• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከ9ሺህ በላይ ፈላሻ ሙራዎች ወደ እስራኤል ሊጓዙ ነው

November 16, 2015 11:13 am by Editor Leave a Comment

ከ25 ዓመታት በላይ ከኢትዮጵያ ወደ እስራኤል ለመጓዝ እየጠበቁ ያሉ በተለየ ፈላሻ ሙራ ተብለው የሚጠሩት ቤተ እስኤላውያን ወደ “ቅድስት አገራቸው” እንዲመጡ የእስራኤል መንግሥት ወሰነ፡፡ እስኤል እንደገቡም የአይሁድ እምነትን በተመለከተ የተሃድሶ ትምህርት እንደሚሰጣቸው ተመልክቷል፡፡

በእስራኤል ያሉ እና ሌሎች ዓለምአቀፋዊ የዜና ምንጮች እንደዘገቡት የጠ/ሚ/ር ቢኒያም ኔታንያሁ መንግሥት ውሳኔውን ያስተላለፈው እሁድ ዕለት በሙሉ ድምጽ ነበር፡፡ ይህ የአሁኑ ውሳኔ ከመሰጠቱ በፊት የዛሬ ሁለት ዓመት እስራኤል ምንም ዓይነት ዜጋዋ በኢትዮጵያ እንደሌለ ይፋ ነበር፡፡ “ዛሬ ጠቃሚ ውሳኔ አስተላልፈናል” በማለት የተናገሩት ኔታንያሁ ውሳኔው በእስራኤል እየኖሩ ከቤተሰቦቻቸው ለተለያዩት ኢትዮጵያውያን ተስፋ ሰጪና ጠቃሚ እንደሆነ በላኩት መግለጫ አመልክተዋል፡፡

ከዚህ በፊት እስራኤል “የተስፋዋ አገር ዜጎቿን” ከኢትዮጵያ ያስወጣች ሲሆን መጨረሻ ላይ የቀሩት በተለይ ፈላሻ ሙራ የሚባሉት በ18ኛውና በ19ኛው ክፍል ዘመናት ወደ ክርስትና እንዲቀየሩ የተደረጉት ናቸው፡፡ ፈላሻ ሙራ የሚለው ስም የአይሁድን ሕግጋት የማይከተልና በግድ ወይም በፈቃደኝነት ወደ ክርስትና የተቀየረ የሚወክል እንደሆነ Jewishpress.com ባወጣው ዜና ላይ ጠቁሟል፡፡

የኤርትራ ክፍለ ሃገርን ጨምሮ ከጎንደር የመጡት 9ሺህ አንድ መቶ የሚሆኑት አይሁድ ተብለው ስለማይጠሩ እስራኤል እንደደረሱ በአክራሪ የአይሁድ ዕምነት መምህራን የተሃድሶ ትምህርት እንዲሰጣቸው የተወሰነ መሆኑን የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚ/ሩ ማስታወቃቸውን የዜና ዘገባዎቹ ጠቁመዋል፡፡ ከሚሰጧቸው ትምህርቶች መካከል የአይሁድ ሕግጋት እና የጽዮናዊነት እንቅስቃሴ ታሪክ ይገኝባቸዋል፡፡ ፈላሻ ሙራዎቹ በአሁኑ ጊዜ በአዲስ አበባና በጎንደር ይገኛሉ፡፡

ጠ/ሚ/ሩ ባወጡት መግለጫ ላይ እንደተናገሩት እነዚህ “የመጨረሻ” የተባሉት ተጓዦች በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ወደ እስራኤል ይጓዛሉ፡፡ ለዚህ በርካታ ዓመታት ለፈጀ ውሳኔ ተግባራዊነት በአሁኑ ጊዜ የእስራኤል ሸንጎ አባል የሆኑት የኢትዮጵያ ዝርያ ያላቸው እንደራሴ አብርሃም ንጉሤ ከፍተኛ ተጽዕኖ እንዳደረጉ በዜና ዘገባው ላይ ተመልክቷል፡፡ “ለአይሁድ ሕዝብ ይህ ታላቅ ቀን ነው” ያሉት እንደራሴው “ለሺዎች ዓመታት ኢትዮጵያውያን አይሁዶች ወደ እስራኤል ለመመለስ ሲጸልዩ ኖረዋል፤ ለዓስርተ ዓመታት ደግሞ ከቤተሰቦቻቸው ተለያይተው ሲጠብቁ ቆይተዋል፤ ዛሬ ጸሎታቸው ተሰምቷል” ብለዋል፡፡

መጽሓፍቅዱሳዊ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ኢየሱስ ክርስቶስ “ቤታችሁ የተፈታ ይሆናል” ካለ በኋላ በወቅቱ የሮም ጄኔራል የነበረው ቲቶስ (ታይተስ በኋላ አባቱን ተክቶ ቄሣር ሆኗል) ኢየሩሳሌምን ከብቦ ካሰጨነቃት በኋላ በ70ዓም ቤተመቅደሱን በማፍረስ ከተማዋን በሮም ቁጥጥር ሥር ካዋለ በኋላ የአይሁድ ሕዝብ “የእግዚአብሔር ምርጥነት” በይፋ አክትሞ ክርስትና ቦታውን ወስዷል በማለት አንዳንድ የሥነመለኮት ምሁራን ይከራከራሉ፡፡ በአይሁድ እምነት መሠረት መሲሕ ገና ይገለጣል ተብሎ ስለሚጠበቅ በምሁራኑ የሚቀርበው አስተያየት ፈጽሞ ተቀባይነት የለውም፡፡

የዛሬ ሃያ ዓመት አካባቢ አስቀድመው ወደ እስራኤል የሄዱት ኢትዮጵያውያን እንደ ዜጋ የለገሱት ደም ኤችአይቪ/ኤይድስ ይኖርበታል በሚል ስጋት ለበርካታ ዓመታት ሲለግሱ የነበረው ደም ሲደፋ የቆየ መሆኑ ይፋ በተደረገበት ጊዜ ከፍተኛ ቁጣን በቤተ እስኤላውያኑ ዘንድ አስነስቶ እንደነበር ይታወሳል፡፡ ከዚያ በኋላ ሁኔታዎች ይስተካከላሉ የሚል ተስፋ የተሰጠ ቢሆንም ኢትዮጵያውያኑ ከሌሎች በተለየ በድሃ የአገሪቱ ከተሞች እንደሚሰፍሩ፤ አሰቃቂ የፖሊስ ግፍ እንደሚፈጸምባቸው፤ በዘር መድልዖ በደል እንደሚደርስባቸው በቅርብ ጊዜያት የተከሰቱት ዕውነታዎች ያስረዳሉ፡፡ ሆኖም የጠ/ሚ/ር ኔታኒያሁ መንግሥት ችግሮችን እንቀርፋለን፤ ሁኔታዎችን እናሻሽላለን በማለት በተደጋጋሚ ቃል ገብቷል፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule