• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

መስከረም፣ መስከረም

September 16, 2017 01:57 am by Editor 2 Comments

ኢዮሃ አበባዬ / መስከረም ጠባዬ
ኢዮሃ አበባዬ / መስከረም ጠባዬ …

የወራት ሁሉ ቁንጮ መስከረም። ግንቦት እሳት፣ ሰኔ ውኃ ነው። የኢትዮጵያ ምድር በእሳትና በውኃ ሳትጠመቅ እረፍት እና ልምላሜዋን አታጋራም። ከግንቦት ማብቂያ እስከ መስከረም መጀመሪያ ሦስት ወር ብቻ ቢሆንም፣ እስኪጠባ መጠበቁ ሦስት ዓመት ያስመስለዋል። የመከራ አንዱ ቀን እንደ ዘላለም ነው፤ እግሮቹም በብረት ሰንሰለት ከብደዋል። ደስታ ግን ክንፍ እንጂ እግር የለው።meskerem1

ግንቦት ድርቅና ብክነት ነው። መስከረም እረፍትና ልምላሜ። ወራት መኳንንት ቢሆኑ መስከረም ንጉሥ ነው። መስከረም ደጅ ያስጠናል። ደጁን ካልከፈተ፣ ፊት ከነሳ ጥቅምትን ማየት አይቻል። አስራ ሁለቱን ወር እንደ ምን ተንፏቆ የደረሰ፣ አምስት እና ስድስት ቀን ጨምሮ ደጅ ይጠናል፤ ራሱንና ጓዳውን እንዲያዘገጃጅ ይገደዳል።

ይህን ያህል ርቀት ተጕዘው ለጥቂት ከደጅ የሚቀሩ አሉ። የሰኔ ጎርፍ ጠርጎ ወሰዳቸው የተባሉ ነፍስና ሥጋቸውን በጥርሳቸው አንጠልጥለው የሐምሌና የነሐሴን ሙላት ተሻገሩ። ሌላው ዳር ቆሞ የደረሱለትንና ያልደረሱለትን ምኞቶቹን ይከልሳል፤ ያመላልሳል። ሆያ ሆዬ ይላል። ሙልሙል ይጎረድማል።

እንደ ሞት ብቅ ይላል፤ መስከረም ሳይታሰብ ብቅ ይላል፤ እንዳላስጠበቀ ሌቱን ገስግሶ ከተፍ ይላል። ያለፈውን ዘመን አስረጅቶ ቀብሮ፣ አዲስ ሕይወት አዲስ ተስፋ ደግሶ ይቀበላል። “ሕይወት እነሆ!” ይላል።

መስከረም፣ እንቁጣጣሽ እንቁጣጣሽ ይላል፤ ጉዝጓዝ ሣር ትኵስ ቡና ይሸታል። እንኳን ደህና መጣሽ። ዓመት ዓመት ያምጣሽ፣
ኢዮሃ አበባዬ / መስከረም ጠባዬ
ኢዮሃ አበባዬ / መስከረም ጠባዬ
መስከረም ሲጠባ
ወደ አገሬ ልግባ …

የግንቦት ሕጻናት ቢይና አፈር ያቦናሉ፣ አፈር ያፍሳሉ፤ ንፍሮና ቆሎ ያፍሳሉ፤ ጠግበው ቁቅ ይላሉ። የመስከረም ሕጻናት እሸት እሸት ይሸታሉ፤ ያስገሳሉ። ቄኪያቸውን ሰው አፍ ላይ ይስላሉ። አበባ ይስላሉ። አደይ አበባ ይለቅማሉ። ወረቀት ያቀልማሉ፤ ለክርስትና አባታቸው ለክርስትና እናታቸው ለሚወዱት አያታቸው ለሚያቀብጣቸው አጎታቸው ለአክስታቸው ለጎረቤታቸው ያበረክታሉ። ስሙኒ ይለቅማሉ። ሜንታ ከረሜላ ይመጠምጣሉ፤ በደስታ ከረሜላ ይደሰታሉ። ቼሬአሊያ ይኮረሽማሉ፤ ጮርናቄ ያላምጣሉ። ይሳሳቃሉ። እንደ ተርብ ይሯሯጣሉ። ግንባር ለግንባር ተላትመው ይላቀሳሉ። ይንከባለላሉ። ይንቦጫረቃሉ። ስሙኒአቸውን ደጋግመው ይቆጥራሉ። ከሸመቱበት ወዲህ ፍራንኩ ማቃጨሉ ለምን እንደ ቀነሰ በጥርጣሬ ያሰላሉ።

ከሐምሌና ከነሐሴ ጎርፍ የተረፉ ይሰባሰባሉ። በየቤቱ በየቤተክርስቲያኑ ይሰባሰባሉ። በየአደባባዩ ይጨፍራሉ። አክ እንትፍ ያበዛሉ። ይገባበዛሉ። ይጎራረሳሉ። በሞቅታ ይንገዳገዳሉ። ይደጋገፋሉ። ሰላምታ ይሰጣጣሉ። ተስፋ ይቀባበላሉ፤ ተስፋ እንደ ማይጉም ይቀባባሉ። መስከረም ደስታ ነው፤ ልምላሜ ነው፤ ንጹሕ አየር ነው፤ ጤና ነው፤ ንቁ እርጥብ ፀሐይ ነው፤ ሰማያዊ ሰማይ ነው፤ የተባዘተ ጥሩ ጥጥ ብሩህ ደመና ነው። ብርሃንም እንደ ዝናብ፣ በታጨደ መስክ ላይ፥ በምድርም ላይ እንደሚንጠባጠብ ጠብታ ነው። የሚካበድ የአድማሳት ጥቁር ቡልኮ ወልቆ፣ እንቅልፍ የሚያስይዝ የሰላምና የሲሳይ ዝናብ ነው። ሰማይ የሚሰነጥቅ ጋራ የሚንድ የነጎድጓድ ድምጽ በወፎች ዝማሬ ሲተካ ነው። የደስታ ጅራፍ የሚያስያነጭ፣ የገደል ማሚቶ ኵልል ብሎ የወጣበት ጤዛ የሚያስመርቅ። መስከረም፣ ዳዊት የሚያስደግም ወር ነው፣

ምድርን ጎበኘሃት፣ አጠጣሃትም / ብልጥግናዋንም እጅግ አበዛህ
የእግዚአብሔር ወንዝ ውኃን የተመላ ነው / ምግባቸውን አዘጋጀህ፣ እንዲሁ ታሰናዳለህና
ትልምዋን ታረካለህ / ቦይዋንም ታስተካክላለህ
በነጠብጣብ ታለሰልሳታለህ / ቡቃያዋንም ትባርካለህ
በቸርነትህ ዓመትን ታቀዳጃለህ / ምድረ በዳውም ስብን ይጠግባል
የምድረ በዳ ተራሮች ይረካሉ / ኮረብቶችም በደስታ ይታጠቃሉ
ማሰማርያዎች መንጎችን ለበሱ / ሸለቆችም በእህል ተሸፈኑ
በደስታ ይጮኻሉ፣ ይዘምራሉም። [ዳዊት 65፡9-13]

meskerem2ደጁን አንኳኵተው ለከፈተላቸው መስከረም ግብዣው ብዙ ነው፤ ድግሱ የጦፈ። የጋመ በቆሎ እሸት ጥብስ። ቅቤ ልውስ አንጮቴና ቡና ቀላ። ትኵስ አቦል ቡና ቅቤ በረካ። በአስራ ሁለት የጉራጌ መስቀል፣ በአስራ ስድስት ደመራ፣ በአስራ ሰባት ለተቀረነው መስቀል። ጠፍቶ የከረመው የሚገኝበት፣ እሳትና ዐመድ የተስማማበት። ግንቦት በፀሐይ እሳት ያቦነነውን፣ መስከረም በደመና እሳት አብርዶ ያሳርገዋል።

በአስራ ስምንት፣ ተማሪ ልብሱን አጥቦ ተስፋ ፍለጋ፣ እውቀት ፍለጋ ደብተሩን ይዞ ይራመዳል። ከጳጉሜ [ጳጉሜን፣ ቋቍሜ] መስከረም እስኪሸኝ፣ የአገር ሰላምታ እንደ በረቅ እንደ ነጎድጓድ ከቅርብና ከርቀት ይንጎደጎዳል፤ እንደ ምንጭ ውኃ እንደ ጅረት ይዥጎደጎዳል፦
እንኳን አደረሰህ … እንኳን አደረሰሽ
እንኳን አደረሰሽ … አሜን እንኳን አደረስዎ
እንኳን አደረሰዎ … እንኳን አደረሰሽ
እንኳን አደረሳችሁ … እንኳን አደረስዎ አባባ
ሃፒ ኒው ይር ማዘር … ሃቢኑር ያርግሽ እቴ፣ እንኳን አደረሰሽ በዪልኝ እናትሽን
አደረሳችሁ … ይመስገነው … ክብሩ ይስፋ…

meskerem3መስከረም የወሮች ሁሉ ንጉሥ ነው። የኢትዮጵያ ክልሎች፣ ወረዳዎች፣ አደባባዮች፣ ቀዬዎች እና ጓዳዎች ይዘጋጁ፤ ከሩቅ እጅ ይንሱ፣ ከቅርብ እጅ ይንሱ። የሰላም እሳት ያጋዩ፣ ያደፈውን እና ያረጀውን ያቃጥሉ። የመስቀሉ እሳት ተውሳኩን ያጋይ! የአጋንንትን መንጋ ያክስም። የተስፋ ችቦ ይብራ። በአንድነት ሆ! ይበሉ። የደስታ ሆታቸውን ሸለቆ ሸንተረሩ ጋራና ፈፋው ተቀብሎ ያስተጋባ። “ምነው ተሽኮረመምሽ? እንደ መስቀል ወፍ የት ጠፍተሽ ከረምሽ?” ይባባሉ።

ኢዮሃ አበባዬ / መስከረም ጠባዬ
መስከረም ሲጠባ / አደይ ሲፈነዳ
እንኳን ሰው ዘመዱን / ይጠይቃል ባዳ

ለተቀረው ዓለም፣ አዲስ ዓመት ጥር ነው። ለኛ አዲስ፣ መስከረም ነው።

የሰላምና የምህረት ዓመት ይሁንልን!

© ምትኩ አዲሱ፣ 2010 ዓ.ም

Image credit: skyscrapercity.com; googleimages.com


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Mulugeta Andargie says

    September 20, 2017 04:02 am at 4:02 am

    መስከረም!! መስክ አረም!! መስከረም!
    ያዲስ ዓመት ለምለም ወራት! ለምለም!
    ክረምት አላፊ ሃምሌ ነሃሴ!
    ዓዲስ ዓመቱ መጣ ፈሰሴ
    መስከረም ጠባ ወፎች ዘመሩ
    ቢጫው ዓደዩ ሲታይ ማማሩ!
    በየመኩ ላይ ተዘርቶ ፈክቶ
    እንደ መስከረም ማን አለ ከቶ??

    Reply
  2. Mitiku says

    October 1, 2017 12:18 am at 12:18 am

    ውድ ሙሉጌታ፣
    መስከሮምን አሳመርከው አደል? አንተም ይመርብህ!
    ምትኩ

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule