• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በመልካም አስተዳደር ከአፍሪካ 52 አገራት ኢትዮጵያ 32ኛ!

March 7, 2015 08:40 am by Editor Leave a Comment

* የናሚቢያው ፕሬዚዳንት የሞ ኢብራሂም ሽልማትን አሸነፉ

የሞ ኢብራሂም ፋውንዴሽን በየዓመቱ በሚያወጣው የአፍሪካ መልካም አስተዳደር ጠቋሚ ኢትዮጵያ ከ52 አገሮች 32ኛ ወጣች፡፡

እ.ኤ.አ. የ2014 የሞ ኢብራሂም የመልካም አስተዳደር ጠቋሚ ከ30 ገለልተኛ የአፍሪካና ዓለም አቀፍ ታማኝ ምንጮች የተገኙ ከመቶ በላይ መለኪያዎችን በመገምገም ነው የአገሮች የመልካም አስተዳደር ደረጃን ማውጣቱን የገለጸው፡፡ ዋነኛ መለኪያዎቹ አራት ምሰሶዎች መሆናቸውን የሚገልጸው ሞ ኢብራሂም ፋውንዴሽን፣ እነዚህም ሕዝቦች ከመንግሥታቸው የሚጠብቋቸውና መንግሥትም ማቅረብ የሚጠበቅበት ግዴታዎችን የሚዳስስ ነው፡፡ እነዚህ መሠረታዊ ምሰሶዎች የመሠረተ ልማት ዝርጋታ፣ የመናገር ነፃነት፣ የንፅህናና የንብረት ባለቤትነት መብቶች ጥበቃን የሚዳስሱ ናቸው፡፡ በዚህም መሠረት ሞሪሺየስ፣ ኬፕ ቨርዴና ቦትስዋና ከአንድ እስከ ሦስተኛ ወጥተዋል፡፡ ደቡብ አፍሪካ፣ ሲሸልስ፣ ናሚቢያ፣ ጋና፣ ቱኒዚያ፣ ሴኔጋልና ሌሴቶ እስከ አሥረኛ ደረጃ ላይ ይገኛሉ፡፡

ከምሥራቅ አፍሪካ አገሮች መካከል ሩዋንዳ በ11ኛ ደረጃ፣ ኬንያ 17ኛ ደረጃ፣ ኡጋንዳ 19ኛ ደረጃ ላይ ሲገኙ ኢትዮጵያ 32ኛ ላይ ትገኛለች፡፡ ሶማሊያ የመጨረሻው ደረጃ ላይ ስትገኝ ማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክና ኤርትራ ይከተሏታል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ የሞ ኢብራሂም ፋውንዴሽን በየዓመቱ ለአፍሪካ መሪዎች የሚሰጠውን ሽልማት የሥልጣን ዘመናቸውን በማጠናቀቅ ላይ ለሚገኙት የናሚቢያው ፕሬዚዳንት አድርጓል፡፡ ይህ ሽልማት ላለፉት አራት ዓመታት ብቁ የሆነ መሪ ባለመገኘቱ ሳይካሄድ መቆየቱ ይታወሳል፡፡

ሽልማቱ በሥልጣን ላይ እያለ ለአገሩ መልካም አስተዳደር ላሰፈነ፣ የሕዝቦቹን የኑሮ ደረጃ ከፍ ላደረገና በሰላማዊ ሽግግር ከሥልጣን ለወረደ መሪ የሚሰጥ ነው፡፡ ሽልማቱም በአሥር ዓመት ጊዜ ውስጥ ተከፍሎ የሚጠናቀቅ አምስት ሚሊዮን ዶላርና እስከ ዕድሜ ልክ ደግሞ በየዓመቱ 200 ሺሕ ዶላር ያስገኛል፡፡

እ.ኤ.አ. ከ2004 ጀምሮ ሁለት የሥልጣን ጊዜያትን ያሳለፉት የናሚቢያው ፕሬዚዳንት ሂፈክፑንዬ ፓሃምባ፣ በቅርቡ በተደረገ ምርጫ ላሸነፉትና ገና ሥልጣን ላልተረከቡት ሄግ ጌንጐበ ይለቃሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

የዛሬ ዓመት አካባቢ የኢሕአዴግ ምክር ቤት የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በዘላቂነት መፍታት የሚቻለው “በልማታዊነት ላይ በተመሠረተ የተራዘመ ትግል ነው” በማለት በዚህ ረገድ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የሚያስችሉ አቅጣጫዎች መቀመጣቸውን አስታውቋል፡፡ በዚህም የሕዝብን እርካታ ለማረጋገጥ የተጀመረው ልማታዊ መንገድ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጿል፡፡

በአሁኑ ጊዜ በመላ አገሪቱ የመልካም አስተዳደር ችግር መኖሩ ሁላችንንም ያግባባናል፡፡ የዚህ ችግር መሠረታዊ ምክንያት ምንድነው ብለን ስንጠይቅ መልሱን በቀላሉ እናገኘዋለን፡፡ በመላ አገሪቱ በመንሰራፋት ላይ ያለው ሙስና የመጀመሪያው ተጠያቂ ሲሆን የተሿሚዎች ብቃት ማነስ፣ የሕዝብ አገልጋይነት መንፈስ መኮስመን፣ ደንታ ቢስነትና በራስ ያለመተማመን ይጠቀሳሉ፡፡

የመልካም አስተዳደር ችግር ዋነኛ ጠንቅ የሆነው ሙስና ከአነስተኛው የአስተዳደር እርከን ከወረዳ ጀምሮ የፌዴራል መንግሥት መዋቅር ውስጥ ሰርጎ ገብቷል፡፡ አንድን አዋጅ ለማስፈጸም የሚወጡ መመርያዎችና ደንቦች የሚፈጥሯቸውን ክፍተቶች በመጠቀም ባለጉዳዮችን በማጉላላት በሕገወጥ መንገድ የሚጠቀሙ በዝተዋል፡፡ በመሬት አስተዳደር፣ በግንባታ ፈቃድ፣ በብቃት ማረጋገጫ፣ በንግድ ፈቃድ አሰጣጥና ዕድሳት፣ በገቢዎችና ጉምሩክ አሠራሮች፣ ማስረጃ በማረጋገጥ፣ በኮንዶሚኒየም ቤቶች አሰጣጥ፣ ወዘተ ተገልጋዩ ሕዝብ በሕግ የተከበረለት መብት ተጥሶ የሙሰኞች ሲሳይ እየሆነ ነው፡፡ አንገታቸውን ደፍተው የሚሠሩ ትጉሃን  ሠራተኞችን የሚያሳቅቁ ድርጊቶች ይፈጸማሉ፡፡

በብዙዎቹ የአስተዳደር እርከኖች ላይ ተሿሚ የሆኑ ግለሰቦች ማንነት ሲታይ ደግሞ ሙሉ ለሙሉ በሚቻል ሁኔታ የገዥው ፓርቲ አባላት ናቸው፡፡ አባል በመሆናቸው ብቻ የማይመጥኑት ኃላፊነት ላይ ተቀምጠው ከሚያግበሰብሱት ሕገወጥ ጥቅም በተጨማሪ፣ በአቅም ማነስ ምክንያት ሥራ መሥራት ያቃታቸው አሉ፡፡ ድሮ ጠንካራ ግምገማና ቁጥጥር ስለነበር ራሱን ያላዘጋጀ ሰው ሥልጣን አያገኝም ነበር፡፡ ዛሬ የመልካም አስተዳደር ችግር የዜጎችን አዕምሮ እያወከ የለብ ለብ ግምገማ ሲደረግ እንኳን አይታይም፡፡ በዚህ ላይ ደንታ ቢስነትና በራስ ያለመተማመን ጣሪያ በመንካታቸው የሕዝቡ ምሬተ በየዕለቱ እየጨመረ ነው፡፡ እንዲህ ዓይነቱ ችግር ለያዥ ለገናዥ ሲያስቸግር እንዴት የተራዘመ ትግል ያስፈልጋል ይባላል? ደፋርና በራሱ የሚተማመን የነበረ ዜጋ ተሸማቆ አድርባይነት ሲነግሥ እንዴት ዝም ይባላል?

በየወረዳው፣ በየክፍለ ከተማውና የተለያዩ የአስተዳደር መዋቅሮች ለጉዳይ ሲኬድ ስብሰባ፣ ሥልጠና፣ ትምህርታዊ ጉብኝት፣ የአቅም ግንባታ፣ ልምድ ልውውጥ፣ ወዘተ እየተባለ ለስንት ጉዳዮች የሚውለው የአገሪቱ ሀብት ይባክናል፡፡ ከዚህ ሁሉ ግርግር በኋላ የአሠራር ወይም የአመለካከት ለውጥ አይታይም፡፡ ሥልጠናውና አቅም ግንባታው አስፈላጊ መሆኑ ባያጠራጥርም፣ ሥራ እየቆመ ለውሳኔ የሚፈለጉ ሹማምንት በየሰበቡ ሥራ ላይ አለመገኘታቸው ሌላው የመልካም አስተዳደር ጠንቅ ነው፡፡ ለአበልና ለተለያዩ ጥቅማ ጥቅሞች አንድ ወይም የተወሰኑ ሹማምንት ከአንድ መሥርያ ቤት በተደጋጋሚ ሲጠፉ ለስንቶች መከራ እንደሆነ አይታሰብም፡፡ ለዚህ ዓይነቱ ችግር ፈጣን ዕርምጃ ወይስ የተራዘመ ትግል? (ምንጭ: ሪፖርተር)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule