡ የዚህ ችግር መሠረታዊ ምክንያት ምንድነው ብለን ስንጠይቅ መልሱን በቀላሉ እናገኘዋለን፡፡ በመላ አገሪቱ በመንሰራፋት ላይ ያለው ሙስና የመጀመሪያው ተጠያቂ ሲሆን የተሿሚዎች ብቃት ማነስ፣ የሕዝብ አገልጋይነት መንፈስ መኮስመን፣ ደንታ ቢስነትና በራስ ያለመተማመን ይጠቀሳሉ፡፡

የመልካም አስተዳደር ችግር ዋነኛ ጠንቅ የሆነው ሙስና ከአነስተኛው የአስተዳደር እርከን ከወረዳ ጀምሮ የፌዴራል መንግሥት መዋቅር ውስጥ ሰርጎ ገብቷል፡፡ አንድን አዋጅ ለማስፈጸም የሚወጡ መመርያዎችና ደንቦች የሚፈጥሯቸውን ክፍተቶች በመጠቀም ባለጉዳዮችን በማጉላላት በሕገወጥ መንገድ የሚጠቀሙ በዝተዋል፡፡ በመሬት አስተዳደር፣ በግንባታ ፈቃድ፣ በብቃት ማረጋገጫ፣ በንግድ ፈቃድ አሰጣጥና ዕድሳት፣ በገቢዎችና ጉምሩክ አሠራሮች፣ ማስረጃ በማረጋገጥ፣ በኮንዶሚኒየም ቤቶች አሰጣጥ፣ ወዘተ ተገልጋዩ ሕዝብ በሕግ የተከበረለት መብት ተጥሶ የሙሰኞች ሲሳይ እየሆነ ነው፡፡ አንገታቸውን ደፍተው የሚሠሩ ትጉሃን  ሠራተኞችን የሚያሳቅቁ ድርጊቶች ይፈጸማሉ፡፡

በብዙዎቹ የአስተዳደር እርከኖች ላይ ተሿሚ የሆኑ ግለሰቦች ማንነት ሲታይ ደግሞ ሙሉ ለሙሉ በሚቻል ሁኔታ የገዥው ፓርቲ አባላት ናቸው፡፡ አባል በመሆናቸው ብቻ የማይመጥኑት ኃላፊነት ላይ ተቀምጠው ከሚያግበሰብሱት ሕገወጥ ጥቅም በተጨማሪ፣ በአቅም ማነስ ምክንያት ሥራ መሥራት ያቃታቸው አሉ፡፡ ድሮ ጠንካራ ግምገማና ቁጥጥር ስለነበር ራሱን ያላዘጋጀ ሰው ሥልጣን አያገኝም ነበር፡፡ ዛሬ የመልካም አስተዳደር ችግር የዜጎችን አዕምሮ እያወከ የለብ ለብ ግምገማ ሲደረግ እንኳን አይታይም፡፡ በዚህ ላይ ደንታ ቢስነትና በራስ ያለመተማመን ጣሪያ በመንካታቸው የሕዝቡ ምሬተ በየዕለቱ እየጨመረ ነው፡፡ እንዲህ ዓይነቱ ችግር ለያዥ ለገናዥ ሲያስቸግር እንዴት የተራዘመ ትግል ያስፈልጋል ይባላል? ደፋርና በራሱ የሚተማመን የነበረ ዜጋ ተሸማቆ አድርባይነት ሲነግሥ እንዴት ዝም ይባላል?

በየወረዳው፣ በየክፍለ ከተማውና የተለያዩ የአስተዳደር መዋቅሮች ለጉዳይ ሲኬድ ስብሰባ፣ ሥልጠና፣ ትምህርታዊ ጉብኝት፣ የአቅም ግንባታ፣ ልምድ ልውውጥ፣ ወዘተ እየተባለ ለስንት ጉዳዮች የሚውለው የአገሪቱ ሀብት ይባክናል፡፡ ከዚህ ሁሉ ግርግር በኋላ የአሠራር ወይም የአመለካከት ለውጥ አይታይም፡፡ ሥልጠናውና አቅም ግንባታው አስፈላጊ መሆኑ ባያጠራጥርም፣ ሥራ እየቆመ ለውሳኔ የሚፈለጉ ሹማምንት በየሰበቡ ሥራ ላይ አለመገኘታቸው ሌላው የመልካም አስተዳደር ጠንቅ ነው፡፡ ለአበልና ለተለያዩ ጥቅማ ጥቅሞች አንድ ወይም የተወሰኑ ሹማምንት ከአንድ መሥርያ ቤት በተደጋጋሚ ሲጠፉ ለስንቶች መከራ እንደሆነ አይታሰብም፡፡ ለዚህ ዓይነቱ ችግር ፈጣን ዕርምጃ ወይስ የተራዘመ ትግል? (ምንጭ: ሪፖርተር)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የሲኖዶሱ ውዝግብ አካሄድና መጪው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ February 6, 2023 02:03 am
  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule